ጅማ ዩኒቨርሲቲ ያስገነባው ዘመናዊ የህክምና ማዕከል ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ሌሎችች ባለስልጣናት በተገኙበት ይመረቃል

Home Forums Semonegna Stories ጅማ ዩኒቨርሲቲ ያስገነባው ዘመናዊ የህክምና ማዕከል ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ሌሎችች ባለስልጣናት በተገኙበት ይመረቃል

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #8870
    Anonymous
    Inactive

    የጅማ ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ተመረቀ

    ኢትዮጵያ፣ የሱዳንና የጂቡቲ መሪዎች የጅማ ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታልን መረቁ።

    ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ከሱዳኑ ፕሬዝዳንት ኦማር ሀሰን አልበሽር እና ከጅቡቲው ፕሬዝዳንት እስማኤል ኦማር ጌሌ ጋር በመሆን ነው ሆስፒታሉን ዛሬ የመረቁት።

    ሆስፒታሉ 800 የመኝታ ክፍሎች ያሉት ሲሆን በደቡብ ምዕራብ የአገሪቱ ክፍል ለሚገኙ ከ20 ሚሊዮን በላይ ሰዎች የህክምና አገልግሎት መስጠት የሚችል ነው።

    እንዲሁም ለደቡብ ሱዳን እና አጎራባች አገሮች የህክምና አገልግሎት እንዲሰጥ ተደርጎ የተገነባ ነው።

    ሆስፒታሉ ከጤና አገልግሎቱ ባሻገር የምርምር፣ የማስተማሪያና የማህበረሰብ አገልግሎቶችን ለመስጠት ያስችላል።

    መሪዎቹ የህክምና ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ 300 ተማሪዎችንም ይመርቃሉ ተብሎ ይጠበቃል።

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.