የጅማ ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ተመረቀ
ኢትዮጵያ፣ የሱዳንና የጂቡቲ መሪዎች የጅማ ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታልን መረቁ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ከሱዳኑ ፕሬዝዳንት ኦማር ሀሰን አልበሽር እና ከጅቡቲው ፕሬዝዳንት እስማኤል ኦማር ጌሌ ጋር በመሆን ነው ሆስፒታሉን ዛሬ የመረቁት።
ሆስፒታሉ 800 የመኝታ ክፍሎች ያሉት ሲሆን በደቡብ ምዕራብ የአገሪቱ ክፍል ለሚገኙ ከ20 ሚሊዮን በላይ ሰዎች የህክምና አገልግሎት መስጠት የሚችል ነው።
እንዲሁም ለደቡብ ሱዳን እና አጎራባች አገሮች የህክምና አገልግሎት እንዲሰጥ ተደርጎ የተገነባ ነው።
ሆስፒታሉ ከጤና አገልግሎቱ ባሻገር የምርምር፣ የማስተማሪያና የማህበረሰብ አገልግሎቶችን ለመስጠት ያስችላል።
መሪዎቹ የህክምና ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ 300 ተማሪዎችንም ይመርቃሉ ተብሎ ይጠበቃል።