በዩኒቨርሲቲዎች አከባቢ ተከስቶ የነበረው የሰላም መደፍረስ ችግር እየተስተካከለ መሆኑ ተገለጸ

Home Forums Semonegna Stories በዩኒቨርሲቲዎች አከባቢ ተከስቶ የነበረው የሰላም መደፍረስ ችግር እየተስተካከለ መሆኑ ተገለጸ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #9469
    Anonymous
    Inactive

    የትምህርት ተቋማት የእውቀትና የምርምር መሰረት እንጂ የግጭት ማእከላት መሆን የለባቸውም – አቶ ኦባንግ ሜቶ
    —–

    ትምህርት ቤቶች የእውቀትና የምርምር ተቋም እንጂ የግጭት ማእከላት መሆን የለባቸውም ሲሉ የሰብአዊ መብት ተሟጋች አቶ ኦባንግ ሜቶ አመለከቱ።

    የትምህርት ተቋማት የግጭት ማእከላት እንዳይሆኑ ለማድረግ ተማሪዎችንና የትምህርት ማህበረሰቡን በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች ተዘዋውረው ሊያወያዩ መሆኑንም ገልጸዋል።

    የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ መስራችና ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ ከልኡካን ቡድናቸው ጋር በመሆን ላለፉት አምስት ወራት ግጭት በተከሰተባቸው የአገሪቱ አካባቢዎች የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ላይ ያለውን ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

    ”ለመተማመን እንነጋገር” በሚል መሪ ሃሳብ ዛሬ ለኢዜአ መግለጫ የሰጡት አቶ ኦባንግ፤ ትምህርት ቤቶች የእውቀትና የምርምር ተቋም እንጂ የግጭት ማእከላት መሆን እንደሌለባቸው አስገንዝበዋል።

    ልኡካን ቡድኑ በሰብአዊ መብትና ጥሰት ላይ በስፋት ከህዝብና ከመንግስት ጎን በመሆን ለአምስት ወራት እየሰራ መቆየቱን ጠቁመው ተማሪዎች ለፖለቲካ ግብአትና ብሔርን መሰረት አድርገው ለሚቀሰቅሱ አካላት መጠቀሚያ መሆናቸውን እንደታዘቡ ገልጸዋል።

    በጉብኝታቸው ወቅት የተማሪዎች የመማሪያ ግብአት አለመሟላትና ምቹ የመማር ማስተማር ሁኔታ አለመኖር ሌላኛው የግጭት መንስኤ እንደነበርም አብራርተዋል።

    ትምህርት ቤቶች የግጭት ማእከል እንዳይሆኑ ለመከላከል በትምህርት ቤቶች በመዘዋወር ከቀጣዩ የትምህርት መንፈቅ አመት ጀምሮ የማወያየት ስራ እንደሚጀምሩ ገልጸዋል።

    የየአካባቢው ማህበረሰብ፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ተማሪዎችና መምህራን በሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት ላይ ምክክር እንዲያካሂዱ የሚደረግ መሆኑን ጠቁመዋል።

    ከየትምህርት ቤቶቹ አስተዳደር ጋር ውይይቶችን ተከታታይነት ባለው መልኩ የማካሄድ ስራ እንደሚከናወን ገልጸዋል።

    በውጭ አገር ላሉ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችና የፖለቲካ ፓርቲዎች መንግስት ወደ አገራቸው እንዲገቡ ባደረገው ጥሪ መሰረት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ መስራችና ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶና ልኡካን ቡድናቸው ወደ አገራቸው መመለሳቸው የሚታወሰ ነው።

    የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ኦባንግ ሜቶና የስራ ባልደረቦቻቸው የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳይፈጸም በተለያየ መድረክ ላይ በመገኘት ግንዛቤ የማስጨበጥ ተግባር እያከናወኑ እንደሚገኙ ይታወቃል።

    የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.