ዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ የሚያዘጋጀው ዓመታዊ የኪነ ህንጻ አውደ ርዕይ ዘንድሮ ለ13ኛ ጊዜ ይካሔዳል

Home Forums Semonegna Stories ዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ የሚያዘጋጀው ዓመታዊ የኪነ ህንጻ አውደ ርዕይ ዘንድሮ ለ13ኛ ጊዜ ይካሔዳል

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #8116
    Semonegna
    Keymaster

    ዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ ለ13ኛ ጊዜ በሚያካሂደው ዓመታዊ የኪነ ህንጻ አውደ ርዕይ “ኪነ ህንጻና የከተማ ፕላን” በሚል መሪ ሀሳብ ከጥቅምት 8 ቀን እስከ ጥቅምት 11 ቀን 2011 ዓ.ም በብሔራዊ ቲያትር ይካሄዳል።

    አዲስ አበባ (ኢዜአ) – ዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ በየዓመቱ የሚያካሂደው ዓመታዊ የኪነ ህንጻ አውደ ርዕይ ጥቅምት 8 ቀን 2011 ዓ.ም. ይጀመራል።

    ለ13ኛ ጊዜ በሚካሄደው አውደ ርዕዩ “ኪነ ህንጻና የከተማ ፕላን” በሚል መሪ ሀሳብ በብሔራዊ ቲያትር ይካሄዳል።
    የዩኒቨርሲቲው የኪነ ህንጻና የከተማ ፕላን የትምህርት ክፍል ሃላፊ አቶ ቴዎድሮስ ገብረጻዲቅ ለኢዜአ እንደገለጹት አውደ ርዕዩ የትምህርት ክፍሉ ተማሪዎች የሥራ ውጤቶቻቸውን የሚያቀርቡበት ነው።

    አውደ ርዕዩ ተማሪዎች ትምህርታቸውን አጠናቅቀው ወደ ዘርፉ ኢንዱስትሪ ከመቀላቀላቸው በፊት ሥራዎቻቸውን ለኅብረተሰቡ፣ ለመንግስት ተቋማትና ለዘርፉ ባለድርሻ አካላት በማቅረብ ልምድ የሚቀስሙበት እንደሚሆን አቶ ቴዎድሮስ ተናግረዋል። ከዚህ በተጨማሪ ተማሪዎቹ እርስ በእርስ እንዲማማሩም መልካም አጋጣሚ ይፈጥርላቸዋል።

    የተሻለ አቅም ያላቸው ተማሪዎች ወደ ሥራ ዓለም ሲገቡ በዘርፉ ያለውን የሰለጠነ የሰው ሃይል እጥረት ከመቅረፍ አንጻር አስተዋጽዖ እንደሚያበረክቱም ነው አቶ ቴዎድሮስ ያስረዱት።

    አውደ ርዕዩ በየዓመቱ ሲካሄድ በአማካይ እስከ ሁለት ሺህ ሰው እንደሚጎበኘውና ዘንድሮም ከአንድ ሺህ በላይ ተሳታፊዎች እንደሚጎበኙት እንደሚጠበቅ ገልጸዋል።

    ALSO: EVENT: The 9TH ADDISBUILD: International Construction, Steel, Construction Machinery & Infrastructure Exhibition

    በአውደ ርዕዩ የዩኒቨርሲቲው የዘንድሮ የትምህርት ክፍሉ 60 ተማሪዎች የሥራ ፕሮጀክቶቻቸውን እንደሚያቀርቡና የተሻለ ሥራ ያቀረቡ ተማሪዎች የኢትዮጵያ የኪነ ህንጻ ባለሙያዎች ማኅበር (Association of Ethiopian Architects) በሚያዘጋጀው ዓመታዊ ውድድር እንደሚሳተፉም ጠቁመዋል።

    በዚህ አውደ ርዕይ ሌሎች የመንግስትና የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እንደሚሳተፉም ተናግረዋል።

    በብሔራዊ ቲአትር አዳራሽ የሚካሔደው አውደ ርዕይ ከጥቅምት 8 ቀን እስከ ጥቅምት 11 ቀን 2011 ዓ.ም የሚቆይ ይሆናል።

    ዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ ከሚሰጣቸው የትምህርት ዘርፎች አንዱ “ኪነ ህንጻና የከተማ ፕላን” ሲሆን በዚሁ ትምህርት ዘርፍ ተማሪዎችን በመጀመሪያ ዲግሪ (bachelors degree) አስተምሮ ያስመርቃል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)

    ዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.