Home › Forums › Semonegna Stories › ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ በተቀሰቀሰ ረብሻ የአንድ ተማሪ ህይወት አለፈ
- This topic has 3 replies, 2 voices, and was last updated 6 years ago by
Anonymous.
-
AuthorPosts
-
May 28, 2019 at 9:43 am #10968
Anonymous
Inactiveበደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ለአንድ ተማሪ ሞት ምክንያት የሆነውን ድርጊት የከተማው ነዋሪዎች እና የክልሉ መንግስት አወገዙ።
—-ባሕር ዳር (አብመድ) – በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ለአንድ ተማሪ ሞት ምክንያት የሆነውን ድርጊት የከተማው ነዋሪዎች እና የክልሉ መንግስት አወገዙ። የደብረ ማርቆስ ከተማ ነዋሪዎች ስለ ችግሩ እና ስለ ቀጣይ የተማሪዎች ሰላም ተወያይተዋል።
ድርጊቱን ያወገዙት ተወያዮቹ ችግር ፈጣሪዎቹን በማጋለጥ ለጸጥታ አካላት እንደሚሰጡም ቃል ገብተዋል። እስካሁን በድርጊቱ የተጠረጠሩ ተማሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውም ነው በውይይቱ የተገለፀው።
ውይይቱን የተከታተለው ጋሻዬ ጌታሁን እንዳደረሰን መረጃ ሌሎች የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የጸጥታ ስጋት እንዳይደርስባቸው ከጎናቸዉ እንደሚሆኑ ነዋሪዎቹ አረጋግጠዋል።
በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ እሁድ ግንቦት 18/2011 ዓ.ም የአንድ ተማሪ ህይወት ሲያልፋ ሶስት ተማሪዎች ቆስለዉ በህክምና ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል። የችግሩ መንስኤ እስካሁን እንዳልታወቀም ነው ማብራሪያ የተሰጠው።
የክልሉ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤትም የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት እና ሕዝብ በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪ ላይ በደረሰዉ የሕይወት መጥፋት ከልብ ከማዘን ባሻገር ድርጊቱን አጥብቀው እንደሚያወግዙት ገልጿል።
የክልሉ መንግሥት ከሕዝቡና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር ጥቃት አድራሾችን ተከታትሎ ለሕግ እንደሚያቀርብም ነው ያስታወቀው።
ለሟች ቤተሰቦች፣ ለጓደኞቹና ለዩኒቨርሲቲው ማሕበረሰብም መጽናናትን ተመኝቷል።
ምንጭ፦ አብመድ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
May 29, 2019 at 5:26 am #10970Anonymous
Inactiveየዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ አምስተኛ ዓመት ተማሪ ሆሳዕና ከተማ ውስጥ ባልታወቁ ሰዎች ተገደለ
—–ሆሳዕና (ሰሞነኛ ኢትዮጵያ) – በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የ2011 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን መማር-መስተማር ተግባር በሰላም እየተገባደደ ባለበት ወቅት፥ አንድ ያልተጠበቀ አሳዛኝ ክስተት ተከስቷል፡፡ ይኸውም በዩኒቨርሲቲው የምህንድስናና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ የኤሌክትሪከል ምህንድስና ትምህርት ክፍል የ5ኛ ዓመት ተማሪ በሆነው ዓለሙ ባሣ ግንቦት 17 ቀን 2011 ዓ.ም. የደረሰው ድንገተኛ ህልፈተ ሞት ነው፡፡
በተማሪው ላይ የሞት አደጋ የደረሰው ወጣቱ ከዩኒቨርሲቲ ውጪ በሆሳዕና ከተማ ከጓደኞቹ ጋር አምሽቶ ሲመለስ በመንገድ ላይ ባጋጠመው ግጭት መሆኑ ተዉቋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የሆሳዕና እና የሀዲያ ዞን ፖሊስ መምሪያ፣ ዩኒቨርሲቲውና የአካባቢው ማኀበረሰብ ባደረጉት ብርቱ የተቀናጀ ትብብርና ክትትል ሁሉም ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው ይገኛል፡፡ ምርመራው እንደተጠናቀቀም ለፍርድ እንደሚቀርቡ እምነታችን ነው፡፡
በዚህ አጋጣሚ በተማሪ ዓለሙ ባሳ በደረሰው ድንገተኛ ህልፈተ ሞት ምክንያት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን በዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ ስም እየገለጽን፥ ለውድ ቤተሰቦቹ፣ ለወላጅ ዘመዱና ለሚወዱት ጓደኞቹ ከፈጣሪ ዘንድ መጽናናትን እንመኛለን፡፡ እንደዚሁም በዚህ አስቸጋሪና አስደንጋጭ በሆነው ክስተት ወቅት ተማሪዎች ላሳዩት መረጋጋትና በሳል ስሜት፥ የዞንና፣ የሆሳዕና ከተማ ፖሊስ ጽሕፈት ቤቶች ተጠርጣሪዎችን በማሰስና በቁጥጥር ስር በማዋል ለፈጸሙት ፖሊሳዊ ጀብድ፣ የአካባቢውና የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ ስላሳዩት ትኩረትና ትብብር ከልብ የመነጨ ምስጋናን ለመቅረብ እንወዳለን፡፡
ምንጭ፦ የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
June 5, 2019 at 12:03 pm #11066Anonymous
Inactiveአክሱም ዩኒቨርሲቲ ግጭት አንድ ተማሪ ሲሞት በርካቶች ጉዳት ደርሶባቸዋል
—–አክሱም ዩኒቨርሲቲ ውስጥ በተማሪዎች መካከል የተከሰተን ግጭት ተከትሎ አንድ ተማሪ ሲገደል አስር ተማሪዎች ደግሞ መቁሰላቸውን ቢቢሲ አማርኛ ዘግቧል።
የአክሱም ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዚደንት ዶ/ር ኪሮስ ግዑሽ ከግንቦት 19 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ በዩኒቨርሲቲው የብሄር መልክ ያለው ውጥረትና ድንጋይ መወራወር መኖሩን ተናግረዋል።
ውጥረቱ በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ከዚህ ቀደም በተፈጠረው ግጭት አንድ ተማሪ መሞቱ መነሻ ሳይሆን እንደማይቀር ጥርጣሬያቸውን ይናገራሉ። ይሁን እንጂ ዩኒቨርሲቲው የፀጥታ ኃይሎችን በግቢው ውስጥ እንዲገቡ በማድረግ ለማረጋጋት የተለያዩ ጥረቶችን ሲያደርግ ቢቆይም “አልፎ አልፎ የብሔር መልክ ያላቸው ትንንሽ ትንኮሳዎች ነበሩ” ይላሉ ዶ/ር ኪሮስ ።
ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የአክሱም ከፍተኛ ሆስፒታል ሰራተኛ አንድ ተማሪ እንደሞተ ለቢቢሲ አረጋግጠዋል። ባለሙያው ጨምረውም በርካታ ጉዳት የደረሰባቸው ተማሪዎች የህክምና አገልግሎት ለማግኘት ወደ ሆስፒታሉ መምጣታቸውንም ተናግረዋል።
-
AuthorPosts
- You must be logged in to reply to this topic.