ዶ/ር አብይ አህመድ ትዕግስትን መምረጣቸው መልካም ነበር፤ ነገር ግን ትዕግስትም ቢሆን ልክ/ ገደብ ሊኖረው ይገባል።

Home Forums Semonegna Stories ዶ/ር አብይ አህመድ ትዕግስትን መምረጣቸው መልካም ነበር፤ ነገር ግን ትዕግስትም ቢሆን ልክ/ ገደብ ሊኖረው ይገባል።

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #10546
    Anonymous
    Inactive

    ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር ) ልዩነቶችን ለመፍታት ትዕግስትን መምረጣቸው መልካም ሆኖ ሳለ ነገር ግን ትዕግስትም ቢሆን ልክ/ ገደብ ሊኖረው ይገባል። ― አቶ ድልነሳው ጌታነህ ከሎንደን፥ እንግሊዝ

    ዶ/ር አብይ አህመድ ሕዝብን መምራት፣ አገርን ማስተዳደር ተገቢው መንገድ የሃሳብ ልዩነትን በኃይል (ማለትም፥ በማሰር፣ በማሳደድ፣ በመግደል) ሳይሆን ልዩነትን በዕትግስት ተወያይቶ መፍትሄ መሻቱ ጠቀሜታው የላቀ ነው የሚል መርሆ ቢኖራቸውም ትዕግስታቸውን የሚያስጨርሱ እንከኖች ከፊታቸው ተጋርጠው እንደሚገኙ አጠራጣሪ አይደለም።

    በቅርቡ የመረጃ ቲቪ “ዶ/ር አብይን የማትደግፈው ነገር ቢኖር ምንድን ነው?” የሚል ጥያቄ ያለምንም ቅድመ ዝግጅት ወደ ሥራ ወይም ለተለያየ ጉዳይ የሚጓዙ ሰዎችን በድንገት መንገድ ላይ በማስቆም ተመሳሳይ ጥያቄ (pedestrian question) ይጠይቅ ነበር። ለጥያቄው የአብዛኛው ሕዝብ መልስ ‘ትዕግስታቸውን አልደግፍም’ የሚል ነው። ይህንን በአሁኑ ወቅት እኔም እጋራለሁ። ትዕግስት ገደብ ሊኖረው ይገባል። አንዳንድ አካባቢዎች የጦር ቀጠና እየሆኑ ኢ-ሰብዓዊ ድርጊቶች በንፁሃን ዜጎቸ ላይ እየተፈፀመ መቀጠል አይቻልም። ወጣት፣ አዛውንት ታላቅ መስዋዕት ከፍለው ያመጡትን ለውጥ ለመቀልበስ ሕዝብን ከሕዝብ በማጋጨት አባገነናዊ ስርዓት ናፉቂዎች ምኞታቸውን እውን ለማድረግ የሚፈፅሙት ሴራ ለአንዴና ለመጨረሻ በቃ መባል አለበት።

    በትጥቅ በተደራጀ የሽብር ጥቃት ፈፃሚ ላይ በማያዳግም ሁኔታ መንግስታዊ እርምጃ በመውሰድ የሕዝብን ደኅነት መጠበቅና ማስጠበቅ እርምጃውን አባገነናዊ እርምጃ አያደርገውም።

    በእርግጥ የለውጡ ተቀናቃኞች ፍላጎት ልትፈራርስ የነበረችን አገር እንደ አገር እንድትቀጥል እንዲሁም በአይነ ቁራኛ እየተያየ እርስ በርሱ ሊተላለቅ የነበረን ሕዝብ ከእልቂት ዶ/ር አብይ እና ቡድናቸው በሕዝብ ትግልና መስዋዕትነት እገዛ የመጣውን ለውጥ ለመቀልበስ ያልተቆጠበ ሴራ እያካሄዱ ቢሆንም ዘመቻው ሁለት ዓይነት አሰላለፍ አለው። አንደኛው አሰላለፍ የለውጥ አክሻፊዎች በየቦታው ሰርገው በመግባትና ፀብ በመጫር እልቂት፣ ግድያ እንዲፈፀም በማድረግ የዶ/ር አብይ አስተዳደር አገርን በሰላም የመምራት ብቃት እንደሌላቸው በማስመሰል የሕዝብን አመኔታ እንዲያጡ ማድረግ ነው። ሁለተኛው የለውጡ ተቃዋሚዎች ሴራ ብሄርን ከብሄር፣ ሀይማኖትን ከሀይማኖት ጋር እያጋጩ ችግሩ እንዲባባስ በማድረግ ዶ/ር አብይ አማራጭ ሲያጡ መንግስታዊ እርምጃ ሲወስዱ መንበሩን ካመቻቸ በኋላ አባገነን ሆነ ብሎ ለመኮነን ነው። ይህ ደካማ አስተሳሰብ ነው። ስለዚህ መንግሥት የሚያደርገውን ትዕግስት እንደ ድክመት እንዳይወስዱት ተገቢውን አፋጣኝ እርምጃ በተደራጇ የሽብር ጥቃት ፈፃሚ ቡድኖች ላይ መወሰድ አለበት።

    አቶ ድልነሳው ጌታነህ፤ ለንደን፥ እንግሊዝ
    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ተመሳሳይ ታሪኮች

    ዶ/ር አብይ አህመድ


Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.