Home › Forums › Semonegna Stories › ጂንካ ዩኒቨርሲቲ ለ1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የኮምፒዩተር ድጋፍ አደረገ
Tagged: ኬሪያ ኢብራሂም, ጂንካ, ጂንካ ዩኒቨርሲቲ, ገብሬ ይንቲሶ
- This topic has 2 replies, 2 voices, and was last updated 6 years, 3 months ago by
Anonymous.
-
AuthorPosts
-
February 4, 2019 at 6:56 pm #9487
Anonymous
Inactiveጂንካ ዩኒቨርሲቲ ግጭት ላለባቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አርአያ ነው — አፈ ጉባዔ ኬሪያ ኢብራሂም
—–በጂንካ ዩኒቨርሲቲ ያለው ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት ሌሎች ግጭት ላለባቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አርአያ እንደሆነ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ገለፁ።
በዞኑ ያለው ሰላምና መረጋጋት በተምሳሌትነት የሚጠቀስ መሆኑን አፈ ጉባዔ ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂም ተናግረዋል።
በደቡብ ብሔር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን ውስጥ የሚገኙ 16 ብሄረሰቦች የተሳተፉበት የባህል ፌስቲቫል ጥር 27 ቀን 2011 ዓ.ም. በጂንካ ዩኒቨርሲቲ ተካሄዷል።
ፌስቲቫሉ በዞኑ ለመጀመሪያ ጊዜ የተዘጋጀ ሲሆን “ባህላዊ እሴቶች ለአብሮነትና ለልማት” በሚል መሪ ቃል ነው የተካሄደው።
አፈ ጉባዔዋ ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂም በፌስቲቫሉ መክፈቻ ላይ እንደገለጹት፤ በጂንካ ዩኒቨርሲቲ ያለው ሰላምና መረጋጋት ለመማር ማስተማር ስራ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከተ በመሆኑ ለሌሎች ግጭት ላለባቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አርአያ ነው።
በርካታ ብሄረሰቦች የሚኖሩበት ዞኑ በአካባቢው ያለው ሰላምና መረጋጋት በአገር አቀፍ ደረጃ በተምሳሌትነት የሚጠቀስ ነውም ብለዋል።
በዩኒቨርሲቲው የተካሄደው ፌስቲቫል በዞኑ ያለውን ቋንቋ፣ ባህልና ታሪክ ለማስተዋወቅ የሚረዳ መልካም ተግባር እንደሆነም ተናግረዋል።
እንዲሁም የዞኑን ባህልና እሴቶች ለሌሎች አካላት ለማሳወቅ የጀመራቸው የጥናትና ምርምር ስራዎች ወሳኝ መሆናቸውን አንስተዋል።
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ እንዳሉት፤ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ አካባቢያዊ ጥናትና ምርምሮች ወሳኝ ሚና ያላቸው በመሆኑ አገር በቀል እውቀትን ለተማሪዎችና ለኀብረተሰቡ ለማሳወቅ ጂንካ ዩኒቨርሲቲ የጀመረው ጥናትና ምርምር ያለው ፋይዳ የጎላ ነው።
ዩኒቨርስቲው በሳይንስና ቴክኖሎጂ በመደገፍ በተለያዩ የትምህርት ክፍሎች ለሚማሩ ተማሪዎች በኮምፒዩተር አማካይነት የሚሰጠውን መጽሕፍ አቅርቦት አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አሳስበዋል።
ዩኒቨርሲቲው በዞኑ ባህልና እሴቶች ላይ ለሚካሄዱ ጥናትና ምርምሮች የልህቀት ማዕከል በመሆን ማገልገል እንዳለበት ፕሮፌሰር አፈወርቅ ጠቁመዋል።
የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ገብሬ ይምቲሶ በበኩላቸው ከዚህ በፊት በደቡብ ኦሞ ዞን የሚገኙ ብሄረሰቦች የሚያስተዋውቅ ፌስቲቫል ባለመካሄዱ የብሔረሰቦቹን ባህልና እሴት በማስተዋወቅ ረገድ የሚፈለገው ያህል አልተሰራም ብለዋል።
በዚህም ምክንያት ዩኒቨርሲቲው የሚጠበቅበትን ማህረሰባዊ አገልግሎት ለኀብረተሰቡ አለመስጠቱን ተናግረዋል።
ዘንድሮ የባህል ፌስቲቫሉ ለመጀመሪያ ጊዜ መዘጋጀቱ 16ቱ ብሔረሰቦች እርስ በርስ እንዲተዋወቁና የባህል ልውውጥ እንዲያደርጉ ምቹ አጋጣሚ የፈጠረ በመሆኑ ወደፊት ቀጣይነት ባለው መልኩ እንደሚካሄድም አመልክተዋል።
የፌስቲቫሉ ዓላማ በዞኑ የሚገኙ ብሔረሰቦችን ከማቀራረብ ባሻገር ከተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የመጡ የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የ16ቱን ብሔረሰቦች ቋንቋ፣ ባህልና እሴት እንዲያውቁ ማድረግ እንደሆነም ገልጸዋል።
እንዲሁም በዞኑ ግጭቶች ሳይከሰቱ የአገር አንድነትና ሰላም ለማስጠበቅ ወሳኝ ሚና እንዳለውም ፕሮፌሰር ገብሬ አስረድተዋል።
በፌስቲቫሉ የዞኑ ብሔረሰቦች የምግብ፣ የሙዚቃና የዕደ-ጥበብ ስራዎች ለእይታ የቀረቡ ሲሆን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ተገኝተዋል።
የደቡብ ኦሞ ዞን በባህል ብዝሃነት የሚታወቅና በበርካታ የውጭ አገር ዜጎች የሚጎበኝ አካባቢ ነው።
February 8, 2019 at 5:36 pm #9594Anonymous
Inactiveየጂንካ ዩኒቨርስቲ ባህላዊ እሴቶች ጉልተው እንዲወጡ የሚያደርገው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተገለጸ
—–የጂንካ ዩኒቨርስቲ ባህላዊ እሴቶች ጎልተው እንዲወጡ የሚያድርገውን ጥረት አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ጅንካ ዩኒቨርስቲ ባዘጋጀው ባህላዊ ፌስቲቫል ላይ የተገኙ ተጋባዥ እንግዶችና ታዳሚዎች ገለጹ ።
የጅንካ ዩኒቨርስቲ “ባህላዊ ዕሴቶቻችን ለአንድነታችንና ለልማታችን” በሚል መሪ ቃል በጅንካ ዩኒቨርሲቲ ደማቅ ባህላዊ ፌስቲቫል አካሂዷል፡፡
በፌስቲቫሉ የተገኙ የተለያዩ ተጋባዥ እንግዶችና ታዳሚዎች ለዋልታ እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው እያደረገ ያለውን ባህላዊ እሴቶች የማስተዋወቅ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል እንደለበት አንስተዋል፡፡ዩኒቨርሲቲው በበኩሉ የአከባቢውን ማህበረሰብ በጥናትና ምርምር በቴክኖሎጂ በማገዝ ባህላዊ እሴቶች ይበልጥ ጎልተው የሚወጡበትን የተጠናከረ ሥራ እያከናወነ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
የሳይንስና የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ደኤታ ፕሮፌስር አፈወርቅ ካሱ በበኩላቸው ፌስቲቫል በዞኑና አከባቢዋ የሚኖሩ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦችን ይበልጥ ከማጠናክር አንፃር ጉልህ ድርሻ ይኖረዋል ብለዋል፤ በተጨማሪም የሳይንስና የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ለአከባቢው ልዩ ትኩረት በመሥጠት እንደሚሠራ ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ አክለው ገልፀዋል፡፡
-
AuthorPosts
- You must be logged in to reply to this topic.