ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ለፌደራል የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ሹመት ሰጡ
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ለፌደራል መንግስት የስራ ኃላፊዎች ሹመት ሰጡ።
በዚሁ መሠረት፤
1. አቶ ብናልፍ አንዱዓለም ― በሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ዋና አስተባባሪ
2. አቶ መለስ ዓለሙ ― በሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ምክትል ዋና አስተባባሪ
3. አቶ ተመስገን ጥሩነህ ― የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደህንነት ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር
4. አቶ ደሴ ዳልኬ ― በሚኒስትር ማዕረግ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የግብርና እና የመስኖ አማካሪ በመሆን ከጥቅምት 7 ቀን 2011 ዓ.ም ጀምሮ ተሹመዋል።
የተሰጠው ሹመት የትምህርት ዝግጅትና የፖለቲካ አመራር ብቃትን ከግምት ያስገባ መሆኑን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።