የመቱ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብና ተመራቂ ተማሪዎች የተራቆቱ ቦታዎች ላይ ችግኝ ተከሉ
—–
የመቱ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብና ተመራቂ ተማሪዎች የተራቆቱ ቦታዎች ላይ ችግኝ ተክለዋል።
የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብና ተመራቂ ተማሪዎች ችግኞቹን የተከሉት በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን የአካባቢ ጥበቃ እንቅስቃሴ ምክንያት በማድረግ ነው።
ይህ የችግኝ ተከላ የተካሄደው በመቱ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ግቢ ውስጥ ሲሆን፣ በዚህ ችግኝ ተከላ ፕሮግራም ላይ የዩኒቨርሲተው የበላይ አመራሮች፣ መምህራን፣ የአስተዳደር ሰራተኞችና የ2011 ዓ.ም. የዩኒቨርሲቲው ተመራቂ ተማሪዎች ናቸው።
በተያያዘ ዜና በመቱ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ድጋፍ ስድስት ለሚሆኑ አባወራዎች የመኖሪያ ቤት እተሰራላቸው መሆኑንም ለማወቅ ተችሏል።
ቤቱ የሚሰራላቸውም በሚኖሩበት ቀበሌ በኩል የኢኮኖሚ ችግር ያለባቸውና ምንም ገቢ የሌላቸው መሆናቸው የተረጋገጠ ነው ተብሏል።
ምንጭ:- EBC