የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከጣሊያን መንግስት የላብራቶሪ መሣሪያዎችን በእርዳታ አገኘ

Home Forums Semonegna Stories የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከጣሊያን መንግስት የላብራቶሪ መሣሪያዎችን በእርዳታ አገኘ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #10617
    Semonegna
    Keymaster

    የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ላብራቶሪ ኃላፊ እንደተናገሩት፥ የላብራቶሪ መሣሪያዎቹ በአገሪቱ የመጀመሪያ መሆናቸውን እና በጣም ጠቃሚ የሆኑ የአሚኖ አሲድ መጠኖችን ከምግብና ከደም ናሙና ላይ ለመለየት የሚያግዙ እንደሆኑ ገልጸዋል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከጣሊያን መንግስት ግምታቸው 2 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር የሆኑ የላብራቶሪ እቃዎች በእርዳታ አገኘ።

    የጣሊያን መንግስት በተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት (UNIDO) አማካኝነት የለገሰው በተለያዩ ምግቦች ውስጥ የሚገኘውን የአሚኖ አሲድ መጠን የሚለኩ የአሚኖ አሲድ እና የክሩድ ፋት አናላይዘር (amino acid and crude fat analyzer) የተሰኙ የላብራቶሪ መሣሪያዎች ሲሆኑ ግምታቸው 2 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር ይሆናል።

    ርክከቡ በኢንስቲትዩቱ ግቢ በተከናወነበት ወቅት የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዳይሬክተር ዶ/ር ጌታቸው ቶሌራ እንዳሉት፥ በልገሳ የተገኙት የላብራቶሪ እቃዎች ኢንስቲትዩቱ ለሚያከናውናቸው ጥራት ያላቸው የምርምር ሥራዎች ወሳኝ ጥቅም እንዳላቸው ጠቅሰው፤ የኢንስቲትዩቱን ማገዝ አገሪቱ የምግብ እጥረትን ለመቀነስ የምታደርገውን ጥረት ማገዝ ነው ብለዋል።

    በተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት (UNIDO) ከሃያ ዓመት በፊት ጀምሮ በተለያዩ ሥራዎች እገዛ ሲያደርግ መቆየቱን ገልጸው፥ የጣሊያን መንግስት በተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት በኩል ላደረገው እርዳታ ምስጋና አቅርበዋል።

    ● SEMONEGNA on Social Media: FacebookTwitterInstagramPinterest | Video | Forum

    የተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት ተወካይና የቀጣናው ዳይሬክተር ሚስ ኢውሬሊያ ፓትሬዝያ ካላብሮ ካላብሮ (Aurelia Patrizia Calabrò) እንዳሉት፥ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከአጋር ድርጅቱ የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን (EFDA) ጋር በመተባበር ለሚያከናውነውና በሞሪንጋ የምግብ ጠቀሜታና ይዘት ምርምር ላይ ጠቃሚ ሥራዎችን ለመሥራት የሚያግዝ መሆኑን አመልክተዋል።

    የጣሊያን የልማትና ትብብር ኤጀንሲ (Italian Agency for Development Cooperation/ AICS) ተወካይ ፌቨን ጌታቸው በበኩላቸው ኢትዮጵያ ለጣሊያን ቅድሚያ ከሚሰጣቸው አገራት አንዷ መሆ ኗን ገልጸው፥ በግብርና፣ በጤና እና በኢንዱስትሪ መስኮች የተለያዩ የትብብር ሥራዎች እየተሠሩ መሆኑን አመልክተዋል። የዛሬው እገዛ በሞሪንጋ እየተሠራ ላለው ፕሮጀክት ሁለተኛው ዙር ድጋፍ መሆኑን ገልጸው ወደፊትም ትብብሩ እንደሚቀጥል አብራርተዋል።

    ከእቃዎቹ ርክክብ በኋላ የምግብ ሳይንስ እና ሥነ ምግብ ምርምር ላብራቶሪ ጉብኝት ተደርጓል። በጉብኝቱ ወቅት የኢንስቱትዩቱ ላብራቶሪ ኃላፊ አቶ መሰረት ወልደዮሐንስ በሰጡት ገለፃ መሠረት፥ የላብራቶሪ እቃዎቹ በአገሪቱ የመጀመሪያ መሆናቸውን እና በጣም ጠቃሚ የሆኑ የአሚኖ አሲድ መጠኖችን ከምግብና ከደም ናሙና ላይ ለመለየት የሚያግዙ እንደሆኑ ገልጸዋል።

    የላራቶሪ እቃዎቹ እንደ አገር በጣም ጠቃሚ መሆናቸውን አውስተው፥ ለግልም ይሁን ለመንግስት ተቋማት እንዲሁም ለዩኒቨርሲቲዎች በርካታ ድጋፍ የሚያደርጉ መሆኑን አቶ መሰረት አመልክተዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የላብራቶሪ-መሣሪያዎች

     


Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.