NEAEA: የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ውጤት ይፋ ሆነ

Home Forums Semonegna Stories NEAEA: የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ውጤት ይፋ ሆነ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #11670
    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– አገር አቀፍ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች ኤጀንሲ (NEAEA) የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ የፈተና ውጤትን ነሐሴ 7 ቀን 2011 ዓ.ም. ይፋ አደረገ።

    የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ አርአያ ገብረእግዚአብሔር እንደገለጹት፥ ወጤታቸን በመጠባበቅ ላይ ያሉ ተፈታኝ ተማሪዎች ውጤታቸውን በኤጀንሲው ድረ-ገጽ app.neaea.gov.et በመግባት ማወቅ ይችላሉ።

    የመፈተኛ ቁጥራቸውን አድሚሸን (Admission) በሚለው ሳጥንውስጥ በማስገባት ውጤታቸውን መመልከት ይችላሉ ብለዋል አቶ አርአያ።

    በሞባይል አጭር የፅሁፍ መለእክት (SMS) 8181 id በማለት የሚያዩበት አማራጭ መመቻቸቱንም ገልጸዋል።

    • የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ውጤት ለማወቅ እዚህ ጋር ይጫኑ app.neaea.gov.et

    በ2011 ዓ.ም. የትምህረት ዘመን 319 ሺህ 264 ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሄራዊ ፈተና የወሰዱ ሲሆን 59 ተማሪዎች ከ600 መቶ በላይ ውጤት አስመዝግበዋል።

    ዘንድሮ 645 ከፍተኛ ውጤት ሆኖ መመዝገቡም ታውቋል።

    የዘንድሮው ውጤት ካለፉት ዓመት ጋር ሲነፃፀር መካከለኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠ ሲሆን ከ50 በመቶ በላይ ያመጡ ተማሪዎች 48 ነጥብ 59 በመቶ ናቸው።

    በፈተና ሥነ ስርዓት ጥሰት ምክንያት በቀረበባቸው ሪፖርት የ68 ተማሪዎች ውጤት መሰረዙንም አቶ አርአያ ገልጸዋል።

    ከአራት ክልሎች (አማራ፣ ኦሮሚያ፣ ደቡብና ቤኒሻንጉል) የ864 ተማሪዎች ውጤት ለተጨማሪ ማጣራት እንዲያዝ ተደርጓል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ውጤት


Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.