ሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘው በቁጥጥር ስር ውለው ወደ አዲስ አበባ እየመጡ ነው
****************************************************
የቀድሞ የብረታ ብረት እና ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘው በቁጥጥር ስር ዋሉ።
ከኮርፖሬሽኑ አሰራር ጋር በተያያዘ በወንጀል ተጠርጣሪ የሆኑት የሜቴክ ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘው በምዕራባዊ ትግራይ በኩል ባታር በተሰኘው አካባቢ ነው በህብረተሰቡ እና በመከላከያ ኃይል ትብብር የተያዙት።
በአሁኑ ሰዓትም ወደ አዲስ አበባ ተይዘው እየመጡ ነው።
በትናንትናው እለት የጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ከፍተኛ የገንዘብ ምዝበራ በመፈፀማቸው የተጠረጠሩ 27 ከፍተኛ የሜቴክ አመራሮች እና ባለሙያዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ማስታወቁን ሪፖርተራችን አብዲ ከማል ከስፍራው ዘግቧል።