ቤልካሽ ኢትዮጵያ ሄሎማርኬት እና ሄሎሾፕ የተሰኙ ሁለት የኤሌክትሮኒክስ መገበያያ ገፆችን ሊያስጀምር ነው

Home Forums Semonegna Stories ቤልካሽ ኢትዮጵያ ሄሎማርኬት እና ሄሎሾፕ የተሰኙ ሁለት የኤሌክትሮኒክስ መገበያያ ገፆችን ሊያስጀምር ነው

Viewing 2 posts - 1 through 2 (of 2 total)
  • Author
    Posts
  • #9188
    Semonegna
    Keymaster

    ቤልካሽ ኢትዮጵያ የሚያስጀምራቸው ሄሎማርኬት እና ሄሎሾፕ የተሰኙ ሁለት የኤሌክትሮኒክስ መገበያያ ገፆች በኢትዮጵያ ውስጥ እና ከኢትዮጵያ ውጪ ለሚገኙ ተገልጋዮች ኢንተርኔት አማካኝነት ግብይት መፈም የሚችሉባቸው ናቸው።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ቤልካሽ ኢትዮጵያ ተጠቃሚዎች በበይነመረብ (ኢንተርኔት) አማካኝነት ግብይት መፈም የሚችሉባቸው ሁለት የኤሌክትሮኒክስ መገበያያ ገፆችን በቅርቡ እንደሚያስጀምር አስታወቀ።

    ሄሎማርኬት (Hellomarket) የተሰኘው ገፅ በዋነኛነት በኢትዮጵያ ውስጥ ለሚገኙ ተገልጋዮቹ ብቻ ካሉበት ቦታ ሆነው ቁሳቁሶችን የሚሸምቱበት አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን በበይነመረብ አማካኝነት የግዥ ትዕዛዝ እና ክፍያ የተፈፀመባቸው ቁሳቁሶቹን ወደ ደምበኞች ለማጓጓዝም ከ ዓለምአቀፉ ዲኤችኤል (DHL) ጋር ስምምነት ተፈራርሟል።

    The dispute between RIDE Taxi, Ethiopian-kind of Uber, and Addis Ababa Transport Authority continues

    ተቋሙ በመጀመርያው ምዕራፍ ወደ 2,500 የሚጠጉ ሴት ኢትዮጵያውያን በባለቤትነት በሚያስተዳድሩዋቸው የተለያዩ ድርጅቶች የተመረቱ ምርቶችን ለማሻሻጥ ቅድመ ዝግጅቱን አጠናቋል።

    በተመሳሰይ ቤልካሽ ከኢትዮጵያ ውጭ ሆነው የኤሌክትሮኒክ ግብይት መፈፀም ለሚፈልጉ ደንበኞቹ አገልግሎት የሚሰጥ ሄሎሾፕ (Helloshop) የተሰኘ ሌላ ገፅ ያዘጋጀ ሲሆን የክፍያ ስርዓቱም በማስተር ካርድ አማካኝነት አንደሚከወን ለማወቅ ተችሏል።

    Ethiopia – blueMoon Incubator and Addis Garage co-working space for startups in Ethiopia

    ቤልካሽ ኢትዮጵያ መቀመጫውን ኔዘርላንድ ባደረገው እና ቤልካሽ ቴክኖሎጂ ሶሉሽን (Belcash Technology Solutions) የተሰኘ በኤሌክትሮኒክ ክፍያ ቴክኖሎጂ ዘርፍ ላይ የተሰማራ ድርጅት እህት ኩባንያ ሲሆን እ.ኤ.አ ከ2011 ጀምሮ በኢትዮጵያ በተለይም በሞባይል ክፍያ እና የገንዘብ ማስተላለፍ ዘርፎች ላይ የተለያዩ ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ከኩባንያው ድረገፅ የተገኘ መረጃ ያመላክታል።

    የኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ሥርዓት በተገቢው አለመስፋፋት እና በዚህ ዘርፍ ላይ ግልፅ የሆኑ ፖሊሲዎችን አለመኖራቸው በኢትዮጵያ መሰል የኤሌክተሮኒክ ግብይት ተቋማት እንዳይስፋፉ እንቅፋት መሆኑን ባለሞያተኞች ይገልፃሉ።

    ከዚህ ዜና ጋር በተመሳሳይ የቻይናው ግዙፉ የኤሌክትሮኒክስ መገበያያ (e-commerce) አሊባባ ኢትዮጵያ ውስጥ ገብቶ ለመሥራት ፍላጎት እንዳለውና ከኢትዮጵያ ባላስልጣናት ጋር (የቀድሞ የኢፌዴሪ ፕሬዝደንት ዶ/ር ሙላቱ ተሾመን ጨምሮ) መወያየቱን የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዘግቦ ነበር

    ምንጭ፦ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ / አዲስ ፎርቹን
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    ቤልካሽ ኢትዮጵያ


    #9873
    Anonymous
    Inactive

    ተረፈ-ምርትን በመጠቀም ማምረት የሚያስችል ፕሮጀክት ይፋ ሆነ
    —–

    ቆሻሻና አነስተኛ ውሃን በመጠቀም የአሳና ዶሮ ምግብ፣ ማዳበሪያ፣ አትክልትና ፍራፍሬ በቀላሉ ማምረት የሚያስችል የተቀናጀ የግብርና ዘዴ የምርምር ፕሮጀክት ተጠናቆ ወደ ስራ ሊገባ ነው፡፡

    በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ድጋፍ የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ለ3 ዓመታት ባደረገው ምርምር አርሶ አደሩ በአነስተኛ የጓሮ መሬትና ውስን የጉድጓድ ውሃ በማዘጋጀት ዘርፈ ብዙ ምርት መሰብሰብ የሚቻልበት ፕሮጀክት ተጠናቆ ለትግበራ ተዘጋጅቷል፡፡

    ምርምሩ በተደረገበት በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታና ግድም ወረዳ ይምሎ ቀበሌ የተደራጁ ወጣቶችን በማሳተፍ ውጤታማ የአሳ፣ የዶሮ፣ የማዳበሪያ፣ የሙዝና የሸንኮራ አገዳ ምርቶችን በአነስተኛ መሬት ላይ ማሳካት ተችሏል፡፡

    በፕሮጀክቱ ምረቃ ላይ የተገኙት የአ.ፌ.ዴ.ሪ. ኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ጌታሁን መኩሪያ ይህን ፕሮጀክት ትልቅ የሚያደርገው ወጣቶች በአነስተኛ ወጪ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሊጠቀሙበት የሚችሉበት መሆኑ ነው ብለዋል፡፡

    ሚኒስትሩ የፕሮጀክቱን የአተገባበር ሰነድ ለዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ለአቶ ተፈራ ወንድማገኘሁ አስረክበዋል፡፡

    ምንጭ፦ ዋልታ ሚዲያ

Viewing 2 posts - 1 through 2 (of 2 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.