ብርሃን ባንክ በ2011 ዓ.ም የበጀት ዓመት ስኬታማ አፈፃፀም አስመዘገበ

Home Forums Semonegna Stories ብርሃን ባንክ በ2011 ዓ.ም የበጀት ዓመት ስኬታማ አፈፃፀም አስመዘገበ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #8533
    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አባባ (ብርሃን ባንክ)–የብርሃን ባንክ ባለአክስዮኖች ዘጠነኛ መደበኛ ጉባኤ ቅዳሜ ኅዳር 1 ቀን 2011 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ ተካሂዷል። የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሊቀመንበር አቶ ጉማቸው ኩሴ ይፋ ባደረጉት ሪፖርት እ.ኤ.አ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ባንኩ በዋና ዋና የአፈፃፀም መለኪያዎች የላቀ የሥራ አፈጻጸም በማስመዝገብ እንደ ከዚህ በፊቱ ሁሉ ጠንካራ እና ተፎካካሪ ባንክ መሆኑን በድጋሚ አስመስክሯል ሲሉ ገልፀዋል።

    በተገባደደው የበጀት ዓመት ብርሃን ባንክ ከግብር በፊት ብር 410.9 ሚሊዮን ትርፍ ማስመዘገብ መቻሉን ገልፀዋል። በዚሁ በጀት ዓመት ባንኩ ተጨማሪ አክስዮኖችን በመሸጥ የተከፈለ ካፒታሉን ወደ ብር 1.7 ቢሊዮን ያሳደገ ሲሆን ከአለፈው የበጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ20 በመቶ የሆነ ከፍተኛ ጭማሪ ማሳየቱን ገልፀዋል። በተመሳሳይ መልኩም ባንኩ በበጀት ዓመቱ የባለአሲዮኖቹን ቁጥር ወደ 14,879 አድርሷል። ይህም ባንኩን በኢትዮጵያ ባንክ ኢዱስትሪ ውስጥ ከግል ባኮች በባለአክስዮኞ ቁጥር ቀዳሚ ባንክ አድርጎታል። በመሆኑም ባንኩ ሠፊ የሕዝብ መሠረት /Public Base/ ያለው የሕዝብ ባንክ መሆኑን ያረጋግጣል ብለዋል። በሌላ በኩል ሊቀመንበሩ በበጀት ዓመቱ ባንኩ አጠቃላይ ሀብቱ አምና ከነበረው 10 ቢሊዮን ወደ ብር 14 ቢሊዮን ብር በማድረስ የሀብት መሠረቱን እያሰፋ እና ራሱን ለቀጣይ እድገት ይልጥ በተሻለ ሁኔታ እያደራጀ መሆኑን ገልፀዋል። ከዚህም በተጨማሪ ባንኩ የነበረውን የደንበኞች አገልግሎት በላቀ መልኩ የተቀላጠፈ ለማድረግ እንዲሁም አዳዲስ የባንክ አገልግሎት አማራጮችን በመቅረፅ ደንበኞችን ይበልጥ ለማገልገል የሚረዳ ደረጃውን የጠበቀ የመረጃ ማዕከል ገንብቶ እ.ኤ.አ 2018/19 የበጀት ዓመት ለአገልግሎት ዝግጁ አድርጓል።

    ብርሃን ባንክ በበጀት ዓመቱ ካስመዘገበው የላቀ የሥራ አፈፃፀም ውጤት ባሻገር ከእሴቶቹ መካከል አንዱ የሆነውን ማኅበራዊ ኃላፊነትን ከመወጣት አንፃር በተለያዩ ምክንያቶች ከመኖሪያ ቀዬዎቻቸው ለተፈናቀሉ የህብተሰብ አካላት ድጋፍ እንዲደረግ ከሚመለከታቸው የክልል መንግስታት በቀረበለት ጥያቄ መሠረት የብር ሁለት ሚሊዮን ድጋፍ አድርጓል።

    Berhan Bank, one of the private banks in Ethiopia, registers more than 410 million birr before tax

    የብርሃን ባንክ ፕሬዘዳንት የሆኑት አቶ አብርሃም አላሮ በበኩላቸው የተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ከፍተኛ የገበያ ውድድር እና በባንኩ ክፍለ ኢኮኖሚ በርካታ ተግዳሮቶች የነበሩበት ዓመት መሆኑን ጠቅሰው በበጀት ዓመቱ ባንኩ በሁሉም የሥራ ዘርፍ ያስመዘገበው የሥራ አፈጻጸም ውጤት እጅግ አመርቂ መሆኑን ገልጸዋል። ባንኩ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ጠቅላላ ተቀማጭ ሂሳቡን ወደ ብር 11 ቢሊዮን ሲያሳድግ ይህም ከአለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከነበረው ጋር ሲነጻጸር የ42 በመቶ የሆነ ከፍተኛ ዕድገት ማሳየቱን አስታወቀው፥ በተመሳሳይ መልኩም ባንኩ ለተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች የሰጠው የብድር ክምችት በበጀት ዓመቱ ከፍተኛ እድገት አስመዝግቦ ብር 7 ቢሊዮን መድረሱን ይህም ከዓምናው ጋር ሲነጻጸር የ33 በመቶ የሆነ ከፍተኛ ብልጫ እንዳለው ገልጸዋል። ባንኩ በኢኮኖሚው በተለያዩ ዘርፎች እያፈሰሰ ያለው የብድር መጠን በየጊዜው እየጨመረ የመጣ መሆኑን ያስረዱት ፕሬዝዳንቱ ባንኩ በአገር ልማት እና እድገት ላይ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ መሆኑን ተናረግዋል።

    ፕሬዝዳንቱ አያይዘውም ብርሃን ባንክ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 21 አዳዲስ ቅርንጫፎችን በመክፈት በመላ አገሪቱ ያሉትን የቅርንጫፎች ቁጥር ወደ 182 የደረሰ ሲሆን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የባንኩ ደንበኞች ቁጥርም ከአለፈው ዓመት ከነበረው የ43 በመቶ የሆነ ከፍተኛ ዕድገት በማስመዝገብ 523,705 መድረሱን ገልጸዋል።

    ብርሃን ባንክ እያስመዘገበ የመጣውን ከፍተኛ የሆነ ሁለንተናዊ ዕድገት ተከትሎ 372 ተጨማሪ ሠራተኞችን በበጀት ዓመቱ የቀጠረ ሲሆን ይህም ባንኩ ያለውን አጠቃላይ የሰው ሃብት ቁጥር ወደ 3,237 ማሳደጉን ፕሬዘዳንቱ ጠቁመዋል። አያይዘውም ባንኩ ለሰው ሃብት ከሚሰጠው ልዩ ትኩረት የተነሳ በበጀት ዓመቱ የባንኩን የተቀላጠፈ የደንበኞች አገልግሎት የሚያሳልጥ እንዲሁም የባንኩን ግልፅነት እና ተዓማኒነት የተሞላበት እሴቶቹን ሊያስጠብቁ እና ደንበኞችን በልሕቀት ማገልግል ይቻል ዘንድ የተለያዩ ስልጠናዎች እንዲወስዱ ተደርጓል ብለዋል። አቶ አብርሃም በቀጣዩ የበጀት ዓመት ባንኩ እሰካሁን የመጣበትን የስኬት ጉዞ ሊያስቀጠል የሚችል ስትራቴጂ ነድፎ በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኝ በመሆኑ ባንኩ የበለጠ ውጤት እንደሚያመጣ ጽኑ እምነት እንዳላቸው ገልጸው፥ የባንኩ ዳይሬክተሮች ቦርድ፣ የበላይ አመራሩ እና መላው ሠራተኛ እንዲሁም በዋናነት ደግሞ የባንኩ ደንበኞች እና ባለድርሻ አካላት እስካሁን ላበረከቱት የላቀ አስተዋፅዖ ምስጋናቸውን አቅርበው ባንኩ ከዚህም በኋላ በላቀ እና በተቀላጠፈ የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደቱ ደንበኞቹን በትጋት እና በታማኝነት እንደሚያገለግል ያላቸውን ፅኑ እምነት ገልፀዋል።

    ምንጭ፦ ብርሃን ባንክ (berhanbanksc.com)

    ብርሃን ባንክ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.