ግልጽ ደብዳቤ ለኢትዮጵያ ሕዝብ – በአቶ ነአምን ዘለቀ ― አቶ ነአምን ዘለቀ ራሳቸውን ከአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ አገለሉ

Home Forums Semonegna Stories ግልጽ ደብዳቤ ለኢትዮጵያ ሕዝብ – በአቶ ነአምን ዘለቀ ― አቶ ነአምን ዘለቀ ራሳቸውን ከአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ አገለሉ

Viewing 2 posts - 1 through 2 (of 2 total)
  • Author
    Posts
  • #10323
    Semonegna
    Keymaster

    “የሠራዊቱ ሁኔታ ከፍተኛ የህሊና መረበሽ ውስጥ ከቶኛል” አቶ ነአምን ዘለቀ
    —–

    ላለፉት 26 ዓመታት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ተሳትፎ ሲያደርጉ የቆዩት የአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ ከፍተኛ አመራርና ሥራ አስፈጻሚ አባል አቶ ነአምን ዘለቀ ከፓርቲ መልቀቃቸውን ተከትሎ ከቢቢሲ ጋር ቆይታ አድርገዋል።

    ቢቢሲ፡ የአርበኞች ግንቦት 7 የሠራዊ አባላት አሁን ያሉበት ሁኔታ ትንሽ ያስጨነቀዎት ይመስላል። ግን ደግሞ ለመልቀቅ ከወሰኑ ቆይተዋል፤ እርስዎም በጽሑፍዎ እንደጠቀሱት። እና ዝም ብሎ ከመውጣት፣ መልቀቅዎን ከአንድ ጉዳይ ጋ ሆን ብለው ለማያያዝ የሞከሩ ይመስላል።

    አቶ ነአምን፡ (ዘለግ ካለ ሳቅ በኋላ) ምን እላለሁ እንግዲህ። አንተ የመሰልህን (ማሰብ ትችላለህ). . .። መጀመሪያ (ከጽሑፌ) አንተ ይሄን ብቻ ነጥለህ ለምን እንዳወጣኽው አላወቅኩም። እዚያ ላይ ሠራዊቱን በሚመለከት የተደረገው ጥረት በዝርዝር ተቀምጧል። እስካሁን ድረስ እነኚህ የሠራዊት አባላት በከፍተኛ ችግር ላይ ነው ያሉት፤ ላለፉት ሰባት ወራት።

    መንግሥት የእነርሱን ጉዳይ በተደረገው ስምምነት መሠረት (ማለትም) ቶሎ በሁለትና በሦስት ወር ውስጥ መልሰው ይቋቋማሉ፣ ድጎማ ይሰጣቸዋል አለ፤ የጀርመን መንግሥት ገንዘብ ለመስጠት ቃል ገባ፤ ነገር ግን በጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽሕፈት ቤት የተቋቋመው ቢሮ ምንም አቅም ስላልነበረው እስካሁን ድረስ ሲጓተት ቆይቶ አሁን ገና ወደ ኮሚሽን ጉዳዩ ተመርቶ ያው ኮሚሽኑ ኃላፊነት ተሰጥቶት በብሔራዊ አደጋ መከላከል ኮሚሽን በኩል የእነርሱ ጉዳይ እንዲካሄድ ነው እየተደረገ ያለው።

    ቢቢሲ፡ ለመሆኑ የሠራዊቱን አባላት በአካል አግኝተዋቸዋል?

    ሙሉውን ቢቢሲ አማርኛ ላይ ያንብቡ

    #11173
    Anonymous
    Inactive

    የፌደራል የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን የቀድሞ አርበኞች ግንቦት 7 ሠራዊትን ሊያቋቁም ነው
    —–

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የቀድሞ የአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ ሠራዊት አባላትን የፌደራል የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ለማቋቋም ቃል መግባቱን ሠራዊቱን መልሶ የማቋቋም አስተባባሪ ወ/ሮ እማዋይሽ ዘውዱ ለአዲስ አድማስ ጋዜጣ አስታውቀዋል።

    ሠራዊቱን መልሶ የማቋቋም ኮሚቴው በጉዳዩ ላይ ከአደጋ መከላከልና ስጋት አመራር ኮሚሽን ጋር መወያየቱን የገለፁት ወ/ሮ እማዋይሽ፥ መንግስት ተጣርቶ የቀረበለትን የሰው ኃይል መልሶ ለማቋቋም ቃል ገብቷል ብለዋል።

    በአሁን ወቅት በየቦታው ያሉ የሠራዊቱን አባላት ተሳትፎና ማንነት የተመለከቱ መረጃዎችን ኮሚቴው እያጣራ መሆኑን የገለፁት ወ/ሮ እማዋይሽ፥ በአጠቃላይ መደራጀትና መቋቋም የሚያስፈልጋቸው የሠራዊቱ አባላት ከ5ሺህ በላይ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

    የሠራዊት አባላቱ በአራት ምድብ የሚከፈሉ መሆኑን የገለፁት አስተባባሪዋ፥ በመንግስት ታስረው የነበሩ፣ ከኤርትራ የመጡ፣ በዘመቻ ሲንቀሳቀሱ የነበሩና በዘመቻ ወቅት አባታቸውን ያጡ ልጆች መሆናቸውን አስረድተዋል።

    በአሁኑ ወቅት ባህር ዳር ላይ 1900 (አንድ ሺ ዘጠኝ መቶ ያህል) የሠራዊቱ አባላት ለመቋቋም ተመዝግበው ይገኛሉ ያሉት አስተባባሪዋ፥ በቀጣይ አባላቱ በፈለጉት የሥራ መስክ እንዲሠማሩ መንግስት ሙሉ ኃላፊነቱን ወስዶ ለማቋቋም ቃል መግባቱን አስታውቀዋል።

    ምንጭ፦ አዲስ አድማስ ጋዜጣ

Viewing 2 posts - 1 through 2 (of 2 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.