አዋሽ ባንክ ዓመታዊ ያልተጣራ ትርፉ ወደ ብር 2 ቢሊዮን ተጠጋ

Home Forums Semonegna Stories አዋሽ ባንክ ዓመታዊ ያልተጣራ ትርፉ ወደ ብር 2 ቢሊዮን ተጠጋ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #8740
    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ – አዋሽ ባንክ 23ኛውን የባለአክሲዮኖች ዓመታዊ መደበኛና 15ኛውን የባለአክሲዮኖች ድንገተኛ ጉባዔ ኅዳር 15 ቀን 2011 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ሂልተን ተካሂዷል።

    በጉባዔው ላይ የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት እና ባለአክሲዮኖች የተገኙ ሲሆን፥ በስብሰባው ላይ የባንኩ የዳሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ታቦር ዋሚ የባንኩን ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት በዝርዝር አቅርበዋል።

    የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢው በሪፖርታቸው እንደጠቀሱት ያሳለፍነው በጀት ዓመት ለአገራችንም ሆነ ለግል ባንኮች እጅግ ፈታኝ ጊዜ የነበረ ቢሆንም ባንኩ እነዚህን ፈታኝ ተግዳሮቶችን በመቋቋምና ወደ መልካም አጋጣሚ በመለወጥ በሁሉም የሥራ ዘርፎች አመርቂ ውጤት ማስመዘገቡን ገልጸዋል። የተመዘገበው ውጤት እ.ኤ.አ ለ2017/18 ሒሳብ ዓመት በአስር ዓመት ስትራቴጂ ውስጥ ከተቀመጠው  ግብ አኳያም ሲታይ እጅግ የላቀ ውጤት መሆኑን የባንኩ የቦርድ ሰብሳቢ አብራርተዋል።

    አዋሽ ባንክ እ.ኤ.አ በ2017/18 የሒሳብ ዓመት ባንኩን ካጋጠሙት ተግዳሮቶች መካከል ዋና ዋናዎቹ የዋጋ ግሽበት፣ የውጭ ምንዛሪ እጥረት፣ የብድር ጣሪያ መኖር እና ከሚገኘው የውጭ ምንዛሪ 30 በመቶውን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገቢ እንዲያደርጉ መደረጉ በጉልህ ይጠቀሳሉ።

    አዋሽ ባንክ ይህንን ሁሉ ፈተናዎች ተቋቁሞ በሁሉም የሥራ ዘርፎች አመርቂ ውጤቶችን በማስመዘገብ ከሀገርቷ የግል ባንኮች መካከል የቀዳሚነት ሥፍራውን እንደያዘ መቀጠሉን ገልፀዋል።

    Wegagen Bank grosses more than 1 billion birr, which is 49% up from previous fiscal year

    እ.ኤ.አ በ2017/18 የሒሳብ ዓመት የባንኩ ያልተጣራ ትርፍ ብር 1.96 ቢሊዮን ሲሆን ይህም ትርፍ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የብር 650 ሚሊዮን ወይም የ49 በመቶ ዕድገት አሷይቷል። ይህም ትርፍ ለአዋሽ ባንክም ሆነ በግል ባንኮች ታሪክ ውስጥ ከፍተኛው ትርፍ እንደሆነ ታውቋል።

    ለባንክ ሥራ እንደ ደም ስር የሚታየውን የተቀማጭ ሒሳብን በማሰባሰብ ረገድም ጠቅላላ የባንኩ ተቀማጭ ሒሳብ ኤልሲ ማርጅንን ጨምሮ የብር 13 ቢሊዮን ወይም የ40 በመቶ ዕድገት በማሳየት እ.ኤ.አ ሰኔ 2018 መጨረሻ ላይ ብር 45.9 ቢሊዮን ደርሷል።

    አዋሽ ባንክ ለተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች የሰጠው የብድር መጠን ብር 31.3 ቢሊዮን የደረሰ ሲሆን ይህም ብድር ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት አንጻር ሲተያይ የብር 8.7 ቢሊዮን ወይም የ38 በመቶ ጭማሪ አስመዝግቧል።

    እ.ኤ.አ በ2017/18 የሒሳብ ዓመት የባንኩ ጠቅላላ ገቢ አምና ከነበረበት ብር 3.76 ቢሊዮን የብር 1.7 ቢሊዮን ወይም የ44 በመቶ ዕድገት በማስመዝገብ ብር 5.4 ቢሊዮን ሆኗል።

    Berhan Bank, one of the private banks in Ethiopia, registers more than 410 million birr before tax

    በሌላ መልኩ የባንኩ ጠቅላላ ወጪም የብር 1 ቢሊዮን ወይም የ41 በመቶ ዕድገት በማስመዝገብ ብር 3.4 ቢሊዮን ሁኗል። ለወጪዎቹ ማደግ ዓብይት ምክንያቶች የወለድ ምጣኔ መጨመር፣ የሠራተኞች ደመወዝና ጥቅማ ጥቅም ዕድገት፣ የዕቃዎች ዋጋ መናር እና የባንኩ የሥራ ዘርፎች መስፋፋት እንደሆነ ታውቋል።

    ባንኩ ለደንበኞቹ የተቀላጠፈና ዘመናዊ የባንክ አገልግሎት ከመስጠት አኳያም የተለያዩ ሥራዎችን ያከናወነ ሲሆን አገልግሎቶቹንም በዘመናዊ የክፍያ ማሽኖች ማለትም በኤቲኤም እና ፖስ ማሽኖች እንዲሁም በሞባይል ባንኪንግ እና በኢንቴርኔት ባንኪንግ አገልግሎቶች በመታገዝ ለደንበኞቹ በቀን የ24 ሰዓት እና በሳምንት የ7 ቀናት የባንክ አገልግሎቶችን በመስጠት ላይ ነው። ለወደፊቱም ዘመናዊ የሆነ የግንኙነት ማዕከል (Contact Center) እና የደንበኞች ግንኙነት አመራር (Customer Relationship Management – CRM) አገልግሎቶችን በሥራ ላይ ለማዋል በእንቅስቃሴ ላይ ይገኛል። ደንበኞች ሳይጉላሉ በአቅራቢያቸው የባንክ አገልግሎት እንዲያገኙ ለማስቻልም እ.ኤ.አ በ2017/18 ሒሳብ ዓመት ሃምሳ አዳዲስ ቅርንጫፎችን በመክፈት የቅርንጫፎቹን ብዛት 366 አድርሷል።

    ባንኩ ባለፉት ዓመታት ባከናወናቸው አመርቂ ውጤቶች የተነሳም የባንኩ ጠቅላላ ሀብት የዛሬ 3 ዓመት ከነበረበት ብር 25 ቢሊዮን ከእጥፍ በላይ ጭማሪ በማሳየት ብር 55 ቢሊዮን ሁኗል። እንደዚሁም የባንኩ ጠቅላላ ካፒታል መጠባበቂያዎችን ጨምሮ ብር 6.5 ቢሊዮን የደረሰ ሲሆን የባንኩ የተከፈለ ካፒታል ደግሞ ብር 2.9 ቢሊዮን ሆኖ ተመዝግቧል።

    የባንኩ ባለአክሲዮኖች በሚቀጥሉት ሶስት ዓመታት ውስጥ የባንኩን የተከፈለ ካፒታል ብር 6 ቢሊዮን ለማድረስ በተሰማሙት መሠረት በሚቀጥሉ ዓመታት የባንኩ የተከፈለ ካፒታል ከፍተኛ ጭማሪ እንደሚያሳይ ይጠበቃል።

    አዋሽ ባንክ ከተመሠረተበት ጊዜ አንስቶ ማኅበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ከፍተኛ እንቅስቃሴ ሲያደርግ የቆየ ሲሆን በዘንድሮ ዓመትም በተመሳሳይ መልኩ ለበጐ ሥራዎች የሚውል የብር 30,000,000.00 (ሰላሳ ሚሊዮን) እርዳታ እንዲሰጥ የዳይሬክተሮች ቦርድ ወስኗል።

    ምንጭ፦ አዋሽ ባንክ

    አዋሽ ባንክ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.