የዱባይ አቡዳቢው ኤግል ሒልስ በአዲስ አበባ ለገሀር የተቀናጀ የመኖሪያ፣ አገልግሎት መስጫና የመዝናኛ ስፍራ ሥራውን ጀመረ

Home Forums Semonegna Stories የዱባይ አቡዳቢው ኤግል ሒልስ በአዲስ አበባ ለገሀር የተቀናጀ የመኖሪያ፣ አገልግሎት መስጫና የመዝናኛ ስፍራ ሥራውን ጀመረ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #8584
    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ኤግል ሒልስ)–በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የበላይ ጠባቂነት በአዲስ አበባ ለገሀር አከባቢ ሥራዉን ለመጀመር ዝግጅቱን ያጠናቀቀዉ የዱባይ አቡዳቢው ኤግል ሒልስ (Eagle Hills) በአዲስ አበባ ለገሀር የተቀናጀ የመኖሪያ፣ አገልግሎት መስጫና የመዝናኛ ስፍራ ልማት ሥራውን በይፋ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶ/ር አብይ አህመድ በተገኙበት ኅዳር 10 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀመረ።

    ይህ በ360,000 ሜትርካሬ መሬት ላይ የሚያርፈዉ የለገሀር የተቀናጀ የልማት ኘሮጀክት የአዲስአበባን መሀል ከተማ ወካይ ሆኖ በዉስጡ ከ4000 በላይ መኖሪያ ቤቶች፣ የመዝናኛ ስፋራዎች፣ ግዙፍ የንግድ ማዕከላት፣ መጋቢና ዋና መንገዶች እና ሌሎች ዘመናዊ አገልግሎት መስጫ ስፍራዎች ይኖሩታል ።

    ከቦሌ ዓለም አቀፍ አዉሮፕላን ማረፊያ በቅርብ ርቀት የሚሠራው ይህ ሁለገብ መንደር እንዲሁም ባለ አምስት ኮከብ ሆቴሎች፣ አረንጓዴ መዝናኛ ስፍራዎች፣ ምቹና ሰፋፊ የእግረኛ መንገዶች እና የመኪና ማቆሚያ ስፍራዎች በበቂ ሁኔታ በዉስጡ እንዳካተተም ማስተር ኘላኑ ያመለክታል።

    ኘሮጀክቱ በኢትዮጵያ መንግስት እና በዱባዩ ኤግል ሒልስ ትብብር የሚሠራ ሲሆን ነዋሪዎች አሁን ባሉበት ቦታ መኖርያ ቤት ተገንብቶላቸዉ በዘላቂነት በሚያዉቁት ቀዬ እንዲኖሩም ይደረጋል።

    ስለ ኘሮጀክቱ ፋይዳ ሲናገሩ የኤግል ሒልስ ሊቀ መንበረ ሞሀመድ አልባረ፥ “እንደ አንዷ የአፍሪካ ዕንቁዎች ኢትዮጵያ በባህል፣ ታሪክ እና የተፈጥሮ ዉበት የበለፀገች ነች፤ ስለዚህ የእኛ ፍላጎት እንዲህ ዉብ ከሆኑት የሀገሪቱ ትሩፋቶች አንዱ የሆነውን በአዲስ አበባ የለገሀር አካባቢን አልምቶ ዓለም እንዲያውቀው እና ሰዎች ከተለያየ የዓለም ክፍል ኢትዮጵያን መዳረሻቸው አድርገው ሁሉ ነገር የተሟላለት መንደር መኖር፣ መዝናናት እና መገብየት እንዲችሉ ማድረግም ጭምር ነው። ከዚህ በተጨማሪም ይህ ኘሮጀክት ለአከባቢዉ ነዋሪዎችም ሆነ ለሌሎች የሥራ ዕድል በመፍጠር የሀገሪቱን ኢኮኖሚ የበለጠ የማነቃቃት ሰፊ ሚና ይኖረዋል።” ብለው የዚህን ዘመናዊ ኘሮጀክት ሰፊ ጥቅም አስረድተዋል።

    Addis Ababa City Administration to transfer more than 17 thousand 40/60 condominiums houses

    ለገሀር ከፈረንሳይኛ ቋንቋ የተወሰደ ሲሆን ትርጓሜዉም የባቡር ጣቢያ ማለት ነው ይኸውም የባቡር ጣቢያ በአዲስ አበባ ዋነኛ ጣቢያ በመሆን ለዘመናት አገልግሏል። በአዉሮፓውያን የዘመን ቀመር በ1917 የተጠናቀቀው ጣብያዉ ለከተማዋ ብሎም ለኢትዮጵያ ዋነኛው የባቡር ትራንስፖርት ማዕከልም ነበር።

    አዲሱ የለገሀር ፕሮጀክትም በዉስጡ በጥልቅ የኪነ ህንፃ ጥበብ የሚሠሩ ለቢሮ አገልግሎት የሚዉሉ ህንፃዎች ሲኖሩት በቅርብ ርቀትም ባለ አራት እና አምስት ኮከብ ሆቴሎች ይገኛሉ።

    የአቡዳቢዉ ኤግል ሒልስ ትልልቅ የተቀናጀ የመኖሪያ መንደሮች ግንባታ ድርጅት ሲሆን በተለያዩ ሀገሮች ብዙ ቁጥር ያላቸው መንደሮችን ገንብቷል። ይህ ኩባንያ ተመሳሳይ መንደሮችን በዓለም ዙሪያ ለመገንባት አቅዶ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል።

    ኤግል ሒልስ በኢትዮጵያ (በአዲስ አበባ ለገሀር የመኖሪያ ቤቶች ፕሮጀክት)

    ኤግል ሒልስ በኢትዮጵያ የግል የመኖሪያ ቤቶች አልሚ ድርጅት ሲሆን ትልልቅ እሴት ያላቸው ግንባታዎች ላይ ተሳትፎ በማድረግ የሃገሪቱን የኢኮኖሚ እድገት በማፋጠን ረገድ የግሉን ድርሻ አበርክቶ ለማኅበራዊ እና ኢኮኖሚ እድገት አስተዋጽኦ ያበረክታል።

    ይህ በዉበቱ እና ዘመናዊነቱ የላቀ እንደሚሆን የተነገረለት መንደር በዘርፉ ከፍተኛ እውቀት አና ልምድ ባላቸው ባለሙያዎች የሚሠራ ከመሆኑም ባሻገር የአካባቢዉን አረንገጓዴነትና እና ለመኖሪያ ምቹነት ባገናዘበ መልኩ ይገነባል።

    በ360,000 ሜትር ካሬ ቦታ ላይ የሚያርፈው ፕሮጀክቱ የአነስተኛ ንግድ ስፍራዎችንም በዉስጡ የያዘ ሲሆን ዙሪያውም በመናፈሻ ፓርክ የተከለለ ነው ።

    ፕሮጀክቱ ሰፋፊ የሥራ ዕድሎችን ከመፍጠሩም ባሻገር በሀገሪቱ ያሉትን የንግድ እንቅስቃሴዎች በእጅጉ ይደግፋል። የለገሀር የመኖሪያ ቤቶች ፕሮጀክት ድረ ገጽ

    ምንጭ፦ ኤግል ሒልስ

    ለገሀር የመኖሪያ ቤቶች ፕሮጀክት

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.