ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ እና ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተጠናከረ የመጣው የማኅበረሰብ አገልግሎቱ

Home Forums Semonegna Stories ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ እና ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተጠናከረ የመጣው የማኅበረሰብ አገልግሎቱ

Viewing 2 posts - 1 through 2 (of 2 total)
  • Author
    Posts
  • #9477
    Anonymous
    Inactive

    የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ዱራሜ ካምፓስ ለአቅመ-ደካሞች ቤት ሠራ!

    የሣይንስና ከፍተኛ ት/ት ሚኒስተር ባስቀመጠው “አንድ ቀን ለሕዝቤ” መርሃ-ግብር መሰረት ፣ ዛሬ በ25/05/2011 ዓ.ም. “የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የዱራሜ ካምፓስ ለሕዝቤ” በሚል መሪ ቃል ለሁለት የደሃ ደሃ ቤተሠቦች ማለትም ለአቶ አማን መሐመድ ከቀርጭቾ ቀበሌ እና ለአቶ አባቶ መኬቦ ከ ጠዛ አጋራ ቤት መልሶ የመገንባት ስራ በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የዱራሜ ካምፓስ በጎ ፈቃደኛ አስተዳደር ሠራተኞች፣ መምህራን ፣ ተማሪዎችና ሌሎች የግቢው ማህበረሰብ አባላት ተሰርቷል።

    ከቤቱ በተጨማሪ ፣ለእያንዳንዳቸው አባወራዎች ስፓንጅ ፍራሽና ብርድልብስ ተበርክቶላቸዋል።

    በመጨረሻም፣የቤቱ ባለቤቶችና በቦታው የነበሩ ጎረቤቶቻቸው አስተያየታቸውን ተጠይቀዋል። የተሰማቸውን ሲገልፁም÷ ” ይህ በጎ ተግባር መቀጠል አለበት፣ አቅመ-ደካሞችን ከመርዳቱም በላይ ማህበረሰቡ ስለ ተቋሙ መልካም አመለካከት ከመቼውም በላቀ ሁኔታ እንዲኖረው ያደርጋል፤ ተቋሙንም እንደ ዐይኑ ብሌን እንዲጠብቅ የባለቤትነት ስሜት ያሳድርበታል” ብለዋል።

    ምንጭ፦ ከዩኒቨርሲቲው ፌስቡክ ገጽ

    #9602
    Anonymous
    Inactive

    ዋቸሞ ዩኒቨረሲቲ ዘሬ ቅዳሜ የካቲት 02-2011 ዓ/ም በዩኒቨርሲቲው ታሪክ የመጀመሪያ የሆኑትን የህክምና ዶክተሮች አሰመረቀ፡፡
    —–

    ክብርት ፕሮፌሰር ሂሩት ወ/ማርያም የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የሳይነስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፣ፕሮፌሰር ላጲሶ ጌ. ድሌቦ ፣የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የስራ አመራር ቦርድ አባላት፣ የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የሴኔት አባላት፣ የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ስራ ሃላፊዎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ፣ የዩኒቨርሲቲው ማህበረስብ እና ውድ የተመራቂ ቤተሰቦች በተገኙበት በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ታሪክ የመጀማሪያ የሆኑትን የህክምና ዶክተሬት ተማሪዎችን በደማው ሁኔታ አስመረቀ፡፡

    በህ/ጤ/ሳይ/ኮሌጅ፤
    – በቅድመ-ምረቀ በ3 ት/ት መሽኮች በህክምና ዶክተሬት ወንድ 26 ሴት 8 (ድምር 24)፣ በህ/ሰብ ጤና ወንድ 37 ሴት 15 (ድምር 52)፣ በሰርጂካል ነርስ ስፔሻሊቲ ወንድ 11 ሴት 7 (ድምር 18)፣ እና በድህረ ምረቃ በህብረተሰብ ጤና ወንድ 2 ሴት 1 (ድምር 3) በአጠቃላይ ወንድ 76 ሴት 31 (በድምሩ 96) ተማሪዎች፣
    – በግ/ሳ/ኮሌጅ በቅድመ ምረቃ በክረምት መረሃ ግብር በ2 ትምህርት መስኮች በተፈጥሮ ሀብት አያያዝና በዕጽዋት ሳይንስ ወንድ85 ሴት 8 (በድምሩ 93) ተማሪዎች፣
    – ቢዚነስ እና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ በድህረ ምረቃ በአካውንቲንግና ፋናንስ በመደበኛ መርሃ ግብ 4 ተማሪዎች፣

    በአጠቃላይ በውድመ ምረቃ እና በድህረ ምረቃ በመደበኛ እና በክረምት መርሃ ግብር ሰለጠኑ ወንድ 165 ሴት 39 በድምሩ 204 ተማሪዎችን አሰመርቋል፡፡

    በምረቃውም በሁላቱም ጾታ አመረቂ ውቴት የመጡ ተማሪዎች የተሸለሙ ሲሆን ከ ሴቶች ዶ/ር ጋዲሴ ሰስፋ ከወንዶች ዶ/ር ዋክሹም ፌጠነ የሰርትፍኬት እና የብር ሽልማት ተሸለመዋል፡፡ ዶ/ር ዋክሹም ፌጠነ በአጠቀላይ የሜዳሊያ ተሸላሚ ነው፡፡

    ምንጭ፦ ከዩኒቨርሲቲው ፌስቡክ ገጽ

Viewing 2 posts - 1 through 2 (of 2 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.