ዘመን ባንክ የትርፍ መጠኑን ወደ 86 በመቶ አሳደገ

Home Forums Semonegna Stories ዘመን ባንክ የትርፍ መጠኑን ወደ 86 በመቶ አሳደገ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #13152
    Anonymous
    Inactive

    ዘመን ባንክ ባለፈው የበጀት ዓመት ለተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች የሰጠው ብድር 7.6 ቢሊዮን ብር የደረሰ ሲሆን፥ ይህም ከቀዳሚው ዓመት የ50.7 በመቶ እድገት የተመዘገበበት እንደሆነ ባንኩ ጨምሮ ገልጿል።

    አዲስ አበባ (አዲስ አድማስ) – ዘመን ባንክ ባለፈው የበጀት ዓመት የትርፍ መጠኑን ወደ 86 በመቶ ማሳደጉን አስታወቀ። ባንኩ በ2011 ዓ.ም. የበጀት ዓመት ከሰጣቸው የአገር ውስጥና የውጭ አገር የባንክ አገልግሎት ዘርፎች ከ1.5 ቢሊዮን ብር በላይ ያገኘ ሲሆን ሊያገኝ ካቀደው የ1 ቢ. 492 ሚሊዮን ብር ገቢ አንጻር፣ የ6 በመቶ ብልጫ እና ከ2010 ዓ.ም. አንፃር የ39 በመቶ ብልጫ ወይም የ447 ሚሊዮን ብር እድገት ማሳየቱን ባንኩ በሰጠው መግለጫ አስታውቋል።

    ለትርፉ ማደግ እንደ ምክንያት ከተቆጠሩት መካከል የወጪ ቅነሳ፣ የብድር አቅርቦትና በአገልግሎት ዘርፍ የተመዘገበው መልካም አፈፃፀም ዋና ዋናዎቹ እንደሆኑ የጠቀሰው ባንኩ፥ በበጀት ዓመቱ 1 ቢሊዮን 84 ሚሊዮን ብር ወጪ ይኖረዋል ተብሎ የነበረ ቢሆንም በዓመቱ ውስጥ በተሠሩ የወጪ ቅነሳ መርሃ ግብሮች አጠቃላይ ወጪው 947 ሚሊዮን ብር እንዲሆን በማድረግ ትርፋማነቱን ለማሻሻል  እንደረዳውም ተገልጿል።

    ዘመን ባንክ በበጀት ዓመቱ ከታክስ በፊት 635.9 ሚሊዮን ያልተጣራ ትርፍ ያስመዘገበ ሲሆን፥ ይህም ከቀዳሚው 2010 ዓ.ም የ86 በመቶ ወይም የ293.5 ሚሊዮን ብር ብልጫ ማሳየቱንና ከዕቅዱ ደግሞ የ55 በመቶ ብልጫ ያለው አፈፃፀም ሆኖ መመዝገቡን አስታውቋል።

    ባለፈው የበጀት ዓመት ለተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች የሰጠው ብድር 7.6 ቢሊዮን ብር የደረሰ ሲሆን፥ ይህም ከቀዳሚው ዓመት የ50.7 በመቶ እድገት የተመዘገበበት እንደሆነ ባንኩ ጨምሮ ገልጿል። ባንኩ በበጀት ዓመቱ ካገኘው ከ1.5 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ውስጥ 1 ቢሊዮን  15 ሚሊዮን ከወለድ፣ ከዓለም አቀፍ ባንክና ከሌሎች አገልግሎቶች ያገኘው እንደሆነም አስታውቋል።

    የዘመን ባንክ አጠቃላይ ሀብት እ.ኤ.አ በ2019 ዓ.ም. መጨረሻ 14.7 ቢሊዮን የደረሰ ሲሆን ይህም ከቀዳሚው ዓመት በ18 በመቶ ወይም በ2.2 ቢሊዮን ብር ጭማሪ ማሳየቱ የተገለፀ ሲሆን፥ በ2010 ዓ.ም ከነበረው የ10.2 ቢሊዮን ብር ተቀማጭ ገንዘብ፣ በ2011 ዓ.ም. ወደ 11.6 ቢሊዮን ብር ማደጉም ታውቋል።

    በሌላ በኩል ባንኩ በ2011 ዓ.ም. የበጀት ዓመት የደንበኞቹን የባንክ አገልግሎት ፍላጎት ለማሟላትና በቅርበት ለማገልገል ባደረገው ጥረት፣ የቅርጫፎቹን ብዛት ኪዮስኮችን ጨምሮ ወደ 43 ያሳደገ ሲሆን በተያዘው አዲስ የበጀት ዓመትም ይህንኑ የቅርንጫፍ ቁጥር የማሳደግ ሥራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል።

     SEMONEGNA on Social Media: FacebookTwitterInstagramPinterest | Video | Forum

    ምንጭ፦ አዲስ አድማስ/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ዘመን ባንክ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.