አገራችን ዘመን ተሸጋሪ የሆኑ ቅርሶቿን ጠብቃ ለትውልድ ለማቆየት የአርክቴክቱና የአንጂነሩ ሚና ወሳኝ መሆኑ ተጠቆመ

Home Forums Semonegna Stories አገራችን ዘመን ተሸጋሪ የሆኑ ቅርሶቿን ጠብቃ ለትውልድ ለማቆየት የአርክቴክቱና የአንጂነሩ ሚና ወሳኝ መሆኑ ተጠቆመ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #10880
    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር በአገራችን በሁሉም አቅጣጫ የተጠናከረ የመዳረሻ ልማት፣ የቅርስ ጥገናና እንክብካቤ ሥራዎችን በተቀናጀ መልኩ ለማከናውን እንዲያስችል በሙያው የተሠማሩ ከመሀንዲሶች እና የሥነ-ሕንፃ ባለሙያዎች ጋር ግንቦት 6 ቀን 2011 ዓ.ም. አዲስ አበባ ውስጥ በጌት ፋም ሆቴል ምክክር ተካሄደ።

    በመክፈቻው ላይ ተገኝተው የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት ክብርት ዶ/ር ሂሩት ካሳው የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ሲሆኑ፣ በመክፈቻ ንግ ግራቸውም የመርሐ ግብሩን ዓላማ “በኢትዮጵያ ሥነ-ሕንፃ ዲዛይን ጥበብ ከጥንት አባቶቻችን ዘመን ጀምሮ የነበረን ብሎም ዓለምን እስከ ዛሬ ድረስ የሚያስደምሙ ሕንፃ ጥበቦች አሁንም አሉን። እንደሚታወቀው በዓለም የሥነ-ሕንፃ ጥበብ ታሪክ የባቢሎናዊያን፣ የግሪኮች፣ የሮማውያን፣ የባይዛንታይን፣ የመካከለኛ ዘመን፣ የዘመናዊው (modern) ሥነ-ሕንፃ ብለን ማየት የምንችል ይሆናል። በኢትዮጵያ ሥነ-ሕንፃ ታሪክ ቅድመ አክሱም (የዳዓማት)፣ የአክሱማውያን ስልጣኔ፣ የዛጉዌ ስርወመንግስት ሥልጣኔ፣ የሰሎሞኒክ፣ የጎንደሮች ዘመን ሥልጣኔን ማውሳት ይቻላል። አንድ ሥነ-ሕንፃ ሲታነፅ በዋናነት የዚያን ዘመን ማኅበራዊ አደረጃጀት እና የተደረሰበትን አጠቃላይ የዕድገት ደረጃ ከማሳየቱም በላይ በየዘመኑ ያሉ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ሁኔታዎችን ፍንትው አድርጎ የማሳየት ጥበብ አለው” ብለዋል።

    ክብርት ሚኒስትሯ አክለውም “በሀገራችን የአርክቴክቱና የኢንጂነሩ የጥበብ አሻራዎች ለዚህ ላለንበት ዓለም እያበረክቱት ያለው ሙያዊ ድጋፍ ቀላል ግምት የሚሰጠው አለመሆኑንና በሀገር በቀል የሥነ-ሕንፃ ጥበባችን ዓለም ወደኛ እንዲመለከተን አስተዋጽኦቸው ከምንም በላይ የሚደነቅ ነው። አርክቴክቱና አንጂነሩ በሙያው የማኅበረሰቡን እምነት፣ ታሪክና ማንነት በሥነ-ሕንፃ ጥበብ ውስጥ በማኖር ማሳየት በመቻሉ ዘመን ተሸጋሪ አደርጎታል። ስለሆነም በዛሬው ዕለት የምናካሂደው ውይይት በመዳረሻ ልማት፣ በቅርስ ጥገናና እንክብካቤ እንዲሁም በኢትዮጵያ እየተገነቡ ያሉ ሕንፃዎች ኢትዮጵያዊ መገለጫነት የሌላቸው በመሆኑ እንዴት አብረን እንሥራ ብለን ስንነሳ በመጀመሪያ ከአርክቴክቶችና አንጂነሮች ጋር በመሆን የጋራ ቅርሶቻችንን የማወቅ፣ የመለየትና የማስተዋወቅ ሥራ፣ የቅርስ ጥገናና እንክብካቤ ሥራ በራስ ዕውቀት እንዲሆን በማድረግ በቅርስ ጥበቃ ኢትዮጵያዊ መልክ እንዲኖራቸው፣ የዕውቀት ሽግግርና ሕዝብ ሕህዝብ የማገናኘት ሥራ በአንድ ላይ ተሰባስበን የምንሠራበትና የጋራ አቅጣጫ የምንይዝበት ነው በማለት መድረኩን ክፍት አድርገዋል።

    SEMONEGNA on Social Media: FacebookTwitterInstagramPinterest | Video | Forum

    በመቀጠል ሦስት ርዕሰ ጉዳዮች የመወያያ ጥናታዊ ጽሑፎች የቀረቡ ሲሆን፣ እነዚህም በአገራችንን ቅርሶች ነባራዊ ሁኔታ ዳሰሳዊ ጥናት በአቶ ኃይሉ ዘለቀ ከቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን፣ በዘመናዊ የቅርስ አመራርና አስተዳደር ወቅታዊ ቁመና በረ/ፕሮፌሰር ሀሰን ሰዒድ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና በተጠናከረ የመዳረሻ ልማት በአቶ ቴዎድሮስ ደርበው ከባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር የቱሪስት አገልግሎቶች ብቃት የማረጋገጥ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ናቸው።

    ጥናታዊ ጽሑፎችን ያቀረቡ ባለሙያዎች ተንተን ባለመልኩ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ የቅርስ አስተዳደር ሁኔታ ምን ይመስል እንደነበረ ከታሪካዊ ዳራው ጀምሮ የሀብቱ ጥበቃና እንክብካቤ የመንግስትና የሕዝብ ፍላጎት ላይ የተመሠረቱ መሆኑ አመላክተዋል። የሀብቱ ጥበቃና እንክብካቤ በግለሰብ፣ በማኅበረሰብ እና የባለሙያው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑን በተያዘላቸው ጊዜ ቅደም ተከተል ገለፃ አድርገዋል።

    በውይይቱም እያንዳንዱ ባለሙያው በቅርስ ጥገናና እንክብካቤ ዙሪያ በዕውቀትም፣ በሀሳብም በጉልበትም መደግፍ እንዲችል በተደራጀ መልኩ አቅም እንዲፈጠርለት የተጠየቀ ሲሆን በመዳረሻ ልማት (በከተማ ግንባታ) እየታዩ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ በውይይቱ የተሳተፉ መሀንዲሶች እና የሥነ-ሕንፃ ባለሙያዎች እንደአገር የሚሠሩ የሥነ-ሕንፃ ሥራዎችን የዲዛይን ውድድር ውስጥ መሳተፍ እንዲችሉ ዕውቅና በመስጠት አገራዊ ቅርጽ እንዲይዙ ማድረግ ወሳኝ መሆኑ፣ በመዳረሻ ልማት ዘርፍ የሚሠማሩ ዜጎች የኢትዮጵያዊ ማንነት መገለጫ ያላቸው ሕንፃዎች እንዲኖረን በሕንፃ ግንባታ መስክ ትኩረት የሚሰጥ አስገዳጅ ቅድመ ትኩረታዊ ስልት (strategy) እንደአገር ሊኖረን ይገባል።

    ምንጭ፦ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር


Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.