የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የስምንት መንገዶች ግንባታ ሥራ የኮንትራቶችን ከተለያዩ ተቋራጮች ጋር ተፈራረመ

Home Forums Semonegna Stories የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የስምንት መንገዶች ግንባታ ሥራ የኮንትራቶችን ከተለያዩ ተቋራጮች ጋር ተፈራረመ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #8236
    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ኢመባ) – የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን (ኢመባ) 600 ኪ.ሜ ርዝመት የሚሸፍኑ የስምንት መንገዶች ግንባታ ሥራ የኮንትራት ስምምነት ከ13.8 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ከተለያዩ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀገር ተቋራጮች ጋር ተፈራረመ።

    የሁለተኛው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን አካል የሆኑና 600 ኪ.ሜ ርዝመት የሚሸፍኑ የስምንት መንገዶች የመንገድ ግንባታ ሥራዎች የኮንትራት ስምምነት ከብር 13.8 ቢሊዮን በላይ በሆነ ወጪ ጥቅምት 14 ቀን 2011 ዓ.ም በሒልተን ሆቴል ተፈራርሟል። የመንገድ ፕሮጀክቶቹ ዝርዝር መረጃ የሚከተለውን ይመስላል።

    1. ጣርማበር–መለያ–ሰፈሜዳ መገንጠያ 1 መለያ–ሞላሌ–መገንጠያ 2 ሞላሌ–ወገሬ መንገድ (ርዝመት 118.87 ኪ.ሜ)

    o የገንዘቡ መጠን፦ 1,906,200,296.75 ብር
    o የግንባታ ጊዜ ሚፈጀው፦ 36 ወራት
    o ኮንትራክተር፦ መከላከያ ኮንስትራክሽን

    2. ጂማ–አጋሮ–ዴዴሳ ወንዝ መንገድ (ርዝመት 79.07 ኪ.ሜ)

    o የገንዘቡ መጠን፦ 1,306,509,305.57 ብር
    o የግንባታ ጊዜ ሚፈጀው፦ 42 ወራት
    o ኮንትራክተር፦ ቻይና ሬል ዌይ 21ኛ ቢሮ ግሩኘ
    o ቀድሞ የነበረው የመንገዱ ደረጃ፦ አስፋልት

    3. መሰል/ሞሲሊ–ኮራ/ቆሪ–84.2 ኪ.ሜ /ኮንት 1/ መንገድ (ርዝመት 84.2 ኪ.ሜ)

    o የገንዘቡ መጠን፦ 1,536,235,563.54 ብር
    o የግንባታ ጊዜ ሚፈጀው፦ 42 ወራት
    o ኮንትራክተር፦ ቻይና ስቴት ኮንስትራክሽን ኢንጂነሪንግ ኮ. ሊሚትድ

    4. መሰል/ሞሲሊ–ኮራ/ቆሪ–84.2–ጠሩ ኪ.ሜ /ኮንት 2/ መንገድ (ርዝመት 73.34 ኪ.ሜ)

    o የገንዘቡ መጠን፦ 1,502,371,329.85 ብር
    o የግንባታ ጊዜ ሚፈጀው፦ 42 ወራት
    o ኮንትራክተር፦ ቻይና ስቴት ኮንስትራክሽን ኢንጂነሪንግ ኮ. ሊሚትድ

    5. አርሲ–ሮቤ–አጋርፋ–አሊ ኮንትራት 1 አሊ ከተማ-ዋቤ ድልድይ መንገድ (ርዝመት 53.5 ኪ.ሜ)

    o የገንዘቡ መጠን፦ 2,153,060,671.98 ብር
    o የግንባታ ጊዜ ሚፈጀው፦ 36 ወራት
    o ኮንትራክተር፦ ቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ኩባንያ (ሲሲሲሲ)

    6. አዲአርቃይ–ጠለምት መንገድ (ርዝመት 76.6 ኪ.ሜ)

    o የገንዘቡ መጠን፦ 1,981,378,049.64 ብር
    o የግንባታ ጊዜ ሚፈጀው፦ 36 ወራት
    o ኮንትራክተር፦ የንኮማድ ኮንስትራክሽን

    7. እስቴ–ስማዳ መንገድ (ርዝመት 53.08 ኪ.ሜ)

    o የገንዘቡ መጠን፦ 1,925,451,264.41ብር
    o የግንባታ ጊዜ ሚፈጀው፦ 36 ወራት
    o ኮንትራክተር፦ ቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ኩባንያ (ሲሲሲሲ)

    8. ውቅሮ–አጽቢ–ኮነባ መንገድ (ርዝመት 63 ኪ.ሜ)

    o የገንዘቡ መጠን፦ 1,745,722,493.86 ብር
    o የግንባታ ጊዜ ሚፈጀው፦ 42 ወራት
    o ኮንትራክተር፦ ሱር ኮንስትራክሽን

    የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን በመግለጫው እንዳስታወቀው መንገዶቹ ከዚህ በፊት በጠጠር ደረጃ የነበሩ ሲሆን አሁን ግን በአስፋልት ደረጃ የሚገነቡ ይሆናሉ። ለነዚህም ግንባታ ሙሉ ለሙሉ የኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ይሆናል።

    የመንገዶቹ ግንባታ በሚጠናቀቅበት ወቅት እንደ ጤፍ፣ ማር እና ፍየል እንዲሁም ሌሎች የግብርና ምርቶችንም ሆነ ሌሎች ምርቶችን ካለምንም ችግር ወደ ገበያ ለማውጣት ያስችላሉ። በተጨማሪም ከዚህ በፊት በአካባቢው የነበረውን የተቀላጠፈ የትራንስፖርት ችግር በመቅረፍ የአካባቢው ህብረተሰብ በተመጣጣኝ ዋጋ ወደ ፈለገው ቦታ የሚንቀሳቀስበትን ሁኔታ ያመቻቻሉ።

    እነዚህ መንገዶች በአገሪቱ ካለው ማ ኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ እንዲሁም መንግሥት ከያዘው የድህነትና የኋላቀርነት ቅነሳ ስትራቴጂ አንጻር ከፍተኛ አስተዋጽዖ እንደሚያበረክቱ ይታመናል። የመንገዶቹ ግንባታ በሚጠናቀቅበት ወቅት ከዚህ በፊት በአካባቢው የነበረውን የትራንስፖርት ችግር በመቅረፍ የአካባቢው ህብረተሰብ በቀላሉ ወደ ፈለገው ቦታ የሚንቀሳቀስበትን ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ከመሆኑም ባሻገር ፣ በኢንቨስትመንት የተሰማሩ ባለሃብቶች ያመረቱትን ምርት ወደ ገበያ ለማውጣት እንዲችሉና ሌሎች ባለሃብቶችም በአካባቢው ኢንቨስት ለማድረግ ተነሳሽነትን ከመፍጠር አኳያ የዚህ መንገድ መገንባት ጉልህ ሚና ይጫወታል።

    ከዚህም በተጨማሪ በአካባቢው የስራ ዕድል እንዲፈጠር በማስቻል ፣ በአካባቢው የሚገኙ ትንንሽ መንደሮች በከተማ ደረጃ እንዲስፋፉና እንዲያድጉ ከማድረግ እንዲሁም የጤና ፣ የትምህርት እና ሌሎች የማህበራዊ አገልግሎት ተቋማት በሰፊው እንዲስፋፉ ከማድረግ አንፃር ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረክታሉ ተብሎ ይታመናል። ስለሆነም የመንገድ ኘሮጀክቶቹ በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቁ በአካባቢው የሚገኙ የመስተዳድር አካላትና፣ የክልሉ ነዋሪዎች ከፍተኛ ትብብር እንዲያደርጉ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ያሳስባል።

    የኮንትራት ስምምነቱን የፈረሙት በኢመባ በኩል አቶ ሃብታሙ ተገኝ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሲሆኑ በተቋራጮቹ የሥራ ተቋራጮቹ ሥራ አስኪያጆች እና ተወካዮቻቸው ናቸው።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን (ኢመባ)

    የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.