የኢትዮጵያ ቀይ ቀበሮዎች ውሻን በሚያሳብድ በሽታ እየሞቱ ነው

Home Forums Semonegna Stories የኢትዮጵያ ቀይ ቀበሮዎች ውሻን በሚያሳብድ በሽታ እየሞቱ ነው

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #8710
    Semonegna
    Keymaster

    ሰዎች የእርሻና የግጦሽ ቦታዎችን ለማስፋት በጥብቅ ቦታዎች እና በፓርኮች ዙሪያ በሚያደርጉት ጣልቃ ገብነቶች የኢትዮጵያ ቀይ ቀበሮዎች የመኖርያ ቦታ ስጋት ላይ ከመውደቁ ባሻገር የዱር አራዊቱ በበሽታው እየተለከፉ መሆኑ ተጠቁሟል።

    (የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት) – የኢትዮጵያ ቀይ ቀበሮዎች ውሻን በሚያሳብድ በሽታ እየሞቱ መሆናቸው ተረጋግጧል።

    ብርቅዬ እንስሳቱን ውሻን ከሚያሳብድ በሽታ ለመከላከል ክትባት እየተሰጠ መሆኑን ደግሞ የአማራ ክልል አካባቢ ደን እና የዱር እንሰሳት ልማትና ጥበቃ ባለስልጣን አስታውቋል።

    በኢትዮጵያ ከሚገኙ ብርቅየ የዱር እንስሳት መካከል የኢትዮጵያ ቀይ ቀበሮዎች ይጠቀሳሉ። የኢትዮጵ ቀይ ቀበሮዎች በአማራ ክልል በሚገኙ የሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ፣ በቦረና ሳይንት “ወረ ሂመኑ ብሄራዊ ፓርክ፣” በመንዝ ጓሳ እና በአቡነ ዮሴፍ የማኅበረሰብ ጥብቅ ቦታዎች ይገኛሉ። በደላንታ ዳውንት አንዳንድ አካባቢዎችም አልፎ አልፎ እንደሚገኙ ከአማራ ክልል አካባቢ ደን እና የዱር እንሰሳት ጥበቃ ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

    በባለሥልጣኑ የዱር እንሰሳት ጥበቃ ባለስልጣን አቶ አብርሃም ማርየ እንደተናገሩት በነዚህ አካባቢዎች ከ2 መቶ በላይ በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙ የቀይ ቀበሮ ዝርያዎች አሉ።

    እንደ ባለስልጣኑ ገለፃ ብርቅየ የዱር እንስሳቱን ውሻን ከሚያሳብድ በሽታ ለመከላከል የሚያስችል ክትባት እየተሰጠ ነው።

    የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያን የተጋረጠባቸው አደጋ (ቪዲዮ)

    ሰዎች የእርሻና የግጦሽ ቦታዎችን ለማስፋት በጥብቅ ቦታዎች እና በፓርኮች ዙሪያ በሚያደርጉት ጣልቃ ገብነቶች የዱር አራዊቱ የመኖርያ ቦታ ስጋት ላይ ከመውደቁ ባሻገር ቀይ ቀበሮዎቹ በበሽታው እየተለከፉ መሆኑ ተጠቁሟል።*

    ባሳለፍነው ጥቅምት ወር በአቡነ ዮሴፍ የማኅበረሰብ ጥብቅ ስፍራ በሽታው የሞቱ የኢትዮጵያ ቀይ ቀበሮዎች መገኘታቸውም ተገልጧል። የበሽታውን ስርጭት ለመቀነስም ባለሥልጣኑ የኢትዮጵያ ቀይ ቀበሮ ፕሮጀክት ከተባለ ድርጅት ጋር በመተባበር በሁሉም የቀይ ቀበሮ መገኛ ቦታዎች ክትባት እየሰጠ ነው።

    አብዛኛዎቹ ቀይ ቀበሮዎች ክትባቱን እንዲያገኙ ለማድረግ ውሻን በሚያሳብድ በሽታ መድኃኒት የበለፀገ ስጋ በማቅረብ እንዲመገቡ የማድረግ ሥራ የክትባቱ አንድ አካል ነው።

    በተመሳሳይ መልኩ በመንዝ ጓሳ ማኅበረሰብ ጥብቅ ደን አራት የኢትዮጵያ ቀይ ቀበሮዎች ሞተው ተገኝተዋል። ለህልፈት የዳረጋቸው ናሙና ወደ እንግሊዝ ተልኮ “ካናዲስ ዲስትምፕተር” የተባለ በሽታ መሆኑ መረጋገጡን አቶ አብርሃም አስረድተዋል።

    የአማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት (አብመድ) እንደዘገበው ክትባቱ እስከያዝነው ኅዳር ወር መጨረሻ ይቆያል።

    * አፍሪካን ዋይልድላይፍ ፋውንዴሽን (African Wildlife Foundation – AWF) የተባለ ድርጅት ስለ አትዮጵያ ቀይ ቀበሮዎች ባወጣው ዘገባ እነዚህ የዱር አራዊት በቁጥራቸው እጅግ ለመምናመን እና ለህልውናቸው አስጊ የሆኑት ሁለት ዋነኛ ምክንያቶች፥ በሚኖሩበት አካባቢ በሚገኙ ሰዎች የሚዘወተር እርሻ እና የውሻ ዘርን የሚያጠቁ በሽታዎች ቢሆኑም የእርሻ ሥራ (እና ቦታውን ለከብቶች ግጦሽ ማዋል) ግን ከፍተኛውን ድርሻ ይወስዳል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እና AWF

    ቀይ ቀበሮዎች

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.