የወንዶ ገነት ኮሌጅ ከ400ሺ በላይ ሀገር በቀል የዛፍ ችግኞችን ለኅብረተሰቡ አከፋፈለ

Home Forums Semonegna Stories የወንዶ ገነት ኮሌጅ ከ400ሺ በላይ ሀገር በቀል የዛፍ ችግኞችን ለኅብረተሰቡ አከፋፈለ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #8145
    Semonegna
    Keymaster

    የወንዶ ገነት ደንና ተፈጥሮ ሀብት ኮሌጅ በሀገር አቀፍ ደረጃ የመጀመሪያ የሆነውን የትምህር ፐሮግራም በአየር ንብረት ለውጥ (Climate Change) ላይ በዶክትሬት ዲግሪ ተጨማሪ ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጅት አድርጓል።

    ወንዶ ገነት (HU) – በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የወንዶ ገነት ደንና ተፈጥሮ ሀብት ኮሌጅ ከ400ሺ በላይ ሀገር በቀል የዛፍ ችግኞችን ለኅብረተሰቡ ማከፋፈሉን አስታወቀ።

    በዩኒቨርሲቲው የኮሌጁ ዲን ዶ/ር ግርማ አማንቴ እንዳስታወቁት የችግኞቹ መሰራጨት በአሁኑ ወቅት በሀገር አቀፍ ደረጃ ጎልቶ የሚታየውን የአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያያዥ የሆኑ ችግሮችን ከማቃለል በተጨማሪ ሀገር በቀል የዛፍ ዝሪያዎችን ጠብቆ ለማቆየት ከፍተዋኛ አስተዋጽዖ ይኖረዋል።

    በደቡብ ክልል ሲዳማ ዞን እና በአጎራባች ኦሮሚያ ወረዳዎች በተለይም በስራሮ፣ አጄና አርስነገሌ ወረዳዎች በግል አርሶአደሮች፣ መንግስታዊና መንግስታዊ ባልሆኑ ተቋማት አማካይነት ተከላው መከናወኑን ከገለፃው ለመረዳት ተችሏል።

    በኮሌጁ የአካደሚክ ጉዳዮች ተባባሪ ዲን አቶ ግርማ መኩሪያ በበኩላቸው የወንዶ ገነት ደንና ተፈጥሮ ሀብት ኮሌጅ በተያዘው 2011 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ከመጀመሪያ ዲግሪ እስከ 3ኛዲግሪ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር ዝግጅት ማጠናቀቁን ጠቁመው፥ በተለይም በሀገር አቀፍ ደረጃ የመጀመሪያ የሆነውን የትምህር ፐሮግራም በአየር ንብረት ለውጥ (Climate Change) ላይ በዶክትሬት ዲግሪ ተጨማሪ ተማሪዎችን ለመቀበል መዘጋጀቱን አስረድተዋል።

    ለተማሪዎች በተግባር የተደገፈ ትምህርት የሚሰጥበትን አሠራር ለማጠናከር አዳዲስ የቤተ ሙከራ፣ የመማሪያ ክፍል እና የመሳሰሉት ግንባታዎች መጠናቀቃቸውን ገልፀው በየትምህርት ክፍሎች በሚደገፉ የሙከራ ሥራዎች የአከባቢው አርሶ አደሮች ከምግብ ሰብል በተጨማሪ የዓሣ ጫጩቶችን ተቀብለው በሰው ሰራሽ ኩሬዎች በማርባት ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተደረገ እንደሆነ አብራርተዋል። ኮሌጁ ከተመሠረተ ጀምሮ ለ39 ጊዜያት ተማሪዎችን አስተምሮ አስመርቋል።

    የወንዶ ገነት ደንና ተፈጥሮ ሀብት ኮሌጅ ታሪክ (በእንግሊዝኛ)

    The Wondo Genet College of Forestry and Natural Resources (WGCF-NR), part of Hawassa University, was established in 1978 to train forestry professionals, through technical and financial assistance from the Swedish International Development Agency (SIDA). Over the years the WGCF-NR has grown into one of the foremost educational centers in the country providing BSc, MSc and PhD training programs in areas related to forestry, natural resource and wildlife management. It is the only forestry training institute in the country and the majority of forestry professionals in Ethiopia have been educated at the WGCF-NR. WGCF-NR has a representative that sits on the REDD+ Steering Committee. It is expected that the WGCF-NR will be actively involved in the national REDD+ process through research but also in on-the-ground efforts at establishing a national Monitoring, Reporting and Verification (MRV) system.  

    ምንጭ፦ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ | The REDD Desk

    የወንዶ ገነት ደንና ተፈጥሮ ሀብት ኮሌጅ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.