የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ አዲሱ ፕሬዝዳንት ከዩኒቨርሲቲው ኮሌጆችና አስተዳደር ሠራተኞች ጋር ያዘጋጁት የምክክር መድረክ

Home Forums Semonegna Stories የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ አዲሱ ፕሬዝዳንት ከዩኒቨርሲቲው ኮሌጆችና አስተዳደር ሠራተኞች ጋር ያዘጋጁት የምክክር መድረክ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #10847
    Semonegna
    Keymaster

    በምክክር በድረኩም የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ አዲሱ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሐብታሙ አበበ ዩኒቨርሲቲውን በታታሪነት፣ በታማኝነት እና በቅንነት በማገልገል ዩኒቨርሲቲውን የልሂቃን ተቋም እና የመጀመሪያ ተመራጭ ዩኒቨርሲቲ ለማድረግ ተግተው እንደሚሠሩ ገልጸዋል።

    ሆሳዕና ከተማ (ሰሞነኛ)– ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ለአራት ወራት ያህል ለዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንትነት መረጣ ሲያካሂድ ቆይቶ፥ ለመጨረሻ ዙርም ዶ/ር ሐብታሙ አበበ፣ ዶ/ር ኑሪ ላፌቦ እና ዶ/ር አብርሃም አለማየሁ አልፈው ነበር። ከእነዚህ ሦስት ዕጩ ተወዳዳሪዎች መካከልም ዶ/ር ሐብታሙ አበበ በአጠቃላይ ውጤት 69.57% በማስመዝገብ ለዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንትነት ብቁ መሆናቸውን አስመስክረው፣ የኢፌዴሪ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚያዝያ 24 ቀን 2011 ዓ.ም. ለዩንቨርሲቲውና ለሚመለከታቸው ቢሮዎች በፃፈው ደብዳቤ ዶ/ር ሐብታሙ አበበን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ሆነው ተሹመዋል።

    የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ሆነው የተሾሙት ዶ/ር ሐብታሙ አበበ ለፕሬዝዳንትነት ሲወዳደሩ ያቀረቡትን የዩኒቨርሲቲውን የእድገት ስልታዊ ዕቅድ (University’s Development Strategic Plan) በይበልጥ ለማስገንዘብ እና በዩኒቨርሲቲው ውስጥ የላቀ ታታሪነት፣ ትብብር እና ስኬታማ የመማር ማስተማር፣ የምርምር እና የማኅበረሰብ አገልግሎት ስኬቶችን ለማስመዝገብ የሚያስችላቸውን የመጀመሪያ ዙር ምክክር ከማኅበራዊ ሳይንስ፣ ንግድ እና ምጣኔ ሀብት (Business and Economics)፣ ከግብርናና ከተፈጥሮ ሀብት ኮሌጆች እና ከሕግ ትምህርት ቤት ጋር ግንቦት 5 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምረዋል።

    በምክክር በድረኩም ፕሬዝዳንቱ ዩኒቨርሲቲውን በታታሪነት፣ በታማኝነት እና በቅንነት በማገልገል ዩኒቨርሲቲውን የልሂቃን ተቋም እና የመጀመሪያ ተመራጭ ዩኒቨርሲቲ ለማድረግ ተግተው እንደሚሠሩ በመግለጻቸው ከተሰብሳቢ መምህራን አድናቆት ከመቸራቸውም በላይ በጋራ ራዕያቸውን ለማሳካት ተግተው አብረዋቸው እንደሚሠሩ መምህራኑ ቃል ገብተውላቸዋል።

    ፕሬዝዳንቱ እያደረጉት ያለውን የምክክር መድረክ ቀጥለው ግንቦት 6 ቀን 2011 ዓ.ም. በዩንቨርሲቲው ዱራሜ ካምፓስ፣ ግንቦት 7 ቀን በዋናው ካምፓስ ምህንድስና (Engineering)፣ ጤና እና የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ (Natural and Computational Sciences) ኮሌጆች፣ በመጨረሻም ግንቦት 8 ቀን በዩንቨርሲቲው የንግስት እሌኒ መሐመድ መታሰቢያ ሆስፒታል እና ከዩኒቨርስቲው የአስተዳደር ሠራተኞች ጋር እእንደሚቀጥል ታውቋል።

    ዶ/ር ሐብታሙ አበበ በሐምሌ ወር 2011 ዓ.ም. አንድራ ፕራዴሽ (Andhra Pradesh) ግዛት (ደቡም ምስራቃዊ ህንድ) ውስጥ ከሚገኘው አንድራ ዩኒቨርሲቲ (Andhra University) የዶክትሬት ዲግሪያቸውን አግኝተዋል።

    ምንጭ፦ ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ሐብታሙ አበበ


Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.