ዲላ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ሆስፒታል የዓይን ሕክምና ማዕከል አገልግሎት መሥጠት ጀመረ

Home Forums Semonegna Stories ዲላ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ሆስፒታል የዓይን ሕክምና ማዕከል አገልግሎት መሥጠት ጀመረ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #12651
    Semonegna
    Keymaster

    ዲላ፥ ኢትዮጵያ (ዲዩ) – ዲላ ዩኒቨርሲቲ (ዲዩ) ሪፈራል ሆስፒታል ከኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ እና ከደቡብ ክልል ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር የዓይን ህክምና ማዕከል በመገንባት በዲላ ከተማ እና አካባቢው ለሚገኝ ማኅበረሰብ የተለያዩ የዓይን ችግር (የትራኮማ፣ የዓይን ማየት ችግር፣ የሞራ ግርዶሽ) ያለባቸው ሰዎችን ቀዶ ህክምና አገልግሎት መስጠት ጀምረ።

    የዓይን ህክምና ክፍል አስተባባሪ የሆኑት አቶ ቢንያም እስጢፋኖስ፥ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ሆስፒታል ለአስር ዓመታት በአንድ ክፍል ውስጥ በቂ ባልሆነ የዓይን ህክምና እየሰጠ በመሆኑ ይርጋለም፣ ሀዋሳ እና አዲስ አበባ ሲላኩ (“ሪፈር” ሲደረጉ) በሽተኞች፣ በተለይም ከገጠሩ አከባቢ የሚመጡ ህክምና ፈላጊዎች ለተለያዩ ችግሮች ይጋለጡና ለእንግልት ይዳረጉ ነበር። በዚህ ምክንያት ከኦርቢስ ኢንተርናሽናል ጋር በመተባበር ህንፃውን ለማቋቋም ግንባታው ለአንድ ዓመት ሲገነባ እንደነበረና አሁን የሞራ ግርዶሽ ህክምና (cataract surgery) እየተሰጠ መሆኑን ተናግረዋል።

    የጌዴኦ ዞን፣ ቡርጅና አማሮ የመስክ አስተባባሪ የሆኑት አቶ ተመስገን ጌታቸው፥ “ከዚህ በፊት ለተለያዩ ነገሮች መጋለጥ ይኖራል፤ አሁን ግን ኦርቢስ ኢንተርናሽናል ስለተቋቋመ እነዚህ ችግሮች ሁሉ ይቀረፍላቸዋል፤ ጊዜያቸውንም ይቆጥባሉ፤ በጊዜም ህክምናውን ያገኛሉ ብለዋል።” ኦርቢስ ዓለምአቀፍ ኘሮጀክት የሥራ ድርሻው አስፈላጊ የህክምና እቃዎችን የማሟላት እገዛና የባለሙያውን ክኅሎት ለመጨመር ድጋፍ ማድረግ ሲሆን ሌሎች ነገሮች ሆስፒታሉ የሚችል መሆኑን አቶ ተመስገን ገልጸዋል።

    ለጊዜው ኦርቢስ ኢንተርናሽናል ለጊዜው የባለሙያዎች አቅም ግንባታ ስልጠና የመስጠት ተግባር እያከናወነ ቢሆንም የተለያዩ የዓይን ችግር ያለባቸው ሰዎችን የትራኮማ፣ የዓይን ማየት ችግር ያለባቸው የሞራ ግርዶሽ ቀዶ ህክምና በተጓዳኝነት መስጠት በመጀመሩ ሥራው ከተጀመረ በ5 ቀናት ውስጥ ከ200 በላይ የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ጥገና እንደሚያገኙ ይጠበቃል። ህክምናው ከተጀመረ ጀምሮ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ህመምተኞች ለተለያዩ የዓይን በሽታዎች ምርመራ ተደርገው ከ140 በላይ የሞራ ግርዶሽ ቀዶ ህክምና መሠራቱን ተገልጿል።

    ህክምናው በቅርበት በዲላ ሪፈራል ሆስፒታል መከፈቱ ከዚህ በፊት በዓመት 3 ጊዜ ብቻ የነጻ ህከምና እንደሚሰጥና ሀዋሳ እና ይርጋለም በመመላለስ የህክምና፣ የትራንስፖርት እና የመኝታ ወጪ ብቻ ከ3 ሺህ ብር በላይ ይወጣ የነበረው ከመቅረቱም ባሻገር የነፃ ህክምና ሳይመላለሱ በአንድ ቀን አገልግሎት ማግኘት መቻላቸው ታካሚዎችና አስታማሚዎች እንዳስደሰታቸው ገልጸዋል።

    ምንጭ፦ ዲላ ዩኒቨርሲቲ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ዲላ ዩኒቨርሲቲ የዓይን ህክምና

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.