የጎሳዬ ተስፋዬ “ሲያምሽ ያመኛል” አዲስ አልበም በገበያ ላይ ዋለ

Home Forums Semonegna Stories የጎሳዬ ተስፋዬ “ሲያምሽ ያመኛል” አዲስ አልበም በገበያ ላይ ዋለ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #9139
    Semonegna
    Keymaster

    ድምጻዊ ጎሳዬ ተስፋዬ አዲስ ያወጣው “ሲያምሽ ያመኛል” የተሰኘው የሙዚቃ አልበም አስራ አንድ ዓመታትን እንደፈጀ፤ በግጥም፣ በዜማ እና በቅንብር ከአስራ ሦስት ባለሙያዎች በላይ እንደተሣተፉበት እና ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ ፈሰስ እንደተደረገበት ተዘግቧል።

    አዲሰ አበባ (ሰሞነኛ) – በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የተወዳጁ ድምፃዊ ጎሳዬ ተስፋዬ አምስተኛ ሙሉ የአልበም ሥራው የሆነውና “ሲያምሽ ያመኛል” የተሰኘው የሙዚቃ አልበም ታህሳስ 26 ቀን 2011 ዓ.ም. በኢትዮጵያና በመላው ዓለም በገበያ ላይ ውሏል።

    አራተኛ አልበሙን “ሳታመሃኝ ብላ” በሚል ርዕስ ካወጣ ከ11 ዓመታት በኋላ ለአድናቂዎቹ ያቀረበው ይህ አዲስ አልበም፥ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደተደረገበት አከፋፋዩ “ሪቮ ኮሚዩኒኬሽንና ኢቨንት” መግለጹን ሳምንታዊ አዲስ አድማስ ጋዜጣ ዘግቧል።

    በኢትዮጵያ ሙዚቃ ተጽዕኖ ፈጣሪ ከሚባሉትትና የላቀ እውቅናን ከተጎናጸፉት ድምፃዊያን አንዱ የሆነው የድምፃዊ ጎሳዬ ተስፋዬ አዲስ አልበም፣ ለረጅም ጊዜ በጉጉት ሲጠበቅ የቆየ ሲሆን፥ ደረጃውን የጠበቀና የተዋጣለት አልበም ለማድረግ ሲባል 11 ዓመታትን መፍጀቱንና ግጥምና ዜማቸው ተሠርተው ከተጠናቀቁ ከ40 በላይ ሥራዎች ውስጥ 15ቱ ተመርጠው በዚህ አልበም መካተታቸውን አከፋፋዩ ጨምሮ ገልጿል።

    አማርኛ ሙዚቃ፦ ድምጻዊ እሱባለው ይታየው — ዘፈን ማሞቂያ አይደለም

    በዚህ አዲስ አልበም ላይ ከተሳተፉ እውቅ የሙዚቃ አቀናባሪዎች መካከል አበጋዝ ክብረወርቅ ሺዎታ፣ ካሙዙ ካሳአቤል ጳውሎስ፣ መኮንን ለማ (ዶክተሬ)፣ ሚካኤል ኃይሉ (ሚኪ ጃኖ) እና ሱልጣን ኑሪ (ሶፊ) እንደሚገኙበት የገለፀው አከፋፋዩ፥ በግጥምና ዜማውም ከዚህ ቀደም በሠሩት ሥራ አንቱታን ያተረፉት አለምፀሐይ ወዳጆ፣ ይልማ ገ/አብ፣ ሀብታሙ ቦጋለ፣ ቢኒያም መስፍን (ቢኒባና)፣ አለማየሁ ደመቀ፣ መሰለ ጌታሁን እና ራሱ ጎሳዬ ተስፋዬ ተሳትፈውበታል ተብሏል።

    በአገራዊ፣ በማኅበራዊ እና በፍቅር ዙሪያ የሚያጠነጥኑ 15 ሙዚቃዎችን ያካተተው “ሲያምሽ ያመኛል” አልበም ሪከርድ የተደረገው በአሜሪካ ኒው ዮርክ ሲቲ ሲሆን ጥራትና ደረጃውን የጠበቀና ዘመኑ ያፈራው የሪከርዲንግ ቴክኖሎጂ አሻራ ያረፈበት መሆኑም ታውቋል።

    ጎሳዬ ተስፋዬ ከዚህ ቀደም “ሶፊ”፣ ከሌሎች ድምፃዊያን ጋር “ቴክ ፋይቭ”፣ ከአለማየሁ ሂርጶ ጋር “ኢቫንጋዲ” እና በ1999 ዓ.ም ለብቻው የሠራውን “ሳታመሃኝ ብላ” የተሰኙ የሙዚቃ አልበሞችን ለአድናቂዎቹ ማቅረቡ ይታወሳል።

    ◌ ሲያምሽ ያመኛል አልበምን በዲጂታል ለመግዛት: CD Baby Siyamish Yamegnal by Gossaye Tesfaye

    ምንጭ፦ አዲስ አድማስ ጋዜጣ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    ጎሳዬ ተስፋዬ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.