ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የዓመቱ ምርጥ አፍሪካዊ ለመባል በዕጩነት ተመረጡ

Home Forums Semonegna Stories ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የዓመቱ ምርጥ አፍሪካዊ ለመባል በዕጩነት ተመረጡ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #8731
    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) አፍሪካዊ የአመራር መጽሔት (African Leadership Magazine) በሚያዘጋጀው የዓመቱ ምርጥ አፍሪካዊ ምርጫ ላይ ለ2018 ዓ.ም. (እ.ኤ.አ) የዓመቱ ምርጥ አፍሪካዊ መሪ ለመባል ዕጩ ሆነው ተመርጠዋል።

    መጽሔቱ የዓመቱ ምርጥ ሰው ብሎ የሚመርጠው በተለያዩ ዘርፎች ለአፍሪካ እና አፍሪካውያን የላቀ አስተዋጽዖ ያበረከቱ እና እጅግ ጉልህ የሆነ ተጽዕኖ የፈጠሩ አፍሪካውያንን በማወዳደር ሲሆን፥ መጽሔቱ መታተም ከጀመረበት እ.ኤ.አ 2008 ዓ.ም. ጀምሮ ሽልማቱ ይሰጣል።

    ዘንድሮ በእጩነት ከቀረቡት መካከል በወንድ መሪዎች ዘርፍ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በ97.25% ድምጽ በማግኘት ቀዳሚውን ቦታ ሲይዙ፣ የቀድሞው የቦትስዋና ፕሬዝደንት የሆኑት ሰረትሴ ካማ ኢያን ካማ (Serêtsê Khama Ian Khama) በ2.00% የምርጫ ድምጽ ሁለተኛ፣ የነዳጅ ላኪ ሀገራት ህብረት (Organization of the Petroleum Exporting Countries – OPEC) ጠቅላይ ሰብሳቢ የሆኑት ናይጀርያዊው መሐመድ ሳኑሲ ባርኪንዶ (Mohammed Sanusi Barkindo) በ0.75% የምርጫ ድምጽ በሦስተኝነት ይከተላሉ።

    የአፍሪካዊ የአመራር መጽሔት ዋና አዘጋጅ ዶ/ር ኬን ጊያሚ (Dr. Ken Giami) እንደገለጸው የዘንድሮው ምርጫ ከሌሎች ጊዘያት በተለየ መልኩ ብዙ ሰዎች፣ ከሁሉም የ አፍሪካ አቅጣቻዎች ድምጽ የሰጡበት ሁሉም ዕጩዎች ያጋጠማቸውን ተግዳሮቶች አሸንፍው በተሠማሩባቸው መስኮች ሁሉ የሚጠበቅባቸውን በመወጣት ልቀው ሊታዩ ችለዋል ብሏል።

    በሰባት የዕጩነት ቦታዎች (ስድስት ዘርፎች) በአጠቃላይ ሰላሳ (30) አፍሪካውያን ለዕጩኘት የቀረቡ ሲሆን፥ በሀገር ደረጃ በአጠቃላይ ናይጄርያ አስር (10) ዕጩዎችን በማስመረጠ ቀዳሚውን ስፍራ ይዛለች። የሰላሳዎች ዕጩዎች ሀገራዊ ስብጥር፥ ቦትስዋና (2)፣ ኬፕ ቨርዴ (1)፣ ግብጽ (1)፣ ኢትዮጵያ (1)፣ ጋና (4)፣ ኬንያ (1)፣ ሞሮኮ (2)፣ ናይጄርያ (10)፣ ሴኔጋል (1)፣ ደቡብ አፍሪካ (5)፣ እስዋቲኒ/ስዋዚላንድ (1)፣ እና ታንዛንያ (1) መሆናቸው ታውቋል።

    ከዕጩዎቹ መካከል አሸናፊዎቹን ለመለየት ማንኛውም ግለሰበ የመጽሔቱ ድረ-ገጽ ላይ ሄዶ መምረጥ (ድምጽ መስጠት) ይችላል። (ድረ-ገጹን እዚህ ጋር ያገኙታል)። በድረ-ገጽ ድምጽ የመስጠት ተግባር እ.ኤ.አ ታህሳስ 10 ቀን 2018 ዓ.ም. በመካከለኛው አፍሪካ ሰዓት እኩለ ሌሊት (10th December 2018, at midnight Central African Time.) ላይ ይጠናቀቃል ይዘጋል።

    አምና እ.ኤ.አ በ2017 ዓ.ም. በተደረገው ተመሳሳይ ምርጫ የሩዋንዳው ፕሬዚደንት ፖል ካጋሜ (Paul Kagame) የዓመቱ ምርጥ አፍሪካዊ መሪ ሆነው መመረጣቸው ይታወሳል።

    አፍሪካዊ የአመራር መጽሔት (African Leadership Magazine) መቀመጫነቱን በእንግሊዝ ሀገር፣ ፖርትስማውዝ ከተማ አድርጎ አፍሪካንና አፍሪካውያንን ከተቀረው ዓለም ጋር ለማገናኘት፣ ለማቀራረብ የሚሠራ የህትመት ድርጅት ነው። በየዓመቱም በተለያዩ ዘርፎች አፍሪካና አፍሪካውያን ላይ በተለያየ መልኩ ጉልህ ሚና የተጫወቱ አፍሪካውያንን “የዓመቱ ምርጥ አፍሪካውያን” ብሉ ይመርጣል።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ዐቢይ አህመድ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.