Search Results for 'ሙላቱ ተሾመ'

Home Forums Search Search Results for 'ሙላቱ ተሾመ'

Viewing 4 results - 1 through 4 (of 4 total)
  • Author
    Search Results
  • Semonegna
    Keymaster

    ቤልካሽ ኢትዮጵያ የሚያስጀምራቸው ሄሎማርኬት እና ሄሎሾፕ የተሰኙ ሁለት የኤሌክትሮኒክስ መገበያያ ገፆች በኢትዮጵያ ውስጥ እና ከኢትዮጵያ ውጪ ለሚገኙ ተገልጋዮች ኢንተርኔት አማካኝነት ግብይት መፈም የሚችሉባቸው ናቸው።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ቤልካሽ ኢትዮጵያ ተጠቃሚዎች በበይነመረብ (ኢንተርኔት) አማካኝነት ግብይት መፈም የሚችሉባቸው ሁለት የኤሌክትሮኒክስ መገበያያ ገፆችን በቅርቡ እንደሚያስጀምር አስታወቀ።

    ሄሎማርኬት (Hellomarket) የተሰኘው ገፅ በዋነኛነት በኢትዮጵያ ውስጥ ለሚገኙ ተገልጋዮቹ ብቻ ካሉበት ቦታ ሆነው ቁሳቁሶችን የሚሸምቱበት አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን በበይነመረብ አማካኝነት የግዥ ትዕዛዝ እና ክፍያ የተፈፀመባቸው ቁሳቁሶቹን ወደ ደምበኞች ለማጓጓዝም ከ ዓለምአቀፉ ዲኤችኤል (DHL) ጋር ስምምነት ተፈራርሟል።

    The dispute between RIDE Taxi, Ethiopian-kind of Uber, and Addis Ababa Transport Authority continues

    ተቋሙ በመጀመርያው ምዕራፍ ወደ 2,500 የሚጠጉ ሴት ኢትዮጵያውያን በባለቤትነት በሚያስተዳድሩዋቸው የተለያዩ ድርጅቶች የተመረቱ ምርቶችን ለማሻሻጥ ቅድመ ዝግጅቱን አጠናቋል።

    በተመሳሰይ ቤልካሽ ከኢትዮጵያ ውጭ ሆነው የኤሌክትሮኒክ ግብይት መፈፀም ለሚፈልጉ ደንበኞቹ አገልግሎት የሚሰጥ ሄሎሾፕ (Helloshop) የተሰኘ ሌላ ገፅ ያዘጋጀ ሲሆን የክፍያ ስርዓቱም በማስተር ካርድ አማካኝነት አንደሚከወን ለማወቅ ተችሏል።

    Ethiopia – blueMoon Incubator and Addis Garage co-working space for startups in Ethiopia

    ቤልካሽ ኢትዮጵያ መቀመጫውን ኔዘርላንድ ባደረገው እና ቤልካሽ ቴክኖሎጂ ሶሉሽን (Belcash Technology Solutions) የተሰኘ በኤሌክትሮኒክ ክፍያ ቴክኖሎጂ ዘርፍ ላይ የተሰማራ ድርጅት እህት ኩባንያ ሲሆን እ.ኤ.አ ከ2011 ጀምሮ በኢትዮጵያ በተለይም በሞባይል ክፍያ እና የገንዘብ ማስተላለፍ ዘርፎች ላይ የተለያዩ ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ከኩባንያው ድረገፅ የተገኘ መረጃ ያመላክታል።

    የኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ሥርዓት በተገቢው አለመስፋፋት እና በዚህ ዘርፍ ላይ ግልፅ የሆኑ ፖሊሲዎችን አለመኖራቸው በኢትዮጵያ መሰል የኤሌክተሮኒክ ግብይት ተቋማት እንዳይስፋፉ እንቅፋት መሆኑን ባለሞያተኞች ይገልፃሉ።

    ከዚህ ዜና ጋር በተመሳሳይ የቻይናው ግዙፉ የኤሌክትሮኒክስ መገበያያ (e-commerce) አሊባባ ኢትዮጵያ ውስጥ ገብቶ ለመሥራት ፍላጎት እንዳለውና ከኢትዮጵያ ባላስልጣናት ጋር (የቀድሞ የኢፌዴሪ ፕሬዝደንት ዶ/ር ሙላቱ ተሾመን ጨምሮ) መወያየቱን የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዘግቦ ነበር

    ምንጭ፦ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ / አዲስ ፎርቹን
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    ቤልካሽ ኢትዮጵያ


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ ኢትዮጵያ) – የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የፌደሬሽን ምክር ቤቶች ጥቅምት 15 ቀን 2011 ዓ.ም. ባካሄዱት ልዩ ስብሰባቸው አምባሳደር ሳህለወርቅ ዘውዴን 4ኛው የኢትዮጵያ ርዕሰ ብሄር (ፕሬዝዳንት) አድርጎ በሙሉ ድምፅ መርጧል።

    ፕሬዝዳት ሳህለወርቅ ዘውዴ ቃለ መሃላ ፈፅመው ኃላፈነታቸውን በትጋትና በታኝነት አገርና ህዝብን ለማገልገል ቃል ገብተዋል።

    አምባሳደር ሳህለ ወርቅ ዘውዴ ላለፉት አመስት ዓመታት በፕሬዝዳንትነት ላይ የነበሩትን ዶ/ር ሙላቱ ተሾመን በመተካት አገሪቱን በፕሬዝዳንትነት የሚመሩ ይሆናል። ተሰናባቹ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሙላቱ ተሾመም ከተመራጯ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ጋር የስልጣን ርክክብ አድርገዋል።

    አምባሳደር ሳህለወርቅ ዘውዴ ማን ናቸው?

    ተወልደው ያደጉት አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ሲሆን የመጀመሪያና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን የተከታተሉት በሊሴ ገብረማርያም ትምህርት ቤት ነው። አራት ሴት ልጆች ለነበሯቸው ወላጆቻቸው የመጀመሪያ ልጅ የሆኑት ሳህለወርቅ ዘውዴ ገና በ17 ዓመታቸው ነጻ የትምህርት ዕደል አግኝትው ወደ ፈረንሳይ በማቅናት ሞንትፔልየር (Montpellier) በምትባለው የፈረንሳይ ከተማ በሚገኘው ዮኒቨርሲቲ ኦፍ ሞንትፔልየር (University of Montpellier) የተፈጥሮ ሳይንስን አጥንተዋል። በሀገረ ፈረንሳይ ለዘጠኝ ዓመታት ከቆዩ በኋላ ወደ ኢትዮጵይ በመመለስ በትምህርት ሚኒስቴር ውስጥ የሕዝብ ግንኙነት ክፍልን ማገልገል ጀመሩ። ቆይተውም የሕዝብ ግንኙነት ክፍሉን በበላይነት መርተዋል። ከዚያም ወደ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በመዘዋወር በተለያዩ የሥራ ኃላፊነቶች አገልግለዋል።

    ወሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ በአምባሳደርነት ለመሾም ከአምባሳደር ዮዲት እምሩ ቀጥሎ ሁለተኛዋ እንስት ናቸው። በመጀመሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው የተሾሙትም ሴኔጋል ሲሆን የአምባሳደርነት ስልጣናቸውም ሴኔጋልን ጨምሮ ማሊን፣ ኬፕ ቨርዴን፣ ጊዚ ቢሳውን፣ ጋምብያን እና ጊኒን (እ.ኤ.አ 1989–1993) ያጠቃልል ነበር። ቀጥሎም እ.ኤ.አ 1983–2002 በጅቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደርና በኢጋድ (IGAD) የኢትዮጵያ ተጠሪ ሆነው አገልግለዋል። እ.ኤ.አ ከ2002 ጀምሮ እስከ 2006 ድረሰ በፈረንሳይ (ሞሮኮን ጨምሮ) የኢትዮጵያ አምባሳደርና በዩኔስኮ (UNESCO) የኢትዮጵያ ተጠሪ ሆነው አገልግለዋል። እ.ኤ.አ ከ2006 ጀምሮ እስከ 2009 ድረስ በአፍሪካ ህብረት (AU) እና በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) የኢትዮጵያ ተጠሪ ሆነው ሀገራቸውን አገልግለዋል።

    ከሀያ ዓመታት በላይ በተለያዩ ሀገራትና ዓለማቀፋዊ ድርጅቶች የኢትዮጵያ አምባሳደርና ተጠሪ በመሆን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤትን ያገለገሉት አምባሳደር ሳህለወርቅ ዘውዴ እ.ኤ.አ በ2009 የተበባሩት መንግስታት ድርጅትን (ተመድ) በመቀላቀል የድርጅቱ በመካከለኛው አፍሪካ ሪፑብሊክ የተቀናጀ ሰላም ግንባታ መሪ (Head BINUCA) በመሆን ማገልገል ጀመሩ። ይህ አገልግሎታቸውም ወደ ሚቀጥለው ኃላፊነት አሸጋግሯቸው እ.ኤ.አ በ2011 ዓም የዚያን ጊዜ የተመድ ጠቅላይ-ጸሀፊ ባን ኪ-ሙን (Ban Ki-moon) አዲስ ለተቋቃመው በናይሮቢ የተመድ ጽህፈት ቤት (UNON) የመጀመሪያዋ ጠቅላይ-መሪ አድርገው ሾማቸው። በዚያም ለሰባት ዓመታት ካገለገሉ በኋላ እ.ኤ.አ በሰኔ ወር 2010 የአሁኑ የተመድ ጠቅላይ-ጸሀፊ አንቶንዮ ጉቴሬስ (António Guterres) አምባሳደር ሳህለወርቅ ዘውዴን በተመድ ጠቅላይ-መሪ ስር (Under-Secretary-General) የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተጠሪ (UN’s Special Representative to the AU) እና በአፍሪካ ህብረት ውስጥ የተመድ ጽህፈት ቤት ዋና ኃላፊ (Head of UNOAU) አድርገው ሾሟቸው እስካሁን ድረስ በዚሁ ሹመታቸው እያገለገሉ ይገኛሉ።

    አምባሳደር ሳህለወርቅ ዘውዴ ባለትዳርና የሁለት ወንድ ልጆች እናት ናቸው።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ሳህለወርቅ ዘውዴ


    Semonegna
    Keymaster

    የኢፌዴሪ መንግስት የፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመን የመልቀቂያ ጥያቄ ከተቀበለ ከሀያ ዓመታት በላይ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ስር በአምባሳደርነትና የኢትዮጵያ ተጠሪነት ያገለገሉት አምባሳደር ሳህለወርቅ ዘውዴ ፕሬዝዳንት ሆነው እንደሚሾሙ የተለያዩ የዜና ምንጮች ዘግበዋል።

    አዲስ አባባ – ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ (ዶ/ር) ሀሙስ ጥቅምት 15 ቀን 2011 ዓ.ም. በሚውለው የሕዝብ ተወካዮችና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች 2ኛ አስቸኳይ መደበኛ ስብሰባ የሥራ መልቀቂያ እንደሚያቀርቡ ይጠበቃል። የአስቸኳይ ስብሰባው ዋና አጀንዳ የፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመን የሥራ መልቀቂያ መቀበልና አዲስ ፕሬዚዳንት መምረጥ እንደሚሆን ተገልጿል።

    ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ (ዶ/ር) የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሆነው የተመረጡት መስከረም 27 ቀን 2006 ዓ.ም ሲሆን ሶስተኛው ፕሬዚዳንትም (ከዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ እና አቶ ግርማ ወልደጊዮርጊስ ቀጥሎ) ናቸው።

    ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ወለጋ አርጆ ከተማ በ1949 ዓ.ም ነው የተወለዱት፤ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በቻይና የፖለቲካ ኢኮኖሚ ፍልስፍና፣ ሁለተኛውን በህግና ዲፕሎማሲ ከአሜሪካ፣ 3ኛ ዲግሪያቸውን ከቻይና ቤጂንግ ዩኒቨርስቲ በህግ አግኝተዋል።

    ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ በጃፓንና በቻይና የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ሆነው ያገለገሉ ሲሆን፤ ከ1993-1994 ዓ.ም የግብርና ሚኒስትር፣ ከጥቅምት 1994-1998 ዓ.ም የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ሆነውም አገልግለዋል። በፕሬዝዳንትነት እስከተመረጡበት ጊዜም በቱርክ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ነበሩ።

    ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ የተለያዩ የምርምር ሥራዎችን በተለያዩ መስኮች ያከናወኑና በመምህርነትም ያገለገሉ ሲሆን ከአገር ውስጥ አማርኛና ኦሮምኛ ከውጭ ደግሞ እንግሊዝኛ፣ ቻይንኛና ፈረንሳይኛ ቋንቋዎችን መናገርና መጻፍ ይችላሉ።

    በኢፌዴሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 70 ንዑስ አንቀጽ 4 መሰረት የአንድ ፕሬዝዳንት አገልግሎት ጊዜ ስድስት ዓመት ሲሆን፥ አንድ ግለሰብ ከሁለት ጊዜ በላይ በርዕሰ ብሔርነት ሊመረጥ እንደማይችል ይደነግጋል። ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ የመጀመሪያ ቨፕሬዝዳትነት አምስተኛ ዓመታቸው ነው።

    ከዚህ ጋር በተያያዘ የተለያዩ የሀገር ውስጥ ሚዲያዎች ኢትዮጵያን ከሀያ ዓመታት በላይ በሚኒስቴርነትና በአምባሳደርነት ያጋለገሉት አምባሳደር ሳህለወርቅ ዘውዴ ቀጣዩ የኢትዮጵያ ርዕሰ ብሔር (ፕሬዝዳንት) ይሆናሉ ብለው ቅድመ ግምታቸውን እየሰጡ ነው። በዚህም አምባሳደር ሳህለወርቅ ዘውዴ ፕሬዝዳንት ሆነው ከተመረጡ በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያዋ እንስት ፕሬዝዳንት ይሆናሉ ማለት ነው።

    ለመሆኑ አምባሳደር ሳህለወርቅ ዘውዴ ማን ናቸው?

    ተወልደው ያደጉት አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ሲሆን የመጀመሪያና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን የተከታተሉት በሊሴ ገብረማርያም ትምህርት ቤት ነው። አራት ሴት ልጆች ለነበሯቸው ወላጆቻቸው የመጀመሪያ ልጅ የሆኑት ሳህለወርቅ ዘውዴ ገና በ17 ዓመታቸው ነጻ የትምህርት ዕደል አግኝትው ወደ ፈረንሳይ በማቅናት ሞንትፔልየር (Montpellier) በምትባለው የፈረንሳይ ከተማ በሚገኘው ዮኒቨርሲቲ ኦፍ ሞንትፔልየር (University of Montpellier) የተፈጥሮ ሳይንስን አጥንተዋል። በሀገረ ፈረንሳይ ለዘጠኝ ዓመታት ከቆዩ በኋላ ወደ ኢትዮጵይ በመመለስ በትምህርት ሚኒስቴር ውስጥ የሕዝብ ግንኙነት ክፍልን ማገልገል ጀመሩ። ቆይተውም የሕዝብ ግንኙነት ክፍሉን በበላይነት መርተዋል። ከዚያም ወደ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በመዘዋወር በተለያዩ የሥራ ኃላፊነቶች አገልግለዋል።

    ወሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ በአምባሳደርነት ለመሾም ከአምባሳደር ዮዲት እምሩ ቀጥሎ ሁለተኛዋ እንስት ናቸው። በመጀመሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው የተሾሙትም ሴኔጋል ሲሆን የአምባሳደርነት ስልጣናቸውም ሴኔጋልን ጨምሮ ማሊን፣ ኬፕ ቨርዴን፣ ጊዚ ቢሳውን፣ ጋምብያን እና ጊኒን (እ.ኤ.አ 1989–1993) ያጠቃልል ነበር። ቀጥሎም እ.ኤ.አ 1983–2002 በጅቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደርና በኢጋድ (IGAD) የኢትዮጵያ ተጠሪ ሆነው አገልግለዋል። እ.ኤ.አ ከ2002 ጀምሮ እስከ 2006 ድረሰ በፈረንሳይ (ሞሮኮን ጨምሮ) የኢትዮጵያ አምባሳደርና በዩኔስኮ (UNESCO) የኢትዮጵያ ተጠሪ ሆነው አገልግለዋል። እ.ኤ.አ ከ2006 ጀምሮ እስከ 2009 ድረስ በአፍሪካ ህብረት (AU) እና በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) የኢትዮጵያ ተጠሪ ሆነው ሀገራቸውን አገልግለዋል።

    ከሀያ ዓመታት በላይ በተለያዩ ሀገራትና ዓለማቀፋዊ ድርጅቶች የኢትዮጵያ አምባሳደርና ተጠሪ በመሆን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤትን ያገለገሉት አምባሳደር ሳህለወርቅ ዘውዴ እ.ኤ.አ በ2009 የተበባሩት መንግስታት ድርጅትን (ተመድ) በመቀላቀል የድርጅቱ በመካከለኛው አፍሪካ ሪፑብሊክ የተቀናጀ ሰላም ግንባታ መሪ (Head BINUCA) በመሆን ማገልገል ጀመሩ። ይህ አገልግሎታቸውም ወደ ሚቀጥለው ኃላፊነት አሸጋግሯቸው እ.ኤ.አ በ2011 ዓም የዚያን ጊዜ የተመድ ጠቅላይ-ጸሀፊ ባን ኪ-ሙን (Ban Ki-moon) አዲስ ለተቋቃመው በናይሮቢ የተመድ ጽህፈት ቤት (UNON) የመጀመሪያዋ ጠቅላይ-መሪ አድርገው ሾማቸው። በዚያም ለሰባት ዓመታት ካገለገሉ በኋላ እ.ኤ.አ በሰኔ ወር 2010 የአሁኑ የተመድ ጠቅላይ-ጸሀፊ አንቶንዮ ጉቴሬስ (António Guterres) አምባሳደር ሳህለወርቅ ዘውዴን በተመድ ጠቅላይ-መሪ ስር (Under-Secretary-General) የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተጠሪ (UN’s Special Representative to the AU) እና በአፍሪካ ህብረት ውስጥ የተመድ ጽህፈት ቤት ዋና ኃላፊ (Head of UNOAU) አድርገው ሾሟቸው እስካሁን ድረስ በዚሁ ሹመታቸው እያገለገሉ ይገኛሉ።

    አምባሳደር ሳህለወርቅ ዘውዴ ባለትዳርና የሁለት ወንድ ልጆች እናት ናቸው።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ሳህለወርቅ ዘውዴ


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ – የሕዝብ ተወካዮችና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች የጋራ የመክፈቻ ስነ-ሥርዓት በኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ (ዶ/ር) የተከፈተ ሲሆን፥ ፕሬዝዳንቱ በመክፈቻ ንግግራቸው በምክር ቤቶቹ በበጀት ዓመቱ ለማከናወን የታሰቡ ተግባራትን አንስተዋል።

    በንግግራቸው ካነሷቸው ነጥቦች መካከል ሀገሪቱ በሁለተኛው እድገት እና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ (GTP II) አሳካዋለሁ ያለቻቸውን ዕቅዶች በሀገሪቱ በተከሰተ ግጭት እና አለመረጋጋት ምክንያት ማሳካት አልተቻለም ብለዋል።

    ግጭቶች እና አለመረጋጋቶች በሀገሪቱ ሲከሰቱ ከጅምራቸው እንዲቆሙ የማድረግ ውስንነት እንደነበርም ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ አንስተዋል። ይህ ደግሞ የሀገሪቱን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ አደጋ ውስጥ ከቶታል። በቀጣይ ህልውናዋን ለማረጋገጥ የሚያስችል ወሳኝ የፖለቲካ ምዕራፍ ተጀምሯል ። በዚህ የለውጥ ሂደት የሕዝቡን ህልውና አደጋ ላይ የሚጥሉ ማናቸውንም እንቅስቃሴዎች የህግ የበላይነትን በሚያረጋግጥ መልኩ ህጋዊ እርምጃ ለመውሰድ ቁርጠኛ አቋም ተይዟል ብለዋል።

    ከቅርብ ወራት ጀምሮ በፖለቲካው ዘርፍ የታዩ ለውጦች ለወደፊት የሀገሪቱ የለውጥ ጉዞ ትልቅ ሚና ይጫወታል። በስደት ላይ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጋር የተደረገው ሰላማዊ ድርድር ትልቅ ለውጥ የታየበት የፖለቲካ እንቅስቃሴ ነበር። እንደ ዶክተር ሙላቱ ገለፃ ለዚህ ፖለቲካዊ መሻሻል ምክር ቤቱ ያፀደቀው የምህረት አዋጅ ትልቁን ሚና ተጫውቷልም ነው ያሉት። የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት በተደረገው ጅምር እንቅስቃሴ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ምሁራን፣ጦማሪ እና አክቲቪስቶች በነፃነት የመሥራት እድል ተፈጥሮላቸዋል።

    ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ በተቃርኖ ውስጥ የነበሩት ሁለቱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክረስቲያን ሲኖዶሶች ችግር ተፈትቶ ወደ አንድ እንዲመጡ መደረጉም የለውጡ አካል ነበር። ለረጅም ዓመታት አለመግባባት ውስጥ የነበሩት አትዮጵያ እና ኤርትራ መግባባታቸው በቀጠናው የነበረውን የድህነት እና ኋላቀርነት መገለጫ ማጥፋት ችሏል።

    ———————————————-

    ———————————————-

    በደቡብ ሱዳን ተቀናቃኝ ኃይሎች መካከል በተፈጠረ አለመግባባት በዜጎች ላይ ይደርስ የነበረውን ግፍ ኢትዮጵያ መታደግ ችላለች። ከሌሎች አጎራባች እና የውጭ ሀገራት ጋርም ጥብቅ የሆነ ወዳጅነት እንዲኖራት መደረጉ በአጭር ጊዜ ውስጥ የተመለከትነው የፖለቲካ ለውጥ ውጤት ነው ብለዋል ፕሬዝዳንቱ።

    ዶክተር ሙላቱ ተሾመ በመክፈቻ ንግግራቸው የዜጎችን ነፃነት እና መሰረታዊ መብቶች ከማስጠበቅ አንፃር የተሠራው ሥራ ውስን እንደነበር ተናግረዋል።

    በአሁኑ ወቅ የሕዝቡ የዴሞክራሲ እና የፖለቲካ ጥያቄዎች የጎለበተበት በመሆኑ መንግስት የፖለቲካ ማሻሻያ የሚያደርግበት ነው ። የተጀመረውን ለውጥ ለማስቀጠል መንግስት በበጀት ዓመቱ ልዩ ልዩ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ሰጥቶ ይሠራልም ብለዋል።

    አሁን በሀገሪቱ የተጋረጠው የሰላም መደፍረስ ሕዝቡን አደጋ ውስጥ አስገብቶታል። የህግ የበላይነትም ተጥሷል። ፕሬዝዳንቱ በመክፈቻ ንግግራቸው የዜጎችን በሰላም የመኖር መብት እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር መንግስት አስፈላጊውን እርምጃ እንዲወስድ አሳስበዋል። የመገናኛ ተቋማት በማንኛውም የመገናኛ ዘዴ ሀሳባቸውን በነፃነት የመግለፅ ሁኔታ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ትኩረት ሰጥቶ ይሠራል።

    ተከስቶ የነበረው ሁከት እና አለመረጋጋት በሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ላይ አሉታዊ ተፅእኖ አድርሷል።በስፋት እየታየ ያለውን የኢኮኖሚ አለመረጋጋት ለመቀነስ እና የኢኮኖሚ ምህዳሩን ለማስፋት በዚህ የበጀት ዓመት በተጨባጭ እንደሚሠራም ተናግረዋል። መንግስት የተረጋጋ እና ቀጣይነት ያለው ማክሮ ኢኮኖሚን ለማሳደግ ፅኑ አቋም እንዳለው አንስተዋል። ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን የጀመረችው ድርድር በዚህ ዓመት ተጠናክሮ ይቀጥላልም ብለዋል ፕሬዝዳንቱ።

    ከመክፈቻ ንግግሩ ለመረዳት እንደተቻለው የምሥራቅ አፍሪካ በይነ መንግስት (ኢጋድ) በማጠናከር እና ወደ ተግባር ገብቶ ቀጠናዊ አገልግሎቱን እንዲያሰፋ ኢትዮጵያ የበኩሏን ድርሻ ትወጣለች።

    ሀገራችን በርካታ አለማቀፍ የስብሰባ መድረክ አገልግሎት እየተካሄደባት በመሆኑ የቪዛ አገልግሎት እንዲሰጥ ይደረጋል። የሚሰጠው የቪዛ አገልግሎት ቀልጣፋ እንዲሆን እየተሠራ መሆኑን ፕሬዝዳንቱ አንስተዋል።

    የግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚ በቴክኖሎጂ እንዲታገዝ እንዲሁም የመስኖ እርሻን በማጠናከር የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ለማሳደግ ይሠራል።
    የትምህርት ጥራትን ለማሳደግ አዲሱን ፍኖተ-ካርታ መሰረት ያደረገ የሥርዓት ትምህርት ማሻሻያ የደረጋል። የሴቶች እና ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በያዝነው በጀት ዓመት የጤና ተቋማት ግንባታ እና ቁሳቁስ አቅርቦት ትኩረት ተሰጥቶት ይሠራል። አሁን የተፈጠረውን ለውጥ ተከትሎ በሥርዓት አልበኞች ምክንያት እየታዩ ያሉ መፈናቀሎችን ትኩረት ሰጥቶ መሥራት ያስፈልጋል ሲሉ ፕሬዝዳንት ዶክተር ሙላቱ ተሾመ በመክፈቻ ንግግራቸው አንስተዋል።

    ምንጭ፦ የደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መ የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

    ሙላቱ ተሾመ

Viewing 4 results - 1 through 4 (of 4 total)