Search Results for 'የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር'

Home Forums Search Search Results for 'የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር'

Viewing 15 results - 1 through 15 (of 19 total)
  • Author
    Search Results
  • Anonymous
    Inactive

    የቡራዩ የልዩ ተሰጥኦ እና ተውህቦ ማበልጸጊያ ኢንስቲትዩት ፕሮጀክት ግንባታ ደረጃ 84 በመቶ መድረሱ ተገለጸ

    አዲስ አበባ – በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እየተገነባ ያለውን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ የልዩ ተሰጥኦ እና ተውህቦ ማበልጸጊያ ኢንስቲትዩት /Innovation and Technology Talent Development Institute/ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ዘርፍ የፌደራልና የክልል ቢሮ አመራሮች ነሐሴ 8 ቀን 2012 ዓ.ም. ጎብኝተውታል። ከጉብኝቱ በተጨማሪም አመራሮቹ የአረንጓዴ አሻራቸውን በማዕከሉ ቅጥር ግቢም አኑረዋል።

    እንደ የኢኖቬሽን ልማትና ምርምር ዘርፍ ሚኒስቴር ዲኤታ ክቡር አቶ ሲሳይ ቶላ ፕሮጀክቱ ባለፉ ዓመታት በነበሩ ሀገራዊ ምክንያቶች መዘግየት አጋጥሞት ነበር። በአሁኑ ወቅት በተሻለ የአፈጻጸም ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ጠቁመው፥ በተጠናከረ አመራርና ድጋፍ በማጠናቀቅ በ2013 ዓ.ም. ሁለተኛ ሩብ ዓመት መጀመሪያ ወራት ሥራ ለማስጀመር እየተሠራ ነው ብለዋል።

    ማዕከሉ ሥራ ሲጀምር ለአካባቢው ማኀበረሰብ የሥራ ዕድል ከመፍጠሩ ባሻገር በሀገራችን የሚገኙ ባለተሰጥኦዎችን አሰባስቦ ተሰጥኦዋቸውን በማጎልበት ወደ ተጨባጭ ውጤት የሚቀይሩበት ስለሆነ፥ መላ ኢትዮጵያውያን እንዲደግፉትና እንዲሳተፉበት ጥሪ አቅርበዋል። ያለፉ ዓመታት በነበሩ ሀገራዊ ለውጥ ሂደቶች የተነሳ ያጋጠሙ መዘግየቶችን በቀሪ ወራት አካክሶ ሥራ ለማስጀመር የፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅም ተመድቦለታል።

    ክቡር አቶ ሲሳይ አክለውም ለዓመታት ያጋጠመ የመዘግየት ችግር ተካክሶ በሦስት ወራት ውስጥ አመርቂ የግንባታ ደረጃ ላይ ማድረስ ተችሏል። በቀጣይም በተሻለ ጥራትና ፍጥነት ተጠናቆ ሥራ እንዲጀምር ቅድመ ዝግጅቶች እየተደረጉና መሟላት የሚገባቸው ግብዓቶችን ከግንባታው ጎን ለጎን እየተሟሉ ይገኛል። ለስልጠናና ትምህርት እንዲሁም ተሰጥኦ ማፍለቅና ትግበራ የሚውሉ የቁሳቁስ እገዛና ድጋፍ ከልዩ ልዩ አካላት መገኘት ጀምሯል ያሉት ክቡር አቶ ሲሳይ፥ በቀጣይ የግሉ ዘርፍ፣ ሀገር-አቀፍና ዓለም-አቀፍ እርዳታ ለጋሽ ድርጅቶች፣ ልዩ ልዩ ተቋማት እና የመንግሥት አካላትን ትብብር እንዲያደርጉ እንጠይቃለን ብለዋል።

    የቡራዩ የልዩ ተሰጥኦ እና ተውህቦ ማበልጸጊያ ኢንስቲትዩት ሥራ ሲጀምር በየደረጃው ካሉ አመራሮች፣ መንግሥታዊ ካልሆኑ ተቋማትና ባለ ድርሻ አካላት ዘርፈ ብዙ ድጋፍ እንደሚጠበቅ አውስተው፥ ተቋሙ የታለመለትን ግብ እንዲያሳካና ዘላቂነት እንዲኖረው የአሠራር መመሪያዎችን፣ የትብብር ማዕቀፎችን፣ የሥርዓተ ትምህርት ዝግጅትን፣ የተውህቦና የክህሎት መለያ መስፈርቶችን የሚመለከቱ ጉዳዮችን ቀድሞ የማዘጋጀት ሥራ ከወዲሁ እየተሠራ ነው ብለዋል።

    በመጨረሻም ለዚህ ሀገራዊ ማዕከል መገንቢያ ቦታ በመስጠት፣ ባሳለፍናቸው ሁለት ዓመታት በነበሩ ሀገራዊ ክስተቶች ወቅት የተጀመሩ ግንባታዎችና ቁሳቁሶች ላይ ጉዳት እንዳይደርስ ጥበቃና እንክብካቤ ላደረጉ የቡራዩ ከተማ አስተዳደርና አካባቢዋ ነዋሪዎች ምስጋና አቅርበዋል። ባለተሰጥኦዎችም ወደፊት ወደተቋሙ መጥተው በሚኖራቸው ቆይታ አስፈላጊውን እገዛና እንክብካቤ ማግኘት የሚያስችላቸውን ቅድመ ዝግጅት ሁሉ ትብብራቸው እንዳይቋረጥ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

    ተቋሙን ሥራ ማስጀመር የሚያስችሉትን የግንባታ ሥራዎችን ቅድሚያ ሰጥቶ መሥራት እንዲቻል በተሰጠ አመራር እየተሠራ ነው ያሉት ደግሞ የግንባታ ሥራ ተቋራጩ ሥራ አስኪያጅ ኢ/ር መስፍን ባልቻ ናቸው። እንደ ኢ/ር መስፍን የቤተ መጻሕፍት፣ ቤተ ሙከራ፣ ወርክሾፖች፣ የመማሪያ ክፍል እና የማደሪያ ሕንጻዎችን በልዩ ትኩረት ተገንብተው ከ78% እስከ 90% የአፈጻጸም ደረጃዎች ማድረስ ተችሏል። በአሁኑ ወቅት ግንባታው ያለበት አማካይ የአፈጻጸም ደረጃ ከ84% በላይ ነው። ቀሪ የሲቪል ሥራዎችን በማጠናቀቅ የቁሳቁስ ገጠማና ሌሎች አስፈላጊ ግብዓቶችን በማቅረብ ለማጠናቀቅ እየተሠራ በመሆኑ በቀጣይ ሦስትና አራት ወራት ጊዜ ማጠናቀቅ ይቻላል ብለዋል።

    የቡራዩ የልዩ ተሰጥኦ እና ተውህቦ ማበልጸጊያ ኢንስቲትዩት ግንባታ ከሦስት ዓመት በፊት በኦሮሚያ ክልል በቡራዩ ከተማ አስተዳደር በተሰጠ አምስት ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ከ700 ሚሊዮን ብር በላይ በተያዘ የመንግሥት በጀት የተጀመረ ነው። ከመላው ኢትዮጵያ ከ8ኛ እስከ 12ኛ ክፍል እስከ 1000 ባለተሰጥኦዎችን መልምሎና ተቀብሎ ከመደበኛ ትምህርታቸው ጎን ለግን ተሰጥኦዋቸውን በማልማት፣ በማጎልበትና ወደ ተጨባጭ አምራችነት በመቀየር ለሀገራዊ ብልጽግና መሠረት መጣል የሚችል ተቋም መሆኑን መግለጻችን ይታወቃል።

    ምንጭ፦ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር

    የቡራዩ የልዩ ተሰጥኦ እና ተውህቦ ማበልጸጊያ ኢንስቲትዩት

    Anonymous
    Inactive

    72 ኪሎ ግራም የምትመዝነው ETRSS-1 ሳተላይት በቻይና መንግሥት ድጋፍና በኢትዮጵያ መንግሥት በጀት የተገነባች ሲሆን፥ ለግብርና፣ ለማዕድን ፍለጋ፣ ለአካባቢ ጥበቃ፣ ለአየር ንብረት ለውጥ ክትትል/ ምርምርና ለመሳሰሉት ጥቅም ላይ ትውላለች።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ኢትዮጵያ የመጀመሪያዋን የመሬት ምልከታ ሳተላይት ታህሳስ 10 ቀን 2012 ዓ.ም. (በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር) ላይ ከቻይና ዋና ከተማ ቤይጂንግ 400 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከሚገኘው የቻይና ሳተላይት ማስወንጨፊያ ጣቢያ ወደ ህዋ ትመጥቃለች። ጉዳዩን በማስመልከት የኢፌዴሪ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ር ኢንጂ.) እና የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ቴክኖሎጂ ኢንስቲቲዩት ጀነራል ዳይሬክተር ሰለሞን በላይ (ዶ/ር) ኅዳር 12 ቀን 2012 ዓም መግለጫ ሰጥተዋል። [ከአንድ ሳምንት በፊት ይህ ዜና በተዘገበበት ጊዜ ቀኑና ሰዓቱ ታህሳስ 7 ቀን 2012 ዓ.ም. ከጠዋቱ 12 ሰዓት ከ21 ደቂቃ ተብሎ የነበረ ሲሆን vኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ር ኢንጂ.) በትዊተር ገጻቸው ቀኑ ወደ ታህሳስ 10 ቀን 2012 ዓ.ም. መዛወሩን አስታውቀዋል]።

    ETRSS-1 የተሰኘችው ይህች ሳተላይት በቻይና መንግሥት ድጋፍና በኢትዮጵያ መንግሥት በጀት የተገነባች ሲሆን፥ ከቻይና መንግሥት የጠፈር ኤጀንሲ ጋር በትብብር የማምጠቅ ሥራው ይከናወናል። 72 ኪሎ ግራም (~159 ፓውንድ) የምትመዝነው ETRSS-1 ሳተላይት ለግብርና፣ ለማዕድን ፍለጋ፣ ለአካባቢ ጥበቃ፣ ለአየር ንብረት ለውጥ ክትትል/ ምርምርና ለመሳሰሉት ጥቅም ላይ ትውላለች።

    መግለጫ በሚሰጡበት ጊዜ፥ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ር ኢንጂ.) ኢትዮጵያ የመጀመሪዋን ሳተላይት ለማምጠቅ ዝግጅቷን ማጠናቀቋ ወሳኝ ጊዜ ላይ እንደምትገኝ ማሳያ ነው ብለዋል። የሳተላይቷ ቁጥጥር ሙሉ ለሙሉ በኢትዮጵያ እና በኢትዮጵያውያን የዘርፉ ባለሙያዎች የሚከናወን እንደሚሆን ተናግረዋል። ይህንን ለማድረግም ከአዲስ አበባ ከተማ ወጣ ብሎ በተቋቋመው እንጦጦ ኦብዘርቫቶሪና የምርምር ማዕከል (Entoto Observatory and Research Center) ቅጥር ግቢ ውስጥ የመቆጣጠሪያ ጣቢያ ግንባታው ተጠናቅቋል። ይህ ጣቢያ የሳተላይቷ ደኅንነት ክትትል የሚደረግበትና ከሳተላይቷ የሚገኙ መረጃዎች የሚሰበሰቡበት ነው።

    የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ቴክኖሎጂ ኢንስቲቲዩት ጀነራል ዳይሬክተር ሰለሞን በላይ (ዶ/ር) በበኩላቸው በሳተላይቷ ግንባታ ከንድፍ ጀምሮ ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች መሳተፋቸውንና በሀገር ውስጥ ከሚገኙም ሆነ ከውጭ አገራት ከመጡ ምሁራን እና ባለሙያዎች መካከል የዕውቀትና የቴክኖሎጂ ሽግግር የተገኘበት መሆኑን ተናግረዋል።

    ETRSS-1 ሳተላይት  ከተወነጨፈች በግማሽ ሰዓት ውስጥ ከመሬት 700 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኝ ህዋ ላይ ቦታዋን ትይዛለች። የሳተላይቷ ግንባታ 2008 ዓ.ም. ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በነበሩበት ጊዜ የተፈረመና 2009 ዓ.ም. ላይ የተጀመረ ነው።

    የሳተላይቷ መምጠቅ ኢትዮጵያ ለሳተላይት ምስል ግዢ በዓመት የምታወጣውን ከ350 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የሚያስቀር ነው።

    ምንጭ፦ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ETRSS-1 satellite

    Anonymous
    Inactive

    ሴቶች በቴክኖሎጂ ዘርፍ የሥራ ፈጣሪ እንዲሆኑ ለማድረግ ታሳቢ ያደረገው የሶፍትዌር ማበልፀግና የሥራ ፈጠራ ስልጠና በይፋ ተጀመረ።
    —–
    የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርና እንጦጦ ፌሎሺፕ በጋር በመተባበር ባዘጋጁት በዚህ ስልጠና ከተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተወጣጡ 25 ሴቶች ይሳተፋሉ።

    ስልጠናው ከካናዳ በመጡ የዘርፉ ምሁራኖች የሚሰጥ ሲሆን ከስልጠና በኋላ ወደ ሥራ መግባት የሚያስችላቸውን እውቀት ይዘው እንዲወጡና ሥራ እንዲፈጥሩ ይደረጋል።

    የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ዳይሬክተር ወ/ሮ ኤልሳቤት ገብረሥላሴ የዓለምን ኢኮኖሚ እየመራ ባለው የቴክሎጂ ዘርፍ ውስጥ ሴቶች ጉልህ ሚና እንዲጫወቱ ሚኒስቴሩ እየሠራ መሆኑን ተናግረዋል።

    የእንጦጦ ፌሎውሺፕ መስራችና ሥራ አስኪያጅ ዌንጌላዊት ተካ ፕሮግራሙ አጋጣሚውን በቀላሉ ማግኘት የማይችሉ ሴቶችን በሶፍትዌር ማብልፅግና ሥራ ፈጠራ ላይ ተሰማርተው ራሳቸውን እና ሀገራቸውን እንዲጠቅሙ ለማድግ የተዘረጋ መሆኑን ተናግረዋል።

    3ወር በሚፈጀው በዚህ ስልጠና የሚሳተፉ ሴቶች አብዛኞቹ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ኑሯቸውን የሚመሩ ናቸው።
    በመክፈቻ ሥነ-ስርዓቱ ላይ አምባሳደር ገነት ዘውዴ ልምዳቸውን ለሰልጣኖቹ አካፍለዋል።

    ምንጭ፦ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ (ኢፌዴሪ) የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አማካኝነት የተሠራው ለእርሻ አገልግሎት የሚውል ባለሞተር ማረሻ ተመረቀ።

    የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ጌታሁን መኩሪያን (ዶ/ር ኢንጂ.) ጨምሮ የሚኒስቴሩ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና የሮዳ ኢንጂነሪን ሠራተኞች በተገኙበት ተመርቋል።

    ከዚህ ቀደም ከውጭ ሀገራት የአርሶ አደሩን ድካም ያቃልላሉ ተብለው የተገዙ ዘመናዊ የማረሻ መሣሪያዎች ከሀገራችን ድንጋያማ መሬት ጋር ባለመስማማታቸው የሚጠበቅባቸውን ጥቅም ሳይሰጡ በ አጭር ጊዜ ውስጥ ከጥቅም ውጭ ይውላሉ። ይህ በኢትዮፕያውያን ዲዛይን ተደርጎ የተሠራው ባለሞተር ማረሻ ግን ለሀገራችን መሬት ተስማሚ እንዲሆን ተደርጎ የተሠራ ነው።

    ማረሻው ከተገጠመለት ሞተር ውጪ በኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች የተሠራ በመሆኑ ለጥገና፣ ማሻሻያ ለማድረግና ተጨማሪ ጥቅሞችን ለመጨመር የተመቸ መሆኑን የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

    በቀጣይ በዚሁ ባለሞተር ማረሻ ላይ አርሶ አደሩ ተቀምጦ የሚያርስበት፣ መሬቱን ለመጎልጎል የሚያስችል፣ ምርቱን ማረሻው ላይ ለመጫን የሚያስችሉ አዳዲስ ግልጋሎቶችን እንዲሰጥ ተደርጎ እንደሚዘምን የሮዳ ኢንጂነሪን ባለቤት አቶ አክሊሉ አባተ ተናግረዋል። ማጨድና መውቃት፣ እንዲሁም ምርት መሰብሰብ የሚችል መጎታችም በቀጣይ እንደሚሠራለት ተጠቁሟል። አርሶ አደሩ በቀላሉ ነዳጅ ማግኘት እንዲችል ከእፀዋት ተረፈ ምርት መሠራት የሚችል ባዮፊዩል (biofuel) እንዲጠቀምም ይደረጋል።

    አርሶ አደሮቻንን እስከ ዛሬ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ አላደርግናቸውም ያሉት ሚኒስትሩ ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ር ኢንጂ.) በቀጣይ ችግሮቻቸውን የሚያቃልሉ ቴክኖሎጂዎችን ማላመድና መፍጠር ላይ በትኩረት እንሠራለን ብለዋል። አክለውም፥ ባለሞተር ማረሻውን አርሶ አደሮች የመግዛት አቅም ኖሯቸው እንዲጠቀሙበት ለማድረግም ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በትብብር ይሠራል ነው ያሉት።

    ባለሞተር ማረሻውን ከማዘመንና ጠጨማሪ አገልግሎቶችን አንዲያረክት ማሻሻያዎችን ከማድረግ በተጨማሪ ዋጋውም ከጥንድ በሬዎች መግዣ ባነሰ ዋጋ አርሶ አደሩ እጅ እንዲገባ ጥረት ይደረጋል ተብሏል። ባለሞተር ማረሻው በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርና በሮዳ ኢንጂነሪንግ ትብብር የተሠራ ነው።

    ምንጭ፦ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    ባለሞተር ማረሻ


    Semonegna
    Keymaster

    የወልድያ ዩኒቨርሲቲ ከስዊድኑ ጎተንበርግ ዩኒቨርሲቲ (The University of Gothenburg) ጋር በትብብር የቅርስ ጥበቃና እንክብካቤን የሚመለከት ትምህርት ለመስጠት የሚያስችላቸው የመግባቢያ ሰነድ ይፈርማሉ።

    በቅርስ ጥበቃና እንክብካቤ መስክ በሀገራችን ያለውን የባለሙያ እጥረት የሚቀርፍ መነሻ ሀሳብ ከስዊድን ጎተንበርግ ዩኒቨርሲቲ የመጡ መምህራን ለክቡራን ሚንስትሮች ገለፃ አድርገዋል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ሀገራችን ኢትዮጵያ ከስዊድን መንግስት ጋር ያላት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች ረጅም ዓመታትን ያስቆጠረ መሆኑ በተለይ በኪነ-ሕንፃ ትህምርት ዘርፍ ያላቸው ልምዶች ታሪካዊና ጠናካራ ግንኙነት የተፈጠረበት መሆኑ ብዙ ይወሳል።

    በመሆኑም የወልድያ ዩኒቨርሲቲ ስዊድን ውስጥ በትልቅነቱ ሁለተኛ ከሆነው ጎተንበርግ ዩኒቨርሲቲ (The University of Gothenburg) ጋር በትብብር ለመክፈት ያሰበው የቅርስ ጥበቃና እንክብካቤ እውን እንዲሆንና የቅርስ ጥገና ተግባራዊ ትምህርት በወልዲያ ዩኒቨርሲቲ እንዲሰጥ ታስቦ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በኩል ቅድመ ዝግጅት መጀመሩን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አርኪዮሎጂ (archeology) ትምህርት ክፍል መምህር የሆኑት ዶ/ር መንግስቱ ጎበዜ፥ የታሰበው የትምህርት መርሀግብር ለክቡራን ሚኒስትሮች (ለፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ፥ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ እና ለወ/ሮ ብዙነሽ መሠረት፥ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር የባህል ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ) የሥልጠናውን ዓላማና ግብ የሚያግባባ ገለፃና ትውውቅ አድርገውላቸዋል።

    በመቀጠልም በልዑካኑ በስዊድን ጎተንበርግ ዩኒቨርሲቲ በኩል የመጡት መምህራን ያላቸውን ዝግጁነትና ተቋማዊ አደረጃጀት እንዲሁም የገጠሩ ሕዝብ ባህላዊ ሀብቱን እየተወ ወደ ከተማ ከሚኮበልል እዛው በቅርሱ ተጠቃሚ የሚሆንበት መሠረት የጣለ ልምድ መኖሩን የሚያብራራ ገለጻ በ‘Bosse Lagerqvist’ እና ‘Lars Runnquist’ የልዑኩን ቡድ ኑን በመወከል ገለፃ አደርገዋል። ተመራማሪ ፕሮፌሰሮች በነሱ በኩል ተግባራዊ ትምህርቱ ከቁሰቁስ አቅርቦት እንደሚደገፍ ጭምር በትብብር የሚሠራበት ሁኔታ ለመፍጠር በቻርትና ስዕላዊ መግለጫዎች ማብራሪያ አድርገዋል።

    ሰባት ዩኒቨርሲቲዎች፣ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር እና STEMpower ጋር የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ

    ለመርሀግሩ ማጠቃለያ ክቡራን ሚኒስትሮችም በበኩላቸው በሁለቱም ሀገራት መካከል ያለውን የረጅም ጊዜ ታሪካዊ ግንኙነት መልካም በሚባል ደረጃ የደረሰ መሆኑን በማመስገን፥ ያቀረባችሁት ሀሳብ የሚጠቅመንና እንደኢትዮጵያ በቅርስ ጥበቃና እንክብካቤ መስክ የሚሰጡ ትምህርቶች በንድፈ-ሀሳብ ብቻ በመሆኑ በትብብር ስለምንሠራው ብዙ ባለሙያዎችን የምናፈራበት ዕድል ይፈጥራል ብለዋል።

    የትምህርት ማስተማሪያ መርሀግብሩ የሁለተኛ ዲግሪ ለመስጠት የሚያበቃ ሲሆን፥ ለዚህ የመግባቢያ ሰነድ በቅርብ ጊዜ እንደሚፈረም እንዲሁም ተግባራዊ ትምህርቱ የሚሰጥበት ቦታ አንድ ካምፓስ በላሊበላ ቅርጫፍ የሚዘጋጅበት ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል።

    ምንጭ፦ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የወልድያ ዩኒቨርሲቲ


    Semonegna
    Keymaster

    ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ዳያስፖራዎች ልዑካን ቡድን አባላት የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ትውልደ ኢትዮጵያውያን ሀገራቸውን በሙያቸው እንዲያግዙ ጥሪ ማቅረባቸውን ተክተሎ የመጡ ናቸው።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– በኢትዮጵያ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሲካሄድ የቆየው መንግስት ቴክኖሎጂ ለመጠቀም ያለውን ዝግጁነት የሚለይና ለችግሮች የመፍትሄ አቅጣጫ የሚያስቀምጥ አውደ-ጥናት ተጠናቀቀ።

    በአውደ ጥናቱ የመንግስት አግልግሎት አሰጣጥ፣ ቴክኖሎጂ ለመጠቀም ያለው ዝግጁነት፣ የፋይናንስ አስተዳደር ስርዓት ክፍተት ተለይተውበታል – ሚኒስቴሩ እንደዘገበው።

    የጤና አስተዳደር፣ የታክስ አሰባሰብ ስርዓት፣ የመረጃ ግንኙነት (ኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን) ቴክኖሎጂ ደኅንነት፣ በባንክ አገልግሎት፣ በኢንሹራንስ አገልግሎት፣ ትምህርት ሚኒስቴር፣ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ በኦዲት አገልግሎት፣ የአደጋ መከላከልና ዝግጁነት፣ የውሃ አወጋገድ ላይ ክፍተቶች ተለይተዋል።

    አሜሪካ ውስጥ ቨርጂንያ ኢንተርናሽናል ዩኒቨርሲቲ (Virginia International University; Fairfax, VA) መምህር በሆኑት ዶ/ር ተፈራ በየነ የተመራው ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች ልዑክ ክፍተቶቹን ከለዩ በኋላ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል።

    ከ7ሺህ 800 በላይ አዳዲስ አነስተኛና መካከለኛ የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪዎች በመላው አገሪቱ ሊቋቋሙ ነው

    ባለሙያዎቹ በኢንሹራንስ፣ በህክምና ቴክኖሎጂ፣ በዲፕሎማሲ፣ በኢንፎርሜሽን ኮሙኑኬሽን ቴክኖሎጂ ዘርፍ በአሜሪካን ሀገር በተለያዩ መሥሪያ ቤቶች ከፍተኛ ልምድ ያካበቱ ኢትዮጵያዊያን ናቸው።

    ሚኒስትሮች፣ ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የፋይናንስ ዳይሬክተሮች እና ሌሎችም ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸው አካላት ከቡድኑ ጋር ለ1 ሳምንት ክፍተቶችን እና ጉድለቶችን የመለየት ሥራ ሲሠሩ ቆይተዋል።

    የሚመለከታቸው አካላት በየዘርፉ የሚደረጉ ማስተካከያዎችን በኃላፊነት ወስደው ወደ ተግባር የመቀየር ኃላፊነት ተሰጥቷቸዋል። በማጠቃለያው ላይ፥ ልዑካኑ የኢትዮጵያ መንግስት ወይም የሚመለከተው መንግስታዊ ተቋም ዕድሉን ከሰጠን የሀገራችንን ችግር ለመፍታት በቂ አቅም አለን ብለዋል። ወደፊትም በማንኛውም መልኩ ሀገራቸውን ለማገዝ ቃል ገብተዋል።

    የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታዎች ሹመቴ ግዛው (ዶ/ር) እና ጀማል በከር ልዑካኑ ሀገራቸውን ለመረዳት ያላቸውን ቁርጠኝነት በማድነቅ ምስጋና አቅርበዋል።

    የልዑካን ቡድኑ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ትውልደ ኢትዮጵያውያን ሀገራቸውን በሙያቸው እንዲያግዙ ጥሪ ማቅረባቸውን ተክተሎ የመጡ ናቸው።

    ምንጭ፦ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ትውልደ ኢትዮጵያዊያን


    Semonegna
    Keymaster

    የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የሴቶችን ጫና በሚያቀልሉ ቴክኖሎጂዎች ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየመከረ መሆኑን የሚኒስቴሩ የሴቶች፤ ህፃናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ኤልሳቤጥ ገብረሥላሴ አስታውቀዋል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር በ7 ክልሎች ውስጥ በቴክኖሎጂ ውጤቶች ሊደገፉ የሚችሉ ሴቶች ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደሩ ያሉ ሥራዎችን በጥናት ለይቷል።

    ችግሮቹ የተለዩት በአፋር፤ በቤኒሻንጉል፤ በጋምቤላ፤ በደቡብ፤ በአማራ፤ በትግራይና በሶማሌ ክልል በተጠናው ጥናት መሠረት መሆኑን ሚኒስቴሩ አስታውቋል።

    በፀሐይ ኃይል የሚሠራ የምግብ ማብሰያ፤ በሬ ለምኔ ዘመናዊ ማረሻ እና የቆጮ መፋቂያ ማሽን በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ሥራ እንደሚገቡ ተገልጿል። ዘመናዊ የበቆሎ መፈልፈያና የአፋ አሊ (የአፋር ቤት) መሥሪያ በመካከለኛ ጊዜ ወደ ሥራ ለማስገባት የታቀደ ሲሆን በመስመር መዝሪያ እና ከጉድጓድ ውሃ ማውጫ መሣሪያ ደግሞ በረጅም ጊዜ ወደ ሥራ ለማስገባት በዕቅድ ተይዟል።

    የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የሴቶችን ጫና በሚያቀልሉ ቴክኖሎጂዎች ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየመከረ ነው። የሚኒሰቴሩ የሴቶች፤ ህፃናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ኤልሳቤጥ ገብረሥላሴ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የሴቶችን የሥራ ጫና የሚያቃልሉና ምርታማ የሚያደርጉ ቴክኖሎጂዎች ላይ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል። ለስኬታማነቱ የሚመለከታቸው ሁሉ ድጋፋቸውን እንዲያደርጉም ዳይሬክተሯ ጥሪ አቅርበዋል።

    ምንጭ፦ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ 
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    የሴቶችን ጫና የሚያቃልሉ የቴክኖሎጂ ውጤቶች


    Semonegna
    Keymaster

    የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የጥናትና ምርምር ማኅበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዚዳንት ዶ/ር አልማዝ አፈራ በዚህ ፕሮጀክት የተሳተፉ ተመራማሪዎችን ያሉትን ተግዳሮቶች ተቋቁመው ለዚህ በመብቃታቸው ምስጋና ቸረዋቸዋል።

    ደብረ ብርሃን (ሰሞነኛ)– የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የጥናትና ምርምር ማኅበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት ከኢፌዴሪ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታና ግድም ወረዳ ይምሎ ቀበሌ በተቀናጀ የአሳ፣ የዶሮ፣ የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶች ላይ ሲያካሂድ የቆየውን የምርምር ፕሮጀክት አጠናቆ ለዞኑ አስተዳደርና ለአካበቢው ማኅበረሰብ አስረከበ።

    በርክክብ ሥነ-ስርዓቱ ወቅት የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ መምህርና መሪ ተመራማሪ ዶ/ር ገዛኸኝ ደግፌ እንደተናገሩት ምርምሩ በትንሽ ቦታ አሳን፣ ዶሮንና አትክልትን አቀናጅቶ ማልማት የሚያስችል የቴክኖሎጅ ዕውቀትን በመጠቀም የአሳ፣ የዶሮና የአትክልት ልማቱን አቀናጅቶ መሥራት እንደሚቻል ነው ብለዋል። በዚህም የዶሮ ኩስን ለአሳዎች ምግብ እንዲውል እንዲሁም “vermicompost” ቆሻሻን ወደ ጠቃሚ ነገርነትና ማዳበሪያነት የሚቀይሩ ትሎችን ለዶሮዎችና ለአሳ ምግብነት እንዲውል የሚያስችል እንደሆነ አብራርተዋል።

    በምስራቅ ጎጃም ዞን ስንዴ አምራች ወረዳዎች ለገበሬዎች የቀረቡላቸው ኮምባይነሮች በምርታቸው ላይ ጉልህ አስተዋጽዖ እያደረጉ ነው

    አቶ ተፈራ ወንድማገኘሁ የሰሜን ሸዋ ዞን ዋና አስተዳደሪ እንዳሉት ይህ ለምርቃት የበቃው የምርምር ሥራ የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በዞኑ ከሚያከናውናቸው ምርምሮች አንዱ ሲሆን ፣ በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ፈጻሚነትና በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የገንዘብ ድጋፍ የተሠራ መሆኑን ተናግረዋል። ዋና አስተዳዳሪው አክለው እንዳስታወቁት ይህንን ምርምር በዞኑ በሚገኙ ወረዳዎችና ቀበሌዎች ለማስፋፋት ትልቅ ኃላፊነትና አደራ የተጣለባቸው መሆኑን አውስተው ለተግባራዊነቱም እንደሚሠሩ ተናግረዋል።

    የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ኢንጅነር ጌታሁን መኩሪያ ባደረጉት ንግግር ሚኒስቴር መሥሪያ ቤታቸው ከሚደግፋቸው በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች በሚባል ደረጃ ከ60 በላይ ምርምሮች መካከል የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ አንዱና ውጤታማው በመሆኑ ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ በሚችሉ ትናንሽ ፕሮጀክቶች በመደገፍ የሀገራችንን ልማት ማረጋገጥ ይኖርብናል ብለዋል። ይህን ፕሮጀከት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ለሁሉም ዞኖችና ወረዳዎች እንዲተላለፍ ማኑዋልና ስታንዳርድ ተዘጋጅቷል። የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳደርም በአማራ ክልል ለሚገኙ ሁሉም ዞኖች እንዲያደርስ ኃላፊነት የተሰጣቸው ሲሆን በቀጣይ በሀገር አቀፍ ደረጃ እንዲሰራጭ አናደርጋለን ብለዋል።

    ዶ/ር አልማዝ አፈራ የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የጥናትና ምርምር ማኅበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዚዳንት በበኩላቸው በዚህ ፕሮጀክት የተሳተፉ ተመራማሪዎችን ያሉትን ተግዳሮቶች ተቋቁመው ለዚህ በመብቃታቸው ምስጋና ቸረዋቸዋል። እንደ ፕሬዚዳንቷ ገለፃ፥ በሀገራችን እስከ ሁለት ሚሊዮን የሚደርሱ ሥራ-አጥ ወጣቶች መኖራቸው የሚታወቅ ሲሆን እንደነዚህ ዓይነት የምርምር ሥራዎች ደግሞ ወጣቶችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚ በማድረግ ሚናቸው የጎላ ነው ብለዋል። ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲም ብዙ የምርምር ውጤቶች ያሉት ሲሆን እነዚህን ምርምሮች ወደ ፕሮጀክት መቀየር የሚያስችል ተሞክሮ ስለሆነ ይህ ትልቅ ማሳያ ይሆነናል ብለዋል። በመጨረሻም የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርንና የኤፍራታና ግድም ወረዳ አስተዳደርን ላደረጉት ድጋፍና ትብብር ምስጋና አቅርበዋል።

    ምንጭ፦ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የተቀናጀ የግብርና ምርምር ፕሮጀክት


    Anonymous
    Inactive

    ቡናን ከምርት እስከ ውጭ ገበያ ያለውን ሂደት በቴክኖሎጂ ለማገዝ ስምምነት ተፈረመ
    —–

    ‹‹ቲታንስ ዲ አፍሪቅ›› በተለያዩ የቴክኖሎጂ ዘርፎች በአፍሪካ ውስጥ የሚሰራ ድርጅት ሲሆን ኢትዮጵያ ውስጥ ቡናን ከምርት ጀምሮ እስከ ውጭ ገበያ ያለውን ሂደት በቴክኖሎጂ ለማገዝ ተስማምቷል፡፡

    የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ‹‹ከቲታንስ ዲ አፍሪቅ›› ጋር ቴክኖሎጂን የሚጠቀም የግብርና ስራ ላይ በጋራ ለመስራት ተስማሙ፡፡

    በዚህ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የግብርና ስራ ለበርካታ ወጣቶች የስራ እድል ለመፍጠር እቅድ እንደተያዘም ተገልጿል፡፡

    ኢትዮጵያ የቡና አምራች ሀገር ብትሆንም ዘርፉ በቴክኖሎጂ ባለመደገፉ እና እሴት መጨመር ላይ ትኩረት ባለመደረጉ ከዘርፉ የሚገባትን ያክል ተጠቃሚ አይደለችም፡፡

    ይህንን ችግር ለመቅረፍ ዘርፉን በቴክኖሎጂ መደገፍ አስፈላጊ በመሆኑ ነው ድርጅቱ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በጋራ ለመስራት የተስማማው፡፡

    ስምምነቱን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ዴኤታ ዶክተር ሹመቴ ግዛው እና የቲታንስ ዲ አፍሪቅ ማኒጂንግ ዳይሬክተር ዶክተር ጊልበርት ሳጊያ ተፈራርመዋል፡፡

    ቴክኖሎጂ በሁሉም ዘርፍ የሚገባ በመሆኑ የትኛውንም ስራ በቴክኖሎጂ ለመደገፍ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ተቋማዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት እየሰራ መሆኑን ሚኒስቴር ዴኤታው ተናግረዋል፡፡

    ‹‹ቲታንስ ዲ አፍሪቅ›› አፍሪካ ውስጥ በቴክኖሎጂ የበለፀገ ማህበረሰብ ለመገንባት እየሰራ ያለ ድርጅት ነው፡፡

    ምንጭ፡- የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– በ”ለሁሉ” የተለያዩ የክፍያ ማዕከላት የውሃ፣ መብራትና ስልክ ክፍያ ለመፈጸም ሄደው መጉላላት እየገጠማቸው መሆኑን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ነዋሪች ገለጹ።

    በአዲስ አበባ 34 የሚሆኑ የውሃ፣ የመብራት፣ የስልክና ሌሎች የአገልግሎት መስጫ “ለሁሉ” ማዕከላት ያሉ ቢሆንም ሰሞኑን በአገልግሎት ፈላጊዎች ወረፋ ተጨናንቀዋል። ተገልጋዮቹ የወርሃዊ ክፍያቸውን ለመፈጸም ረዥም ሰልፍ በመያዝ እንግልትና መስተጓጎል እየገጠማቸው መሆኑንም ገልፀዋል።

    የኢዜአ ጋዜጠኛም ከ”ለሁሉ” አገልግሎት መስጫ ማዕከላት መካከል በፒያሳ ጊዮርጊስ፣ በአራት ኪሎና ለገሃር አካባቢ በሚገኙ የክፍያ ማዕከላት ተዘዋውሮ ችግሩ መኖሩን ተመልክቷል።

    አራት ኪሎ በሚገኘው የክፍያ ማዕከል የተገኙት ወይዘሮ አስካለ ኃይሌ እንደሚሉት ከተወሰኑ ወራት ወዲህ በከተማዋ ባሉ ብዙ የክፍያ ማዕከላት ወረፋና መጉላላት ተባብሷል።

    VIDEO: The newly established i-Pro Mobile Assembly Company in Dessie struggling to get building

    በአራት ኪሎ የ”ለሁሉ” የክፍያ ማዕከል ክፍያ ለመፈጸም የተገኙት ወ/ሮ ኤልሳቤት ግርማም በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ ከፍተኛ ቅሬታ እንዳላቸው ነግረውናል።

    በአራዳ ክፍለ ከተማ ኢትዮ-ቴሌኮም ጊቢ ውስጥ በሚገኘው “ለሁሉ” የክፍያ ማዕከል ክፍያ ለመፈጸም የተገኙ ተገልጋዮችም በመስተጓጎላቸው ምሬታቸውን ገልፀውልናል።

    ከጉለሌ ክፍለ ከተማ የመጡት ወ/ሮ ብስኩት ይጥና እና አቶ መስፍን ተገነውም የውሃና መብራት ክፍያ ለመፈጸም ማልደው ቢገኙም አገልግሎቱን ማግኘት እንዳልቻሉ ገልፀውልናል።

    አገልግሎት የሚሰጡ ሰራተኞች በቁጥር ጥቂት መሆናቸውና “ሲስተም የለም በማለት”፣ ከፍተኛ መጨናነቅ እየተፈጠረ መሆኑንም ጭምር ተገልጋዮቹ ገልፀዋል።

    በመሆኑም “ክፍያውን የሚያስፈጽሙልን አካላት ከቴክኖሎጂ ጋር በተጣመረ ቅልጥፍና ሊያስተናግዱን ይገባል” በማለትም ቅሬታቸውን አሰምተዋል።

    ካነጋገርናቸው ተገልጋዮች መካከል ለሦስት ቀናትና ከዚያ በላይ ክፍያ ለመፈጸም እንደተመላለሱ ጠቅሰው ለችግሩ የሚመለከተው አካል አፋጣኝ መፍትሄ እንዲያበጅላቸው የጠየቁም አሉ።

    በፒያሳ ጊዮርጊስ አካባቢ የሚገኘው “ለሁሉ” ማዕከል ኃላፊ ወ/ሮ ጽዮን ዮሃንስን እንዲሁም የአራት ኪሎ ክፍያ ማዕከል ሃላፊ ወ/ሮ ወይንሸት ገብረጻዲቅ ችግሩ መኖሩን አምነዋል። ወ/ሮ ጽዮን እንደሚሉት ችግሩ የተፈጠረው ሌላኛው የአራዳ የክፍያ ማዕከል ዝግ በመሆኑ ነው።

    እንደ ወ/ሮ ወይንሸት ገለፃ ህብረተሰቡ በጊዜ የመክፈል ልማድ ስለሌለው ወደ መጨረሻው ቀን ክፍያው በሚፈጽምበት ወቅት አንዲህ ያለው መጨናነቅ ይፈጠራል ብለዋል።

    ኢዜአ በ”ለሁሉ” የክፍያ መፈጸሚያ ዋና መሥሪያ ቤት በመገኘት ከኃላፊዎች ምላሽ ለማግኘት ቢሞክርም “ከቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ሚኒስቴር ፍቃድ ያስፈልጋል” በማለት መላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    ለሁሉ ክፍያ


    Anonymous
    Inactive

    ኢትዮጵያ የኤሌክትሮኒክስ ግብይትን ለመዘርጋት የጀመረችውን ስራ ዴንማርክ እንድታግዝ ጠየቀች፡፡
    —–

    በኢትዮጵያ የዴንማርክ አምባሳደር ካሪን ፖውልሰን ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የስራ ሃላፊዎች ጋር በግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያና በኤሌክትሮኖክስ ግብይት ዙሪያ ምክክር አድርገዋል፡፡

    የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ር ኢንጂ.) ኢትዮጵያ የጀመረችውን የኤሌክትሮኒክስ ግብይት ዴንማርክ እንድታግዝና ቴክሎጂን በሚጠቀም የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ዘረፍ እንድትሳተፍ ጠይቃዋል፡፡

    1ቢሊየን ዶላር ገደማ የውጭ ምንዛሬ የሚያስገኘውን ቡና እሴት ጨምሮ በኤሌክትሮኖክስ ግብይት ወደ ገበያ ማቅረብ ቢጀመር ገቢውን በ4 እና 5 እጥፍ ማሳደግ እንደሚቻል ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡

    የኤሌክትሮኒክስ ግብይትን በኢትዮጵያ ለመጀመር የአለም አቀፉ ፖስታል ድርጅት ቴክኒካል ኮሚቴ ጥናት መጀመሩ ይታወሳል፡፡

    የኢትዮጵያ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር

    Anonymous
    Inactive

    የኤሌክትሮኒክስ ግብይት በኢትዮጵያ ለመጀመር የአለም አቀፉ የፖስታ ድርጅት ቲክኒካል ኮሚቴ ጥናት ጀመረ፡፡
    —–

    አፍሪካን በተለያዩ ቀጠናዎች ከፍሎ የኤሌክትሮኒክስ ግብይት ለመጀመር እየሰራ የሚገኘው ዓለማቀፍ የፖስታ ኅብረት (Universal Postal Union) አጥኚ ቡድኑን ወደ ኢትዮጵያ የላከው ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በተፈራረመው ስምምነት መሰረት ነው፡፡

    ቡድኑ የኢትዮጵያ ዝግጁነት ከፖሊሲ፣ ከመሰረተ ልማትና ከኢ-ታክስ አኳያ፤ ኢትዮጵያ ስርዓቱን ለመዘርጋት ምን ማድረግ አለባት፣ ትግበራውን በምን መልኩ መከናወን ይኖርበታል የሚሉትንና የመሳሰሉትን ጉዳዮች ያጠናል፡፡

    የግብይት ስርዓትን ለማዘመን፣ ገዢና ሻጭን በቀጥታ ለማገናኘት፣ ቀጠናዊ ትስስር ለመፍጠር፣ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን ሃብት ለማሳደግ ትልቅ ጠቀሜታ ይኖረዋል ተብሎ የሚታሰበው የኤሌክትሮኒክስ ግብይት ስርዓት በኢትዮጵያ በቅርቡ ተግባራዊ ለማድረግ ርብርብ እንደሚደረግ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ር ኢንጂ.) ተናግረዋል፡፡

    የአለም አቀፉ የፖስታል ድርጅት የምስራቅ አፍሪካ ማዕከሉን ኢትዮጵያ ውስጥ ለመገንባት ማቀዱ ይታወሳል፡፡

    በ2017 በአፍሪካ በኤሌክትሮኒክስ ግብይት ከ85 ቢሊየን እስከ 100 ቢሊየን ዶላር የገበያ ድርሻ ይይዛል ተብሎ ይገመታል፡፡

    የኢትዮጵያ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– የአሜሪካ ኢምባሲ 2ኛውን ‹‹SolveIT›› የተሰኘ ሀገር አቀፍ የፈጠራ ውድድርን የኢዲስ አበባ ከተማን በይፋ አስጀመረ። ኢምባሲው ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር፣ ከጃፓን ዓለማቀፋዊ ኮኦፐሬቲቭ ኤጀንሲ (Japan International Cooperation Agency – JICA) እና ከአይኮግ ላብስ (iCog Labs) ጋር በመተባር ነው ውድድሩን ይፋ ያደረገው።

    ፕሮጀክቱ በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ 15 ከተሞች የሚካሄድ ሲሆን ቴክኖሎጂ ነክ የፈጠራ ሥራዎች ላይ ትኩረቱን ያደረገ ነው።
    ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂ ነክ የፈጠራ ሰራዎች ያሏቸው ወጣቶች የሚሳተፉበት ይህ ውድድር የፈጠራ ባላሙያዎቹ ሥራዎቻቸውን ሊያዳብር የሚችል ስልጠና በየከተሞቹ ይሰጣቸዋል።

    SolveIT ሀገር አቀፍ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ውድድርን የአሜሪካ ኢምባሲና የጃፓን ዓለማቀፋዊ ኮኦፐሬቲቭ ኤጀንሲ ፕሮጀክቱን በገንዘብ ይደግፉታል። ተመሳሳይ ፕሮግራሞች በየከተሞቹ የሚዘጋጁ ሲሆን የተመረጡ ችግር ፈቺ የፈጠራ ሥራዎች ለሽልማት ይበቃሉ ተብሏል።

    VIDEO: These two Ethiopian students are working to launch their own rocket – the future Eng. Kitaw Ejigu

    የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የኢኖቬሽን ልማትና ምርምርና ዘርፍ ዳይሬክተር ጀነራል ካህሊድ አህመድ (ዶ/ር) በፕሮጀክቱ ተመርጠው የመጡ የፈጠራ ሥራዎች ገበያውን እንዲቀላቀሉ ሚኒስቴሩ አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።

    ተጨማሪ ስልጠና የሚያስፈልጋቸውን በቴክኖሎጂ ማበልፀጊያ ማዕከላት በማስገባትና የሥራ ማስጀመሪያ ገንዘብ በመደጎም ጭምር ድጋፍ እንደሚያደረግ አረጋግጠዋል።

    የአሜሪካ ኤምባሲ በኢትዮጵያ በዋናነት ስፖንሰር የሚያደርገው SolveIT ውድድር በወጣት ኢትዮጵያውያን ዘንድ የሳይንስ፣ የቴክኖሎጂ፣ የኢንጂነሪንግ፣ የአርት እና የሒሳብ (STEAM) በወጣቶች ዘንድ ይበልጥ እንዲጎለብቱ የሚያበረታታ ውድድር ሲሆን ፥ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች ለሚኖሩበት ህብረተሰብ፣ ብሎም ለሀገራቸው ችግር ፈቺ የሆኑ የቴክኖሎጂ፣ የሶፍትዌርና የሀርድዌር ፈጠራዎችን በመፍጠር እንዲሳተፉ ያደርጋል።

    ዕድሜያቸው ከ18 እስከ 28 ዓመት የሆነ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች በሚኖሩበት ከተማ ሆነው ህብረተሰባቸው የሚያጋጥመውን ችግር ሊፈታ የሚፍል ፈጠራ ለመፍጠር ለዘጠኝ ወራት ያህል ጊዜ ተሰጥቷቸው ይሠራሉ። በዚህም ጊዜ ከአወዳዳሪዎች በተመደቡላቸው ባለሙያዎች ስልጠና ይሰጣቸዋል። ፈጠራዎቻቸው ከሞባይ አፕ (mobile app) ጀምሮ እስከ ከፍ ያለ የኮምፒዩተር ሶፍትዌር ሊሆን ይችላል። በከተሞቻቸው (በክሎቻቸው) አሸናፊ የሆኑ ተወዳዳሪዎች ከፍ ወዳለው (የፌደራል) ውድድር ያልፋሉ፤ በዚያም ለሳምንት ያህል በዳኞች ና በከፈተኛ ኤክስፐሮች እየተዳኙ ይወዳደራሉ። በዚህም የመጨረሻዎቹ አሸናፊዎች ይለያሉ።

    በአሁኑ ጊዜ ተወዳዳሪዎችን እየተቀበለ ይገኛል። የበለጠ መረጃ የአይኮግ ላብስ (iCog Labs) ድረ ገጽ ላይ ማግኘት ሲችሉ (እዚህ ጋር ይጫኑ)፥ መመዝገቢያውን ደግሞ እዚህ ጋር ያገኙታል (Register)።

    ምንጭ፦ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    SolveIT ውድድር


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– ግዙፉ የመኪና አምራች የሆነው የጀርመኑ ኩባንያ ቮልስዋገን በኢትዮጵያ ኢንቨስት ለማድረግ የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ፈረመ። ስምምነቱን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽነር አበባ አበባየሁ እና ከሰሃራ በታች የኩባንያው የአፍሪካ ቀጣና ሥራ አስፈጻሚ ቶማስ ሻፈር ተፈራርመዋል። በስምምነቱ መሠረትም ኩባንያው የመኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካ መክፈት፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫ ዕቃዎችን ማቅረብ፣ የስልጠና ማዕከል መክፈት እና ተጓዳኝ ሥራዎችን ይሠራል።

    በስምምነቱ ላይ በኢትዮጵያ የሥራ ጉብኝት ላይ የሚገኙት የጀርመኑ ፕሬዚዳንት ፍራንክ ዋልተር ስታይንማየር እና የኢፌዴሪ የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ ተገኝተዋል።

    ቮልስዋገን ኩባንያ ከሰሃራ በታች ካሉ የአፍሪካ አገራት መካከል ኢትዮጵያን የማስፋፊያ ማዕከሉ አድርጎ ሲመርጥ፣ ከኩባንያው ጋር የመግባቢያ ስምምነት በመፈረም ከሰሃራ በታች ካሉ አገራት ኢትዮጵያ ሦስተኛዋ አገር (ከጋና እና ናይጄሪያ ቀጥሎ) ሆናለች።

    ◌ VIDEO: የጀርመኑ ግዙፍ የመኪና አምራች ኩባንያ ኢትዮጵያ ውስጥ ሰፊ ኢንቨስትመንት ለመጀመር እየተንቀሳቀሰ ነው

    ኩባንያው ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ለመሥራት መስማማቱ በቀጥታ የእሴት ሰንሰለት የተቀናጀ የአውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪ ክላስተር ለመፍጠር ወሳኝ ምዕራፍ ይከፍታል ነው የተባለው።

    ኮሚሽነር አበበ አበባየሁ በፊርማ ሥነ-ስርዓቱ ላይ እንዳሉት መንግሥት አገሪቷን ቀዳሚ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ለማድረግ በቁርጠኝነት እየተንቀሳቀሰ ነው።

    ”በአውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪው መስክ ልዩ ክላስተር እንዲመሠረት መንግሥት ያለሰለሰ ጥረት ያደርጋል” ያሉት ኮሚሽነሩ ይህን ተግባራዊ ለማድረግ ቮልስዋገንን ጨምሮ ፍላጎት ካላቸው ተቋማት ጋር በቅንጅት ለመሥራት ‘ዝግጁ ነው’ ብለዋል።

    ◌ VIDEO: German companies including Volkswagen and Siemens embarking to invest in Ethiopia

    የኩባንያው የአፍሪካ ቀጣና ሥራ አስፈጻሚ ቶማስ ሻፈር በበኩላቸው የኢትዮጵያ መንግሥት ለአውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪው እድገት ትኩረት መስጠቱ ‘የሚደነቅ ነው’ ሲሉ ተናግረዋል። ከዚህ በተጨማሪ ቶማስ ሻፈር ‘ኢትዮጵያ ፈጣን እድገት በማስመዝገብ ላይ ያለች እና በሕዝብ ብዛትም ከ አህሪካ አገራት በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠች በመሆኗ፥ ከሰሃራ በታች ባሉ ሀገራት ለመስፋፋት በምናደርገው ጥረት ኢትዮጵያን ሁነኛ ተመራጭ አገር አድርገናታል፤ በተጨማሪም ቮልስዋገን ኩባንያ ሀገሪቱ ያላትን የስትራቴጂ ጥቅም ከግምት በማስገባት በ አውቶሞቲቭ ዘርፍ ከፍትኛ እድገት እንድታስመዘግብ ይተጋል’ ብለዋል።

    ከዚህ ጋር በተያያዘ የጀርመን የቢዝነስ ልኡካን ቡድን ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የሥራ ሃላፊዎችና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በኢትዮጵያ በኢንቨስትመንት መስክ በሚሰማሩበት ሁኔታ ላይ መክረዋል።

    ሲመንስ የተሰኘው በግዙግነቱ ከአውሮፓ ኩባንያዎች ቀዳሚውን ስፍራ የሚይዘው የጀርመን የቴክኖሎጂ ኩባንያ በኢትዮጵያ ከዚህ በፊት ሲሠራቸው ከነበሩ የቴክሎጂ ዘርፍ ሥራዎች በተጨማሪ በተጠናከረ መልኩ ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን አሳውቋል።

    NEWS: German automaker Volkswagen develops automotive industry in Ethiopia

    የጀርመን የቴክኖሎጂ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ማኅበርም ቢሮውን አዲስ አበባ በመክፈት ወደ ሥራ ለመግባት ፍቃደኛ መሆኑን አሳውቋል። ማኅበሩ ጀርመን ውስጥ ያሉ የቴክኖሎጂ ድርጅቶች ማኅበር እንደመሆኑ ድርጅቶቹ በመስኩ ለመሰማራት የሚያስችላቸውን ሁኔታ ለማመቻቸት መልካም አጋጣሚን እንደሚፈጥር ይታመናል።

    በኢትዮጵያ መንግስት በኩል በጊዜያዊነት በነፃ ቢሮ በመስጠት ጭምር ማንኛውንም እገዛ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑንም ተገልጿል።
    የልኡካን ቡድኑ አባላት በኢትዮጵያ ውስጥ በኢንቨስትመንት የተሰማሩ ድርጅቶች ከምንዛሬ እጥረት፣ በደላላ ምክንንያት ምርቶቻቸው ተጠቃሚው ጋር በተጋነነ ዋጋ መድረስ የመሳሰሉ ችግሮች እንደገጠሟቸው ተናግረዋል።

    የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ር ኢንጂ.) የኤሌክትሮኒክስ ግብይት ለመጀመር ሥራዎች እየተሰሩ በመሆኑ ወደ ሥራ ሲገባ ችግሩ እንደሚቀረፍ ተናግረዋል።

    ምንጮች፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) / የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ቮልስዋገን


    Semonegna
    Keymaster

    ቤልካሽ ኢትዮጵያ የሚያስጀምራቸው ሄሎማርኬት እና ሄሎሾፕ የተሰኙ ሁለት የኤሌክትሮኒክስ መገበያያ ገፆች በኢትዮጵያ ውስጥ እና ከኢትዮጵያ ውጪ ለሚገኙ ተገልጋዮች ኢንተርኔት አማካኝነት ግብይት መፈም የሚችሉባቸው ናቸው።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ቤልካሽ ኢትዮጵያ ተጠቃሚዎች በበይነመረብ (ኢንተርኔት) አማካኝነት ግብይት መፈም የሚችሉባቸው ሁለት የኤሌክትሮኒክስ መገበያያ ገፆችን በቅርቡ እንደሚያስጀምር አስታወቀ።

    ሄሎማርኬት (Hellomarket) የተሰኘው ገፅ በዋነኛነት በኢትዮጵያ ውስጥ ለሚገኙ ተገልጋዮቹ ብቻ ካሉበት ቦታ ሆነው ቁሳቁሶችን የሚሸምቱበት አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን በበይነመረብ አማካኝነት የግዥ ትዕዛዝ እና ክፍያ የተፈፀመባቸው ቁሳቁሶቹን ወደ ደምበኞች ለማጓጓዝም ከ ዓለምአቀፉ ዲኤችኤል (DHL) ጋር ስምምነት ተፈራርሟል።

    The dispute between RIDE Taxi, Ethiopian-kind of Uber, and Addis Ababa Transport Authority continues

    ተቋሙ በመጀመርያው ምዕራፍ ወደ 2,500 የሚጠጉ ሴት ኢትዮጵያውያን በባለቤትነት በሚያስተዳድሩዋቸው የተለያዩ ድርጅቶች የተመረቱ ምርቶችን ለማሻሻጥ ቅድመ ዝግጅቱን አጠናቋል።

    በተመሳሰይ ቤልካሽ ከኢትዮጵያ ውጭ ሆነው የኤሌክትሮኒክ ግብይት መፈፀም ለሚፈልጉ ደንበኞቹ አገልግሎት የሚሰጥ ሄሎሾፕ (Helloshop) የተሰኘ ሌላ ገፅ ያዘጋጀ ሲሆን የክፍያ ስርዓቱም በማስተር ካርድ አማካኝነት አንደሚከወን ለማወቅ ተችሏል።

    Ethiopia – blueMoon Incubator and Addis Garage co-working space for startups in Ethiopia

    ቤልካሽ ኢትዮጵያ መቀመጫውን ኔዘርላንድ ባደረገው እና ቤልካሽ ቴክኖሎጂ ሶሉሽን (Belcash Technology Solutions) የተሰኘ በኤሌክትሮኒክ ክፍያ ቴክኖሎጂ ዘርፍ ላይ የተሰማራ ድርጅት እህት ኩባንያ ሲሆን እ.ኤ.አ ከ2011 ጀምሮ በኢትዮጵያ በተለይም በሞባይል ክፍያ እና የገንዘብ ማስተላለፍ ዘርፎች ላይ የተለያዩ ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ከኩባንያው ድረገፅ የተገኘ መረጃ ያመላክታል።

    የኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ሥርዓት በተገቢው አለመስፋፋት እና በዚህ ዘርፍ ላይ ግልፅ የሆኑ ፖሊሲዎችን አለመኖራቸው በኢትዮጵያ መሰል የኤሌክተሮኒክ ግብይት ተቋማት እንዳይስፋፉ እንቅፋት መሆኑን ባለሞያተኞች ይገልፃሉ።

    ከዚህ ዜና ጋር በተመሳሳይ የቻይናው ግዙፉ የኤሌክትሮኒክስ መገበያያ (e-commerce) አሊባባ ኢትዮጵያ ውስጥ ገብቶ ለመሥራት ፍላጎት እንዳለውና ከኢትዮጵያ ባላስልጣናት ጋር (የቀድሞ የኢፌዴሪ ፕሬዝደንት ዶ/ር ሙላቱ ተሾመን ጨምሮ) መወያየቱን የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዘግቦ ነበር

    ምንጭ፦ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ / አዲስ ፎርቹን
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    ቤልካሽ ኢትዮጵያ


Viewing 15 results - 1 through 15 (of 19 total)