Search Results for 'አማራ ክልል'

Home Forums Search Search Results for 'አማራ ክልል'

Viewing 15 results - 106 through 120 (of 120 total)
  • Author
    Search Results
  • Semonegna
    Keymaster

    ሰዎች የእርሻና የግጦሽ ቦታዎችን ለማስፋት በጥብቅ ቦታዎች እና በፓርኮች ዙሪያ በሚያደርጉት ጣልቃ ገብነቶች የኢትዮጵያ ቀይ ቀበሮዎች የመኖርያ ቦታ ስጋት ላይ ከመውደቁ ባሻገር የዱር አራዊቱ በበሽታው እየተለከፉ መሆኑ ተጠቁሟል።

    (የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት) – የኢትዮጵያ ቀይ ቀበሮዎች ውሻን በሚያሳብድ በሽታ እየሞቱ መሆናቸው ተረጋግጧል።

    ብርቅዬ እንስሳቱን ውሻን ከሚያሳብድ በሽታ ለመከላከል ክትባት እየተሰጠ መሆኑን ደግሞ የአማራ ክልል አካባቢ ደን እና የዱር እንሰሳት ልማትና ጥበቃ ባለስልጣን አስታውቋል።

    በኢትዮጵያ ከሚገኙ ብርቅየ የዱር እንስሳት መካከል የኢትዮጵያ ቀይ ቀበሮዎች ይጠቀሳሉ። የኢትዮጵ ቀይ ቀበሮዎች በአማራ ክልል በሚገኙ የሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ፣ በቦረና ሳይንት “ወረ ሂመኑ ብሄራዊ ፓርክ፣” በመንዝ ጓሳ እና በአቡነ ዮሴፍ የማኅበረሰብ ጥብቅ ቦታዎች ይገኛሉ። በደላንታ ዳውንት አንዳንድ አካባቢዎችም አልፎ አልፎ እንደሚገኙ ከአማራ ክልል አካባቢ ደን እና የዱር እንሰሳት ጥበቃ ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

    በባለሥልጣኑ የዱር እንሰሳት ጥበቃ ባለስልጣን አቶ አብርሃም ማርየ እንደተናገሩት በነዚህ አካባቢዎች ከ2 መቶ በላይ በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙ የቀይ ቀበሮ ዝርያዎች አሉ።

    እንደ ባለስልጣኑ ገለፃ ብርቅየ የዱር እንስሳቱን ውሻን ከሚያሳብድ በሽታ ለመከላከል የሚያስችል ክትባት እየተሰጠ ነው።

    የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያን የተጋረጠባቸው አደጋ (ቪዲዮ)

    ሰዎች የእርሻና የግጦሽ ቦታዎችን ለማስፋት በጥብቅ ቦታዎች እና በፓርኮች ዙሪያ በሚያደርጉት ጣልቃ ገብነቶች የዱር አራዊቱ የመኖርያ ቦታ ስጋት ላይ ከመውደቁ ባሻገር ቀይ ቀበሮዎቹ በበሽታው እየተለከፉ መሆኑ ተጠቁሟል።*

    ባሳለፍነው ጥቅምት ወር በአቡነ ዮሴፍ የማኅበረሰብ ጥብቅ ስፍራ በሽታው የሞቱ የኢትዮጵያ ቀይ ቀበሮዎች መገኘታቸውም ተገልጧል። የበሽታውን ስርጭት ለመቀነስም ባለሥልጣኑ የኢትዮጵያ ቀይ ቀበሮ ፕሮጀክት ከተባለ ድርጅት ጋር በመተባበር በሁሉም የቀይ ቀበሮ መገኛ ቦታዎች ክትባት እየሰጠ ነው።

    አብዛኛዎቹ ቀይ ቀበሮዎች ክትባቱን እንዲያገኙ ለማድረግ ውሻን በሚያሳብድ በሽታ መድኃኒት የበለፀገ ስጋ በማቅረብ እንዲመገቡ የማድረግ ሥራ የክትባቱ አንድ አካል ነው።

    በተመሳሳይ መልኩ በመንዝ ጓሳ ማኅበረሰብ ጥብቅ ደን አራት የኢትዮጵያ ቀይ ቀበሮዎች ሞተው ተገኝተዋል። ለህልፈት የዳረጋቸው ናሙና ወደ እንግሊዝ ተልኮ “ካናዲስ ዲስትምፕተር” የተባለ በሽታ መሆኑ መረጋገጡን አቶ አብርሃም አስረድተዋል።

    የአማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት (አብመድ) እንደዘገበው ክትባቱ እስከያዝነው ኅዳር ወር መጨረሻ ይቆያል።

    * አፍሪካን ዋይልድላይፍ ፋውንዴሽን (African Wildlife Foundation – AWF) የተባለ ድርጅት ስለ አትዮጵያ ቀይ ቀበሮዎች ባወጣው ዘገባ እነዚህ የዱር አራዊት በቁጥራቸው እጅግ ለመምናመን እና ለህልውናቸው አስጊ የሆኑት ሁለት ዋነኛ ምክንያቶች፥ በሚኖሩበት አካባቢ በሚገኙ ሰዎች የሚዘወተር እርሻ እና የውሻ ዘርን የሚያጠቁ በሽታዎች ቢሆኑም የእርሻ ሥራ (እና ቦታውን ለከብቶች ግጦሽ ማዋል) ግን ከፍተኛውን ድርሻ ይወስዳል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እና AWF

    ቀይ ቀበሮዎች

    Semonegna
    Keymaster

    ድሬ ዳዋ (ሰሞነኛ)– የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ዘላቂ የሆነ ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲኖር በአንድነት ለመሥራት ቃል ገቡ። ከሰሞኑ ግጭት ውስጥ የገቡ ተማሪዎች የሀይማኖት አባቶችና ከፍተኛ የመንግስት አካላት በተገኙበት ዕርቅ አውርደዋል።

    ሰሞኑን ዩኒቨርሲቲው ውስጥ ባልተከሰተና በሀሰት በተሰራጨ መረጃ ምክንያት በዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች መካከል የተፈጠረው ግጭት ዳግመኛ እንዳይከሰት ተማሪዎቹ ከፍተኛ ጥረት እንደሚያደርጉና በተማሪዎች መካከል የሚፈጠሩ የግለሰብ ግጭቶችንም ወደ ቡድንና የብሄር ግጭትነት ለመቀየር የሚፈልጉ አካላትን ጥረት እንደሚያወግዙ ተናግረዋል።

    ኅዳር 13 ቀን 2011 ዓ.ም. የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ስልጠና ማዕከል ውስጥ በተካሄደው የእርቅ ዝግጅት ላይ የተሳተፉ ተማሪዎች በሰጡት አስተያየት፥ ተማሪዎችን በብሄር እንዲጋጩ ሁኔታዎችን በሚፈጥሩና በሚያነሳሱ ተማሪዎችና አገልግሎት ሰጪ አካላት ላይ ዩኒቨርሲቲው ክትትል አድርጎ አስተማሪ እርምጃዎችን በመውሰድ የሕግ የበላይነትን እንዲያስከብር ጠይቀዋል።

    ከየትኛውም ብሄር ጥሩ ሰዎች እንዳሉ ሁሉ መጥፎዎችም ሊኖሩ እንደሚችሉና እነዚህ ሰዎች በዩኒቨርሲቲያችን ውስጥ የእኩይ ተግባራቸውን ለማስፈፀም ብሄራቸውን ሽፋን በማድረግ ለመጠቀም ስለሚሞክሩ ተማሪዎች ተሳስተው የወንጀለኞች ተባባሪና የእኩይ ተግባራት ማስፈፀሚያ እንዳይሆኑ መረጃዎችንና ሁኔታዎችን ከስሜት በጸዳና በምክንያታዊነት እንዲመለከቱ የመድረኩ ተሳታፊዎቹ ጥሪ አቅርበዋል።

    These two Ethiopian students are working to launch their own rocket – the future Eng. Kitaw Ejigu

    የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ባለፉት ዓመታት በአንድነት ጥያቄያቸውን ሲያቀርቡ እንደነበርና በመካከላቸውም አለመስማማቶች ሲፈጠሩ በራሳቸው መንገድ ተወያይተው ችግሮችን ሲፈቱ እንደነበር አስታውሰው ዘንድሮም ይህን አንድነታችንን በማስጠበቅ በመካከላችን ልዩነቶችን በመፍጠርና ግጭት እንዲቀሰቀስ በማነሳሳት የድብቅ ሴራቸው ማስፈፀሚያ ሊያደርጉን የሚፈልጉ አካላትን ሴራ እናከሽፋለን ብለዋል። ባለፉት ጥቂት ቀናት መለስተኛ ግጭት በመፈጠሩ ይቅርታ የተጠያየቁት ተማሪዎች አጋጣሚውን ለቀጣይ በመማሪያነት በመውስድ ችግሮችን በጋራ ለመከላከል እንደሚጠቀሙበት ተናግረዋል።

    የአማራ ክልልንና የአማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲን (አዴፓ) ወክለው የተገኙት አቶ ባዘዘው ጫኔ እንደተናገሩት ችግሩ በመፈጠሩ የአማራ ክልልና የክልሉ ገዢ ፓርቲ አዴፓ ማዘኑን ገልፀው ግጭቱ ሳይሰፋና የከፋ ችግር ሳያስከትል በቁጥጥር ስር እንዲውል የዩኒቨርሲቲው አመራሮችና ተማሪዎች እንዲሁም የአካባቢው ማኅበረሰብ አካላት ላደረጉት ጥረት ደግሞ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

    ሰዎች በብዛት ተሰባስበው በሚኖሩባቸው አካባቢዎች ግጭት ሊከሰት እንደሚችል አቶ ባዘዘው አስታውሰው በግለሰቦች የሚጀመር ግጭትን ወደብሄር ማዞሩ አደገኛና ሊወገዝ የሚገባው መሆኑን ተናግረዋል። በሐረማያ ዩኒቨርሲቲም ሰሞኑን በተከሰተው ግጭት በርካታ ተማሪዎች ጉዳዩን በማውገዝ ወደ ግጭት ባለመግባታቸው ቶሎ በቁጥጥር ስር እንዲውል እንዳስቻለ የተናገሩት አቶ ባዘዘው ተማሪዎች በአንድነት ተሳስቦ በፍቅር የመኖር ልማዳቸውን በማጎልበት የዩኒቨርሲቲያቸውንና የአካባቢያቸውን ሰላም እንዲጠብቁ ጥሪ አቅርበዋል።

    የኦሮሚያ ክልልንና የክልሉ ገዢ ፓርቲ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲን (ኦዲፓ) ወክለው የተገኙት አቶ አብዱላዚዝ መሀመድ ባደረጉት ንግግር ተማሪዎቹ እርቅ ለማውረድ ያሳዩትን ፍላጎት አድንቀዋል። አቶ አብዱላዚዝ አያይዘውም ባለፉት ሰባት ወራት መንግስት ለዓመታት የተከማቹ የሕዝብ ጥያቄዎችን በመፍታት ላይ እንደሚገኝና በዚህም ከፍተኛ ለውጥ እየተመዘገበ በመሆኑ ይህን ለውጥ የማይፈልጉ አካላት የመንግስትን የለውጥ ጉዞን ለማደናቀፍ በየቦታው ግጭቶች እንዲነሱ በማድረግ መንግስትን ግጭቶችን በመከላከል ላይ እንዲጠመድ በማድረግ የተጀመሩ የለውጥ ጉዞዎችን ለማደናቀፍ ጥረት እያደረጉ እንደሆነ ተናግረዋል።

    ስለዚህ የነገዋ ባለተስፋና የዜጎቿ መኩሪያ የሆነች ኢትዮጵያን ተረካቢ የሆኑ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ይህን ተረድተው ራሳቸውን ከስሜታዊነት አርቀው፣ መረጃዎችን በጥንቃቄ በመመርመር ምክንያታዊ በመሆን ግጭቶች እንዳይከሰቱ ጥረት እንዲያደርጉና ከግጭቶች በመራቅ የእኩይ ተግባር ማስፈፀሚያ ከመሆን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አቶ አብዱላዚዝ ለተማሪዎች ጥሪ አቅርበዋል።

    በሀገራችን የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የተሻለ አስተሳሰብ ያላቸው ወጣቶች የሚገኙበት እንደሆነ እንደሚታመን የተናገሩት የሳይንስና የከፍተኛ ትምህር ጉዳዮች ሚኒስቴር ተወካይ አቶ ጌታቸው ነጋሽ በአስተሳሰባችሁ መላቃችሁንና ማኅበረሰባችን የሰጣችሁን ይህን ግምት ትክክለኛነት ለማሳየት ምክንያታዊ በመሆን ለነገሮች መፍትሄ በመስጠት ልታስመሰክሩ እንጂ እንደዘይትና ውሃ የተፈጠራችሁበት ነገር ሳይለያይ በብሄር ልትከፋፈሉና ልትጋጩ አይገባም ብለዋል።

    የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ተወካይ ፕሬዝዳንት ጀማል ዩሱፍ (ዶ/ር) በበኩላቸው ተማሪዎች በብሄር ከማሰብ ወጥተው አንድነት ላይ በማተኮር የዩኒቨርሲቲውን ሰላም በጋራ በማስጠበቅ በቂ ዕውቀት ጨብጠው በሀገራችን የእድገት ጉዞ ላይ የራሳቸውን አሻራ እንዲያሳርፉና ራሳቸውን የጥፋት ኃይሎች ድብቅ ዓላማ አስፈፃሚ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

    በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት እንዳይኖር እንቅፋት ይፈጥራሉ በማለት በተማሪዎች በቀረቡ ጥቆማዎች ላይም አስፈላጊውን ክትትል ግምገማ በማድረግ የእርምት እርምጃዎችና የሕግ የበላይነትን የማስከበር ሥራዎች እንደሚከናወኑ ዶ/ር ጀማል አረጋግጠዋል።

    በእርቅ መድረኩ ላይ የተሳተፉ የሀይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎችም በተማሪዎች መካከል ሰላም፣ ፍቅርና ይቅር ባይነት እንዲጎለብት የበኩላቸውን ኃላፊነት እንደሚወጡ ቃል ገብተዋል።

    ምንጭ፦ የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማኅበረሰብ ሬዲዮ ጣቢያ (HU FM 91.5 RADIO)

    የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አባባ (ብርሃን ባንክ)–የብርሃን ባንክ ባለአክስዮኖች ዘጠነኛ መደበኛ ጉባኤ ቅዳሜ ኅዳር 1 ቀን 2011 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ ተካሂዷል። የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሊቀመንበር አቶ ጉማቸው ኩሴ ይፋ ባደረጉት ሪፖርት እ.ኤ.አ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ባንኩ በዋና ዋና የአፈፃፀም መለኪያዎች የላቀ የሥራ አፈጻጸም በማስመዝገብ እንደ ከዚህ በፊቱ ሁሉ ጠንካራ እና ተፎካካሪ ባንክ መሆኑን በድጋሚ አስመስክሯል ሲሉ ገልፀዋል።

    በተገባደደው የበጀት ዓመት ብርሃን ባንክ ከግብር በፊት ብር 410.9 ሚሊዮን ትርፍ ማስመዘገብ መቻሉን ገልፀዋል። በዚሁ በጀት ዓመት ባንኩ ተጨማሪ አክስዮኖችን በመሸጥ የተከፈለ ካፒታሉን ወደ ብር 1.7 ቢሊዮን ያሳደገ ሲሆን ከአለፈው የበጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ20 በመቶ የሆነ ከፍተኛ ጭማሪ ማሳየቱን ገልፀዋል። በተመሳሳይ መልኩም ባንኩ በበጀት ዓመቱ የባለአሲዮኖቹን ቁጥር ወደ 14,879 አድርሷል። ይህም ባንኩን በኢትዮጵያ ባንክ ኢዱስትሪ ውስጥ ከግል ባኮች በባለአክስዮኞ ቁጥር ቀዳሚ ባንክ አድርጎታል። በመሆኑም ባንኩ ሠፊ የሕዝብ መሠረት /Public Base/ ያለው የሕዝብ ባንክ መሆኑን ያረጋግጣል ብለዋል። በሌላ በኩል ሊቀመንበሩ በበጀት ዓመቱ ባንኩ አጠቃላይ ሀብቱ አምና ከነበረው 10 ቢሊዮን ወደ ብር 14 ቢሊዮን ብር በማድረስ የሀብት መሠረቱን እያሰፋ እና ራሱን ለቀጣይ እድገት ይልጥ በተሻለ ሁኔታ እያደራጀ መሆኑን ገልፀዋል። ከዚህም በተጨማሪ ባንኩ የነበረውን የደንበኞች አገልግሎት በላቀ መልኩ የተቀላጠፈ ለማድረግ እንዲሁም አዳዲስ የባንክ አገልግሎት አማራጮችን በመቅረፅ ደንበኞችን ይበልጥ ለማገልገል የሚረዳ ደረጃውን የጠበቀ የመረጃ ማዕከል ገንብቶ እ.ኤ.አ 2018/19 የበጀት ዓመት ለአገልግሎት ዝግጁ አድርጓል።

    ብርሃን ባንክ በበጀት ዓመቱ ካስመዘገበው የላቀ የሥራ አፈፃፀም ውጤት ባሻገር ከእሴቶቹ መካከል አንዱ የሆነውን ማኅበራዊ ኃላፊነትን ከመወጣት አንፃር በተለያዩ ምክንያቶች ከመኖሪያ ቀዬዎቻቸው ለተፈናቀሉ የህብተሰብ አካላት ድጋፍ እንዲደረግ ከሚመለከታቸው የክልል መንግስታት በቀረበለት ጥያቄ መሠረት የብር ሁለት ሚሊዮን ድጋፍ አድርጓል።

    Berhan Bank, one of the private banks in Ethiopia, registers more than 410 million birr before tax

    የብርሃን ባንክ ፕሬዘዳንት የሆኑት አቶ አብርሃም አላሮ በበኩላቸው የተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ከፍተኛ የገበያ ውድድር እና በባንኩ ክፍለ ኢኮኖሚ በርካታ ተግዳሮቶች የነበሩበት ዓመት መሆኑን ጠቅሰው በበጀት ዓመቱ ባንኩ በሁሉም የሥራ ዘርፍ ያስመዘገበው የሥራ አፈጻጸም ውጤት እጅግ አመርቂ መሆኑን ገልጸዋል። ባንኩ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ጠቅላላ ተቀማጭ ሂሳቡን ወደ ብር 11 ቢሊዮን ሲያሳድግ ይህም ከአለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከነበረው ጋር ሲነጻጸር የ42 በመቶ የሆነ ከፍተኛ ዕድገት ማሳየቱን አስታወቀው፥ በተመሳሳይ መልኩም ባንኩ ለተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች የሰጠው የብድር ክምችት በበጀት ዓመቱ ከፍተኛ እድገት አስመዝግቦ ብር 7 ቢሊዮን መድረሱን ይህም ከዓምናው ጋር ሲነጻጸር የ33 በመቶ የሆነ ከፍተኛ ብልጫ እንዳለው ገልጸዋል። ባንኩ በኢኮኖሚው በተለያዩ ዘርፎች እያፈሰሰ ያለው የብድር መጠን በየጊዜው እየጨመረ የመጣ መሆኑን ያስረዱት ፕሬዝዳንቱ ባንኩ በአገር ልማት እና እድገት ላይ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ መሆኑን ተናረግዋል።

    ፕሬዝዳንቱ አያይዘውም ብርሃን ባንክ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 21 አዳዲስ ቅርንጫፎችን በመክፈት በመላ አገሪቱ ያሉትን የቅርንጫፎች ቁጥር ወደ 182 የደረሰ ሲሆን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የባንኩ ደንበኞች ቁጥርም ከአለፈው ዓመት ከነበረው የ43 በመቶ የሆነ ከፍተኛ ዕድገት በማስመዝገብ 523,705 መድረሱን ገልጸዋል።

    ብርሃን ባንክ እያስመዘገበ የመጣውን ከፍተኛ የሆነ ሁለንተናዊ ዕድገት ተከትሎ 372 ተጨማሪ ሠራተኞችን በበጀት ዓመቱ የቀጠረ ሲሆን ይህም ባንኩ ያለውን አጠቃላይ የሰው ሃብት ቁጥር ወደ 3,237 ማሳደጉን ፕሬዘዳንቱ ጠቁመዋል። አያይዘውም ባንኩ ለሰው ሃብት ከሚሰጠው ልዩ ትኩረት የተነሳ በበጀት ዓመቱ የባንኩን የተቀላጠፈ የደንበኞች አገልግሎት የሚያሳልጥ እንዲሁም የባንኩን ግልፅነት እና ተዓማኒነት የተሞላበት እሴቶቹን ሊያስጠብቁ እና ደንበኞችን በልሕቀት ማገልግል ይቻል ዘንድ የተለያዩ ስልጠናዎች እንዲወስዱ ተደርጓል ብለዋል። አቶ አብርሃም በቀጣዩ የበጀት ዓመት ባንኩ እሰካሁን የመጣበትን የስኬት ጉዞ ሊያስቀጠል የሚችል ስትራቴጂ ነድፎ በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኝ በመሆኑ ባንኩ የበለጠ ውጤት እንደሚያመጣ ጽኑ እምነት እንዳላቸው ገልጸው፥ የባንኩ ዳይሬክተሮች ቦርድ፣ የበላይ አመራሩ እና መላው ሠራተኛ እንዲሁም በዋናነት ደግሞ የባንኩ ደንበኞች እና ባለድርሻ አካላት እስካሁን ላበረከቱት የላቀ አስተዋፅዖ ምስጋናቸውን አቅርበው ባንኩ ከዚህም በኋላ በላቀ እና በተቀላጠፈ የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደቱ ደንበኞቹን በትጋት እና በታማኝነት እንደሚያገለግል ያላቸውን ፅኑ እምነት ገልፀዋል።

    ምንጭ፦ ብርሃን ባንክ (berhanbanksc.com)

    ብርሃን ባንክ

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ ኢትዮጵያ) – የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ በሙስና ወንጀል እና በሰብዓዊ መብት ጥሰት ተጠርጥረው እስካሁን በቁጥጥር ስር የዋሉ ግለሰቦችን ዝርዝር ይፋ አድርጓል።

    በዚህም መሠረት በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉት፦

    1. ብርጋዴር ጄኔራል ጠና ቁርንዴ ኢጄታ – በብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የማርኬቲንግ ኃላፊ
    2. ብርጋዴር ጄኔራል ብርሃ በየነ – የሜቴክ ኦዲትና ኢንስፔክሽን ኃላፊ
    3. ብርጋዴር ጄኔራል ጥጋቡ ፈትላ መረሳ – የሜቴክ ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የኮርፖሬት ሎጂስቲክስና ሰፕላይ ኃላፊ
    4. ብርጋዴር ጀኔራል ሃድጉ ገብረጊወርጊስ ገብረስላሴ – የሜቴክ ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የኮርፖሬት ኒው ቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ኃላፊ
    5. ኮሎኔል ሸጋው ሙሉጌታ ተስፋሁን – የሜቴክ ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የወታደራዊ ምርቶች ኦፕሬሽን ኃላፊ
    6. ኮሎኔል ሙሉ ወልደገብርዔል ገብረእግዛብሄር – የሜቴክ ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የኒው ቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ኃላፊ የነበሩ
    7. ኮሎኔል ዙፋን በርሄ ይህደግላ – የመከላከያ ጤና ኮሌጅ ሠራተኛ
    8. ሌተናል ኮሎኔል አስምረት ኪዳኔ አብርሃ – የጋፋት አርማመንት ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ተወካይ ኃላፊ የነበሩ
    9. ኮሎኔል አለሙ ሽመልስ ብርሃን – የሜቴክ ሎጂስቲክስና ሰፕላይ የትራንስፖርት ኃላፊ
    10. ኮሎኔል ያሬድ ሃይሉ – የሜቴክ በኮርፖሬት ኒው ቢዝነስ ዴቨሎፕመንት የፕሮጀክት ኃላፊ
    11. ኮሎኔል ተከስተ ሀይለማሪያም አድሃኑ – የሜቴክ ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የኒው ቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ኃላፊ የነበሩ
    12. ኮሎኔል አዜብ ታደሰ – የሜቴክ በኮርፖሬት ማርኬቲንግ የሽያጭ ኃላፊ
    13. ሻለቃ ሰመረ ሀይሌ ሀጎስ – የሜቴክ በደጀን አቪዬሽን የኢንዱስትሪ ኦፕሬሽን ኃላፊ
    14. ሻምበል ይኩኖአምላክ ተስፋዬ – የሜቴክ በኮርፖሬት ማርኬቲንግና ሽያጭ የፕሮሞሽን ኃላፊ
    15. ኮሎኔል ደሴ ዘለቀ ብርሃን – የሜቴክ የአዳማ እርሻ ስራዎች ኢንዱስትሪ ሥራ አስኪያጅ
    16. ሌተናል ኮሎኔል ሰለሞን በርሄ – የሜቴክ በብረታ ብረት ፋብሪኬሽን ኢንዱስትሪ የፋይናንስ ኃላፊ
    17. ሻለቃ ይርጋ አብርሃ – የሜቴክ በህብረት ማሽን ቢዩልዲንግ ኢንዱስትሪ የፋይናንስ ኃላፊ
    18. ኮሎኔል ግርማይ ታረቀኝ – የሜቴክ በኮርፖሬት ሎጂስቲክስና ሰፕላይ የንብረት አስተዳደር ኃላፊ
    19. ሻምበል ገብረስላሴ ገብረጊዮርጊስ – የሜቴክ የኮርፖሬት ትራንስፎርሜሽን የአቅም ግንባታ ማዕከል ኃላፊ
    20. ሻምበል ሰለሞን አብርሃ – የሜቴክ በኮርፖሬት ትራንስፎርሜሽን የስልጠና ኃላፊ
    21. ሻለቃ ጌታቸው ገብረ ስላሴ – የሜቴክ የደን ምንጣሮ ክትትል ኃላፊ
    22. ሌተናል ኮሎኔል ይሰሃቅ ሀይለማሪያም አድሃኖም – የሜቴክ በኮርፖሬት ኮሜርሻልና ሲቪል ምርቶች ኦፕሬሽን የፕላኒንግና ኮንትሮል ኃላፊ
    23. ሻለቃ ክንደያ ግርማይ – የሜቴክ የተለያዩ ኢንዱስትሪዎች የፋይናንስ ኃላፊ
    24. ሌተናል ኮሎኔል አዳነ አገርነው – የሜቴክ በኮርፖሬት ሎጂስቲክስና ሰፕላይ የንብረት ክፍል ኃላፊ
    25. ሻለቃ ጌታቸው አጽብሃ – የሜቴክ ኢንፍራስትራክችርና ኮርፖሬሽን ማሽነሪ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ኦፕሬሽን ኃላፊ
    26. ቸርነት ዳና – የዋይ ቲ ኦ ኩባንያ ባለቤትና ከብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን አመራሮች ጋር የጥቅም ትስስር የነበራቸው ደላላ
    27. አያልነሽ መኮንን አራጌ – ማስረጃ ልታጠፋ ስትል በቁጥጥር ስር የዋለች

    በሰብዓዊ መብት ጥሰት ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉት፦

    1. አቶ ጉሃ አጽበሃ ግደይ – የአዲስ አበባ የደህንነት ኃላፊ
    2. አቶ አማኑኤል ኪሮስ መድህን – የሃገር ውስጥ ደህንነት ጥበቃ ዋና መምሪያ ዳይሬክተር
    3. አቶ ደርበው ደመላሽ – የውስጥ ደህንነት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የነበሩና የኢኮኖሚ ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ
    4. አቶ ተስፋዬ ገብረጻዲቅ – የውስጥ ደህንነት ጥናትና የወንጀል ምርመራ መምሪያ ኃላፊ
    5. አቶ ቢኒያም ማሙሸት – በውስጥ ደህንነት ጥበቃ ዋና መምሪያ የኦፕሬሽን ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ (በዋናነት የግንቦት 7 ጉዳይ ክትትል)
    6. አቶ ተሾመ ሀይሌ – የአማራ ክልል የደህንነት ኃላፊ የነበሩና የጥበቃ ዋና መምሪያ ዳይሬክተር
    7. አቶ አዲሱ በዳሳ – በሃገር ውስጥ ደህንነት የኦሮሚያ ክልል ደህንነት ኃላፊ 
    8. አቶ ዮሃንስ ወይም ገብረእግዚአብሄር ውበት – የውጭ መረጃ
    9. አቶ ነጋ ካሴ – በጸረ ሽብር መምሪያ የኦነግ ክትትል ኃላፊ
    10. አቶ ተመስገን በርሄ – በጸረ ሽብር መምሪያ የኦነግና ኦብነግ ክፍል ዋና ኃላፊ
    11. አቶ ሸዊት በላይ – በሃገር ውስጥ ደህንነት ኦፕሬሽን መምሪያ የግንቦት 7 ክትትል ምክትል መምሪያ ኃላፊ
    12. አቶ አሸናፊ ተስፋሁን – በሃገር ውስጥ ደህንነት የአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን ደህንነት አስተባባሪ
    13. አቶ ደርሶ አያና – በውጭ መረጃ የአማራ ክልል ክትትል
    14. አቶ ሰይፉ በላይ – በውስጥ ደህንነት የደቡብ ክልል ክትትል ኦፊሰር
    15. አቶ ኢዮብ ተወልደ – በውስጥ ደህንነት የደቡብ ክልል ደህንነት ኃላፊ
    16. አቶ አህመድ ገዳ – በውስጥ ደህንነት የኦሮሚያ ክልል ክትትል ምክትል ኃላፊ
    17. ምክትል ኮማንደር አለማየሁ ሀይሉ ባባታ – ቀድሞ የፌደራል ፖሊስ የሽብር ወንጀል ምርመራ ምክትል ዳይሬክተር የነበረና ዋና ዳይሬክተር ሆኖ ያገለገለ
    18. ምክትል ኢንስፔክተር የሱፍ ሀሰን – የሽብር ወንጀል መርማሪ
    19. ዋና ሳጅን እቴነሽ አራፋይኔ – የሽብር ወንጀል መርማሪ
    20. ኢንስፔክተር ፈይሳ ደሜ – የሽብር ወንጀል መርማሪ
    21. ምክትል ኢንስፔክተር ምንላርግልህ ጥላሁን – የሽብር ወንጀል መርማሪ
    22. ዋና ሳጅን ርዕሶም ክህሽን – የሽብር ወንጀል መርማሪ
    23. ኦፊሰር ገብረማሪያም ወልዳይ
    24. ኦፊሰር አስገለ ወልደጊዮርጊስ
    25. ዋና ሱፐር ኢንቴንደንት አሰፋ ኪዳኔ
    26. ዋና ሱፐር ኢንቴንደንት ገብረ እግዚአብሔር ገብረሐዋርያት – የቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የጥበቃና ደህንነት ኃላፊ
    27. ዋና ሱፐር ኢንቴንደንት ተክላይ ኃይሉ – የቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ሠራተኛ
    28. ዋና ሱፐር ኢንቴንደንት አቡ ግርማ – የሸዋ ሮቢት ማረሚያ ቤት ኃላፊ የነበረና በዝዋይ ማረሚያ ቤት ኃላፊ ሆኖ ሲያገለግል የነበረ
    29. ዋና ሱፐር ኢንቴንደንት አዳነ ሐጎስ – የቃሊቲ ማረሚያ ቤት ሠራተኛ
    30. ዋና ሱፐር ኢንቴንደንት ተስፋሚካኤል አስጋለ – በቃሊቲ ማረሚያ ቤት ከፍተኛ የደህንነት ባለሙያ
    31. ዋና ሱፐር ኢንቴንደንት ገብራት መኮንን – የዝዋይ ማረሚያ ቤት የጥበቃና ደህንነት ኃላፊ የነበረና የሸዋ ሮቢት ማረሚያ ቤት ጥበቃና ደህንነት ኃላፊ ሆኖ ሲያገለግል የነበረ
    32. ረዳት ኢንስፔክተር አለማየሁ ኃይሉ ወልዴ – በአዲስ አበባ ፖሊስ የወንጀል መርማሪ
    33. ረዳት ኢንስፔክተር መንግስቱ ታደሰ አየለ – በአዲስ አበባ ፖሊስ የወንጀል መርማሪ
    34. አዳነች ወይም ሃዊ ተሰማ ቶላ
    35. ጌታሁን አሰፋ ቶላ
    36. ሙሉ ፍሰሃ

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    በቁጥጥር ስር የዋሉ ግለሰቦች ዝርዝር

    Semonegna
    Keymaster

    ግንባታው ስድስት ዓመታትን የፈጀው የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በቀን 2000 የሚሆኑ ታካሚዎችን ሊያስተናግድ የሚችል፣ 11 የቀዶ ሕክምና ክፍሎች እና 500 አልጋዎች አንዳሉት ተገልጿል።

    ባሕር ዳር (ሰሞነኛ ኢትዮጵያ) – የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በ207 ሚሊዮን ብር ወጪ ያስገነባው ጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ነገ በሦስት አገሮች መሪዎች ይመረቃል።

    የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘ እና የሕክምና ኮሌጅ የሥራ አፈጻጸም ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር የሺጌታ ገላው በጋራ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ዩኒቨርሲቲው የግንባታ ወጪው 207 ሚሊዮን ብር የፈጀውና ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ የሆነውን ጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የፌደራልና የክልል ባለስልጣናት በተገኙበት ህዳር 1 ቀን 2011 ዓ.ም. በድምቀት እንደሚያስመርቅ ገልጸዋል።

    በምረቃ ሥነ ስርዓቱ ላይ ከሦስቱ መሪዎች በተጨማሪ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸውና ሌሎችም ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ ባለስልጣናትና ጥር የተደረገላቸው እንግዶች ይገኛሉ ፕሮፌሰር የሺጌታ ተናግረዋል።

    ከዚሁ መግለጫ ጋር አብሮ እንደተጠቀሰው በዩኒቨርሲቲው የሕክምና ኮሌጅ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ 148 የህክምና ተማሪዎችም ከኮሌጁ ለስድስተኛ ጊዜ ይመረቃሉ።

    በእነዚህ የሆስፒታሉ እና የተማሪዎቹ ምረቃ መርሀ ግብር ላይ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ (ኢፌዴሪ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)፣ የኤርትራ ሀገረ ግዛት ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂና የሱማልያ ፌደራላዊ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት መሐመድ አብዱላሂ መሐመድ በተገኙበት ይከናወናሉ።

    የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንቱ ዶክተር ፍሬው ተገኘ እንደገለጹት በመሪዎቹ የሚመረቀው ሆስፒታሉ የቀዶ ህክምና የሚጠይቁና ወደ ክፍተኛ ሕክምና መስጫ ቦታ የተላኩ (referral) በሽታዎችን የሚያክምና በተለያዩ የትምህርት ክፍሎች (ዲፓርትመንቶች) ውስጥ በሕክምና እና በጤና ባለሙያነት ተማሪዎችን የሚያሰለጥን ነው።

    Ethiopia: Are Ethiopian hospitals constructed in environment-suitable and climate-friendly way?

    ግንባታው ስድስት ዓመታትን የፈጀው ጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በቀን 2000 የሚሆኑ ታካሚዎችን ሊያስተናግድ የሚችል፣ 11 የቀዶ ሕክምና ክፍሎች ያሉት፣ 500 አልጋዎችን መያዝ የሚችል መሆኑን ፕሮፌሰር የሺጌታ አብራርተዋል። በክልሉ ካሉት ስፔሻላይዝድ ሆስፒታሎች በጥራትም ሆነ በአገልግሎት የተሻለ ሆኖ ለመገኘት መዘጋጀቱንም ገልጸዋል።

    ሀምሌ 7 ቀን 2006 ዓ.ም. ከተመረቀው የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ሆስፒታል በመቀጠል በክልሉ ስድስተኛ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እንደሚሆን አስታውቀዋል። አያይዘውም ሆስፒታሉ ለምርቃቱ ቀን ይብቃ እንጅ እጅግ ዘመናዊ የሆኑ የህክምና ቁሳቁሶችና ሌሎች መሟላት ያለባቸው ነገሮች ስላሉ ከመንግስት በተጨማሪ ለጋሽ አካላትና በዚህ ዙሪያ የሚሠሩ ወገኖችን ትብብር የሚጠይቅ መሆኑን ገልጸዋል።

    ሚያዝያ 28 ቀን 1992 ዓ.ም በኢፌዴሪ የትምህርት ሚኒስቴር ስር በሙሉ ዩኒቨርሲቲነት የተመረቀው የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሀገሪቱ ውስጥ ካሉት ግዙፍ ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ ሲሆን፥ በ2010 ዓ.ም  52,830 ተማሪችዎችን፣  219 የትምህርት  ዘርፎች (69 በመጀመሪያ/ባችለር ዲግሪ፣ 118  በሁለተኛ/ማስተር  እና 32 በሶስተኛ/ዶክትሬት ዲግሪዎች) ተቀብሎ ያስተምራል። ዩኒቨርሲቲው ስምንት ካምፓሶች ሲኖሩት፥ በውስጣቸውም አምስት ኮሌጆች፣ አራት ተቋማት (institutes)፣  ሁለት ፋኩልቲዎችና አንድ የሕግ ትምህርት ቤት (School of Law)  አሉት።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ ዓለም ከተማ የሞቱት ሁለቱ ተመራማሪዎች ወሰን ታፈረ እና ማንደፍሮ አብዲ የሚባሉ ሲሆን፥ ከባድ የመቁሰል አደጋ የደረሰበት የሜጫ ወረዳ ጤና መኮንን (የላቦራቶሪ ባለሙያ) የሆነው ኃይለየሱስ ሙሉ ይባላል።

    አዲስ ዓለም፣ አማራ ክልል – በምዕራብ ጎጃም ዞን ጎንጂ ቆለላ ወረዳ ለምርምር ወደ አዲስ ዓለም ከተማ የሄዱ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሶስተኛ (ዶክትሬት) ዲግሪ ተማሪዎች እና የሜጫ ወረዳ ጤና መኮንን በከተማው የሚኖሩ ግለሰቦች ባደረሱባቸው ጥቃት ሁለቱ ህይወታቸው ሲያልፍ፣ አንዱ ደግሞ የመቁሰል አደጋ ደርሶበታል። ሁለቱ የሞቱት ተመራማሪዎች ወሰን ታፈረ እና ማንደፍሮ አብዲ የሚባሉ ሲሆን፥ ከባድ የመቁሰል አደጋ የደረሰበት የሜጫ ወረዳ ጤና መኮንን (የላቦራቶሪ ባለሙያ) የሆነው ኃይለየሱስ ሙሉ ይባላል።

    የዶክትሬት ተማሪዎቹ አዲስ ዓለም ከተማ ውስጥ በሚገኝ አንድ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ለምርምር የሚሆን የሽንትና የዓይነ ምድር ናሙና እየሰበሰቡ ባሉበት ወቅት ከዕለቱ ቀደም ብሎ በተለይም በማኅበራዊ ሚዲያዎች “ሦስት ተማሪዎች ሞቱ” በሚል በተነዛው ወሬ ተቆጥተው በመጡ የአካባቢው ወጣቶች በደረሰባቸው ከፍተኛ ጥቃት ሕይወታቸው ማለፉን የምዕራብ ጎጃም ዞን የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ አንማው ዳኛቸው ለአሜሪካ ድምፅ የአማርኛ ዝግጅት ክፍል ተናግረዋል።

    ከዚሁ ጋር በተያያዘ ቢቢሲ አማርኛ የጎንጂ ቆለላ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ ደመቀ መላኩን ጠቅሶ እንደዘገበው “በተሳሳተ መልኩ ልጆቻችን የጤና ክትባት እየተሰጣቸው ነው፤ እየተመረዙብን ነው፤ ሊገደሉብን ነው” በሚል የተቆጡ ቁጥራቸው በርከት ያሉ የአካባቢው ግለሰቦች የዶክትሬት ተማሪዎቹ (ተመራማሪዎቹን) ወደነብሩበት የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ሄደዋል። የትምህርት ቤቱ የጥበቃ ሠራተኞች ሁኔታው ከአቅማቸው በለይ ሲሆን በአካባቢው በነበሩ ጥቂት የጽጥታ አስከባሪ አካላት (ፖሊሶች) ታግዘው ተመራማሪዎቹን ወደ ፖሊስ ጣቢያ እየወሰዷቸው ሳለ፥ በከተማው መናኸሪያ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ጥቃቱ እንደደረሰባቸው ቢቢሲ አማርኛ ጨምሮ ዘግቧል።

    አዲስ ዓለም

    ግለሰቦቹ ያደረሱት ጥቃት በተማራማሪዎቹ ላይ ብቻ ሳይገታ ሁኔታው በፈጠረው ግርግር ለቤተ ክርስቲያን ህንፃ ግንባታ ግልጋሎት የሚውል ሲሚንቶ በራሳቸው መኪና ጭነው ወደ አካባቢው ተጉዘው የነበሩ ጥንዶች ንብረትም መቃጠሉን የአሜሪካ ድምፅ አቶ አንማው ዳኛቸውን ጠቅሶ ዘግቧል። አቶ አንማው ለአሜሪካ ድምፅ አክለው በሰጡት ማብራሪያ በዚህ ድርጊት ተሳትፈዋል በሚል የተጠረጠሩ 30 ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን፣ ብሎም በተፈፀመው ድርጊት የአካባቢው ማኅበረሰብም ሆነ መንግሥት ማዘኑን እና በድርጊቱ ተሳትፈዋል የተባሉትን እየፈለጉ በቁጥጥር ስር የማዋሉ ሥራ መቀጠሉን ጠቁመዋል።

    ከቢቢሲ አማርኛ ጋር ቃለ ምልልስ ያደረጉት የጎንጂ ቆለላ ወረዳ የኮሚዩኒኬሽን ኃላፊ አቶ አንተነህ በላይ በበኩላቸው ከዚህ ቀደም በክልሉ ዋና ከተማ ባህር ዳር ውስጥ ለህፃናት ክትባት ሲሰጡ ሞቱ በሚል በተናፈሰ ወሬ ምክንያት መኪና መሰባበር፣ እንዲሁም በአንዳንድ ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት (መቁሰል) መድረሱን አስታውሰው አካባቢው ለባህር ዳር ከተማ ቅርብ በመሆኑ ይሄው መረጃ በመናፈሱ ጥቃቱ ሊፈፀም እንደቻለ አስረድተዋል። አቶ አንተነህ አክለው እንደተናገሩ ጥቃቱን ያደረሱት የ አካባቢ ተወላጆች መሆናቸውና አገር ሊጠቅሙ ምሁራን በራሳቸው ወገኖች በመገደላቸው የ አካባቢው ማኅበረሰብ መፀፀቱን፣ በድርጊቱ የተጠረጠሩ ግለሰቦችን አጋልጦ መስጠት የጀመረውም ራሱ ህብረተሰቡ እንደሆነ ተናግረዋል።

    የአሜሪካ ድምፅ የአማርኛ ዝግጅት ክፍል ጋዜጠኛ ጽዮን ግርማ ከምዕራብ ጎጃም ዞን የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ አንማው ዳኛቸው ጋር ያደረገችውን ቃለ ምልልስ ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

    Semonegna
    Keymaster

    “ለኢንቨስትመንት በሚል ሰበብ አርሶ አደሩን በማደህየት ኢንቨስትመንቱን ማሳደግ አይቻልም፤ መሬታቸው የሚወሰድባቸው አርሶ አደሮች ተመጣጣኝ ካሳ ማግኘት አለባቸው።” ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው

    ዘጋቢ፡-ደጀኔ በቀለ (አብመድ)

    ባሕር ዳር – የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ቢሮ በ2011 ዓ.ም በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ፣ በሕግ ማዕቀፎች እና አሠራሮች ላይ ሲሰጥ የነበረውን ክልላዊ የምክክር መድረክ ዛሬ አጠናቅቋል።

    የአማራ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ለኢንቨስትመንት በሚል ሰበብ ብዙ አርሶ አደሮች መብታቸው ተጥሶ እንደነበር በመጥቀስ አርሶ አደሩን በማደህየት ኢንቨስትመንቱን ማሳደግ አይቻልም፤ መሬት የሚወሰድባቸው አርሶ አደሮች ተመጣጣኝ ካሳ ማግኘት አለባቸው ሲሉ አስገንዝበዋል። ቀደም ሲል ካሳ የማያገኙበት ሕግ የነበረ ቢሆንም ሕጉን የማስተካከል እርምጃ መወሰዱንም አስታውቀዋል።

    አርሶ አደሮች እና የነባር ይዞታ ባለቤቶች መሬታቸውን ሕጋዊ በሆነ መንገድ እንዲጠቀሙ መደረጉ ጥያቄ በሚያነሱበት ጊዜ በመረጃ ላይ የተመሠረተ ምላሽ ለመስጠት ከማገዙም በላይ ህብረተሰቡ ተረጋግቶ እንዲሠራ ያደርገዋል። በመሆኑም አርሶ አደሩን ከአላስፈላጊ እንግልት የምናድንበት በመሆኑ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ርዕሰ መስተዳድሩ አሳስበዋል።

    አርሶ አደሮች በጉልበተኛ ጥቅማቸውን የሚያጡበት ፍትሃዊ ያልሆነ አሠራር ካለ የገጠር መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም ቢሮ ህዝባዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ጠንክሮ መሥራት እና የፍትህ ስርዓቱን ማስከበር ይጠበቅበታልም ነው ያሉት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው።

    ሕገ-ወጥ የመሬት ወረራን በተመለከተ ትኩረት ተሰጥቶት እንዲሠራ ርዕሰ መስተዳድሩ በጥብቅ አሳስበዋል። በተለይ የወል መሬቶች በሕገ-ወጥ መንገድ ወደ ግለሰቦች ይዞታ ስር እየገቡ በመሆኑ በፍጥነት መግታት ካልተቻለ ስር እየሰደደ ሄዶ ግለሰቦች ላይ ጫና ማሳደሩ እንደማይቀር አስገንዝበዋል።

    በመድረኩ የተሳተፉ አካላት በባለቤትነት ይዞ በመንቀሳቀስ ከሚመለከተው ባለድርሻ አካላት ጋር ትኩረት ሰጥተው ሊሠሩ እንደሚገባም አፅንዖት ሰጥተው ተናግረዋል።

    ለተከታታይ አምስት ቀናት የቆየውን የምክክር መድረክ የተካፈሉ አስተያየት ሰጪዎች በበኩላቸው በሚችሉት አቅም ሁሉ ህብረተሰቡን ለማገልገል ፍቃደኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።

    ተጨማሪ ዜና፦ ኢትዮጵያዊው ባለሃብት አቶ በላይነህ ክንዴ እያስገነቡ ያሉት የምግብ ዘይት ፋብሪካ በቅርቡ ሥራ ይጀምራል

    አቶ ወዳጅ ምስክር ከሰሜን ወሎ ዞን፣ ወይዘሮ በላይነሽ አሻግሬ ደግሞ ከደቡብ ጎንደር ፋርጣ ወረዳ በምክክር መድረኩ የተገኙ ተሳታፊዎች ናቸው። ከውይይቱ በቂ ግብዓት እንዳገኙ ነግረውናል። ተሳታፊዎቹ እንደተናገሩት ወቅቱን መሰረት ያደረገ የገጠር መሬት አጠቃቀም ስልጠና መውሰዳቸው ለቀጣይ የተጣለባቸውን የሕዝብ ኃላፊነት በብቃት ለመወጣት ዝግጁ እንደሚያደርጋቸው ለአብመድ ጋዜጠኞች አረጋግጠዋል።

    በመዝጊያ ሥነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት ርዕሰ መስተዳድር ገዱ አንዳርጋቸው የገጠር መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም ቢሮ ከወረዳ እስከ ክልል ድረስ ተቋማዊ በሆነ መንገድ ሥራውን በአግባቡ ለመወጣት ጥረት እያደረገ ያለ ተቋም መሆኑን አውስተው፥ መሬት ሀብት እና የማንነት መገለጫ መሆኑን በመረዳት የኃላፊነት ስሜት በተሞላበት መንገድ ሲንቀሳቀስ ለቆየው ለተቋሙ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ ሥራው አድካሚ መሆኑን በመጥቀስ ወደ ዘመናዊ የመረጃ ቋት ለማስገባት ተቋሙ እያደረገ ያለው ጥረት የሚበረታታ ነው ብለዋል።

    ከገጠር መሬት ጋር በተያያዘ ለሚከሰቱ ማንኛውም ጥያቄዎች ምላሽ መስጠት የሚችለው በመድረኩ ላይ የተሳተፈው ባለሙያ ነው፤ በተለይ በምዕራብ ቆላማው የክልሉ አካባቢዎች ለበርካታ ዘመናት ጥሩ አሠራር ያልነበረባቸውን ቦታዎች በዚሁ ተቋም ውስጥ በተሰማሩ ሙያተኞች እና አመራሮች አማካኝነት ውጤታማ በሆነ መንገድ ማስተካከል ተችሏል ብለዋል።

    በከተሞች ዙሪያ የሚኖሩና ትኩረት የማያገኙ አርሶ አደሮች ጥቅማቸው እና መብታቸው እንዲከበር በማድረግ በኩል ትልቅ ሥራ ተሰርቷል፤ ተገፍተው ለነበሩ አርሶ አደሮች በተገቢው መንገድ ካሳ እንዲያገኙ ተደርጓል ብለዋል።

    ምንጭ፦ የአማራ መገናኛ ብዙሀን ድርጅት (አብመድ)

    ገዱ አንዳርጋቸው

    Semonegna
    Keymaster

    በመቀሌ ከተማ በ147 ሚሊዮን ብር ካፒታል ሙሉ ብርሃን ኢንዱስቱሪና ንግድ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ያቋቋመው ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ምሶሶ ማምረቻ ፋብሪካ ከ200 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ፈጥሯል።

    መቀሌ (ኢዜአ) – በ147 ሚሊዮን ብር ካፒታል የተቋቋመው ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ገመድ ተሸካሚ የኮንክሪት ምሶሶ ማምረቻ ፋብሪካ ምርት ማከፋፈል መጀመሩን አስታወቀ።

    “ሙሉ ብርሃን ኢንዱስቱሪና ንግድ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር” በሚል የተቋቋመው ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ምሶሶ ማምረቻ ፋብሪካ ከ200 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ፈጥሯል።

    የፋብሪካው ሥራ አስኪያጅ አቶ እሥራኤል ብርሃኑ ለኢዜአ እንደገለጹት ፋብሪካው በአገር አቀፍ ደራጃ ያለውን የኮንክሪት ምሶሶ ችግር ለመፍታት ታሳቢ ተደርጎ የተቋቋመ ነው።

    ፋብሪካው በአሁኑ ወቅት በቀን እስከ 90 የሚደርስ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ተሸካሚ ምሶሶዎችን በማምረት ላይ ሲሆን በሙሉ አቅሙ ሥራ ሲጀምር በቀን እስከ 300 የተለያዩ ደረጃ ያላቸው ምሶሶዎችን የማምረት አቅም እንደሚኖረው ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል።

    ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በመነጋገር ፋብሪካው ምርቶቹን ለትግራይአማራአፋር ክልሎች ማከፋፈል መጀመሩን አቶ እሥራኤል አስታውቀዋል።

    ፋብሪካው ከአገር ውስጥ ስሚንቶ፣ አሸዋና ጠጠር የሚጠቀም ሲሆን ለምሶሶው መሥሪያ የሚውሉ ብረቶችን ከውጭ በማስገባት ለአገልግሎት ያውላል።

    ፋብሪካው በሚያመርተው ምርት መንግስት በከተማና በገጠር የኤሌክትሪክ ሽፋን ለማዳረስ እያከናወነ ላለው ሥራ አጋዥ መሆኑን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል።

    የክልሉ መንግስት በቦታ አቅርቦትና ብድር በማመቻቸት እገዛ እንዳደረገላቸው የገለጹት አቶ እሥራኤል ፋብሪካው በሙሉ አቅሙ ማምረት እንዲችል ከውጭ ለሚመጡ ጥሬ ዕቃዎች መግዣ የውጭ ምንዛሬ አቅርቦት እንዲመቻችላቸው ጠይቀዋል።

    በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የትግራይ ቅርንጫፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ገብረመድህን የኮንክሪት ምሶሶ ማምረቻ ፋብሪካው ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ምርቶች ማምረት መጀመሩን ተናግረዋል።

    የኮንክሪት ምሶሶ ማምረቻ ፋብሪካው በመቀሌ ማምረት መጀመሩ ከአሁን ቀደም ከአዲስ አበባ ለማጓጓዝ ለትራንስፖርት ይወጣ የነበረውን ወጪ ይቀንሳል ብለዋል።

    ከፍትኛ የኤሌክትሪክ ምሶሶዎች ለ20 ዓመታት ዋስትና ያላቸው መሆኑን የገለጹት ሥራ አስፈፃሚው ካሁን በፊት ለአገልግሎት ይውሉ የነበሩ የባህርዛፍ ምሶሶዎች በጉዳት ምክንያት ያደርሱ የነበሩትን አደጋና የኤሌክትሪክ መቆራረጥ የሚቀንስ ነው።

    የትግራይ ክልል ኢንቨስትመንት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሃፍቶም ፋንታሁን እንደገለጹት የምሶሶ ማምረቻ ፋብሪካው በመቀሌ ከተማ ለተለያዩ የኢንቨስትመንት ሥራዎች ቦታ ከተሰጣቸው ባለሀብቶች መካከል በፍጥነት ወደ ማምረት ሥራ መሸጋገር መቻሉ በአርያነቱ እንዲቀመጥ የሚያደርገው ነው።

    የትግራይ ክልል የተረጋጋ ሰላም ያለው በመሆኑ በርካታ የውጭና የአገር ውስጥ ባለሀብቶች በተለያዩ የኢንቨስትመንት ሥራዎች እየተሳተፉ መሆናቸውን የጽህፈት ቤት ኃላፊው ገልጸዋል።

    በመካኒካል ምህንድስና የተመረቀው ወጣት አማኑኤል ሀይሉ በፋብሪካው በመቀጠር በወር 6ሺህ ብር የወር ደሞዝ እየተከፈለው ይሠራል። በፋብሪካው የሥራ እድል በማግኘቱ ደስተኛ መሆኑን የሚናገረው ወጣት አማኑኤል ገቢ ማግኘት መጀመሩ ከቤተሰብ ጥገኝነት ወጥቶ የራሱን ቤተሰብ ለመመስረት መቻሉን ገልጿል።

    ወጣት ዙፋን ኪዳኑ በበኩሏ “ማኅበሩ በዘርፉ ኢንቨስት በማድረጉ የአካባቢውን ወጣቶች የሥራ አድል ተጠቃሚ አድርጎናል” ብላለች።

    በትግራይ ክልል በ2010 ዓ.ም 24 ቢልዮን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ 1ሺህ 328 ባለሀብቶች በሥራ እንዳሉ ከክልሉ ኢንቨስትመንት ጽህፈት ቤት የተገኘ መረጃ ያመልክታል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)

    የኤሌክትሪክ ምሶሶ

    Semonegna
    Keymaster

    የማህፀን በር ካንሰር መከላከያ ክትባት የሚሰጥበት ጊዜ ተራዘመ

    የማህፀን በር ካንሰር መከላከያ ክትባት የሚሰጥበት ቀን መራዘሙን የአማራ ክልል ጤና ጥበቃ ቢሮ አስታወቀ።

    ክትባቱ በኢትዮጵያ በሁሉም ክልሎች በጥቅምት ወር እና ከስድስት ወራት በኋላ ደግሞ ለሁለተኛ ዙር ሊሰጥ ታቅዶ ነበር። በቢሮው የክትባት መርሃ ግብር የቴክኒክ አማካሪ አቶ ሙሉጌታ አድማሱ እንደገለፁት ለክትባት የሚሆነው መድሃኒት በመዘግየቱ ምክንያት ክትባት የሚሰጥበት ቀን ወደ ህዳር 5/2011 ዓ.ም ተራዝሟል።

    በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሚሰጠው የማህፀን በር ካንሰር መከላከያ ክትባት ዉጤታማነት በአማራ ክልል በሁሉም ዞኖች እና ወረዳዎች ለጤና ባለሙያዎች ስልጠና መሰጠቱንም አቶ ሙሉጌታ ነግረውናል። ከጤና ጥበቃ ቢሮ ያገኘነው መረጃ እንደሚያሳየው በክልሉ ከ4 መቶ 50 ሺህ በላይ ልጃገረዶች ክትባቱን ይወስዳሉ። እድሜያቸው 14 ዓመት የሆናቸው ልጃገረዶች ብቻ የክትባቱ ተጠቃሚ እንደሚሆኑም ለማወቅ ተችሏል።

    የማህፀን በር ካንሰር መከላከያ ክትባት እድሜያቸው ከ9 እስከ 14 ዓመት የሆናቸው ልጃገረዶችን የግብረ ስጋ ግንኙነት ከመፈጸማቸው በፊት ከበሽታው ለመከላከል ሲባል በዓለማቀፍ ደረጃ ይሰጣል። ይሁን እንጅ በኢትዮጵያ ደረጃ ለሁሉም ልጃገረዶች የሚበቃ መድኃኒት ገዝቶ ማቅረብ ባለመቻሉ ለበሽታው ይበልጥ ተጋላጭ የሆኑት ላይ ክትባቱ እንደሚሰጥ ጤና ጥበቃ ቢሮው ገልጿል።

    Semonegna
    Keymaster

    ቡሬ ከተማ ውስጥ በአቶ በላይነህ ክንዴ የተቋቋመው የፊቤላ ኢንዳስትሪያል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ስር እየተገነባው ያለው የምግብ ዘይት ፋብሪካ ሥራ ሲጀምር በሀገራችን የሚስተዋለዉን የምግብ ዘይት እጥረት በ60 በመቶ ይቀንሳል።

    አዲስ አበባ – በሀገራችን በህብረተሰቡ የመሰረታዊ እቃዎች የዕለት ፍጆታ ላይ የአቅርቦት እጥረት ይስተዋላል። የምግብ ዘይት አቅርቦት እጥረት በመኖሩ መንግስት ለህብረተሰቡ በየወሩ በኮታ ልክ ያከፋፍላል። ይሁንና ችግሩ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ ይገኛል ሲሉ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ቅሬታ ያነሳሉ። በአማራ ክልል በወር ከ23 ሚሊየን ሊትር በላይ የምግብ ዘይት አቅርቦት ያስፈልገዋል። ክልሉ እያሰራጨ ያለው ግን 7 ነጥብ 7 ሚሊየን ሊትር የምግብ ዘይት እንደሆነ ከአማራ ክልል ንግድ ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

    በቡሬ ከተማ በላይነህ ክንዴ በተሰኙ ባለሀብት ፊቤላ ኢንዱስትሪያል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር በሚል ስያሜ የምግብ ዘይትና ሌሎች ምርቶች ማምረቻ ፋብሪካ እየተገነባ ይገኛል። ከ500 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦለት ግንባታው የተጀመረው ፋብሪካ የምግብ ዘይት፣ ፕላስቲክ፣ ሳሙና እና የተቀነባበረ ሰሊጥ ያመርታል።

    የፊቤላ ኢንደስትሪያል ኃ/የተ/የግል ማህበር አስተዳደር እና ፋይናንስ ኃላፊ አቶ ጎጃም ዓለሙ እንደተናገሩት በ2006 ዓ.ም የመሠረት ድንጋይ ተጥሎ ወደ ግንባታ ገብቷል። የህንጻ እና መሠረተ ልማት አውታሮች ግንባታ ተጠናቋል። ነገር ግን የዘይት ፋብሪካው የማሽን ተከላ ዘግይቷል። ለዚህም በዋነኝነት እንደምክንያት የሚጠቀሰው ሀገሪቱ ያጋጠማት የውጭ ምንዛሪ እንደሆነ ከዚህ በፊት Mutesi የተሰኘ በአፍሪካ የንግድና ቢዝነስ እንቅስቃሴ ላይ ያተኮረ ሚዲያ ዘግቦ ነብር። አሁን ላይ ግን ማሽኑን ለመትከል ዝግጅቱ ተጠናቋል አቶ ጎጃም እንደገለጹት። በአጭር ጊዜ ውስጥም ወደ ምርት ይገባል ነዉ ያሉት። የፊቤላ ኢንደስትሪ የምግብ ዘይት ማምረት ሥራ ሲጀምር ከ1 ሚሊዮን ሊትር በላይ በቀን የማምረት አቅም ይኖረዋል። በዚህም የአማራ ክልል የዘይት አቅርቦት እጥረትን ከመፍታት አልፎ ከክልሉ ውጭ ላሉ አካባቢዎች ማድረስ ይችላል።

    “የዘይት ፋብሪካው ሥራ ሲጀምር በሀገራችን ያለውን የፋብሪካ ቁጥር ያሳድጋል። በሀገር ደረጃ የሚስተዋለዉን የምግብ ዘይት እጥረት ችግር እስከ 60 በመቶ ይቀንሳል። በየዓመቱ ከ12 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የቅባት እህሎችን በግብዓትነት ስለሚጠቀም ለአርሶ አደሩ የገበያ ዕድል በመፍጠር ተጠቃሚ ያደርጋል” በማለት አቶ ጎጃም ተናግረዋል። ወደ ውጭ ምርቶችን በመላክ የውጭ ምንዛሪ ያስገኛልም ብለዋል።

    የመብራት እና የውሀ አቅርቦት ችግር የምርት ሂደቱ ላይ ከፍተኛ ጫና የሚያሳድር እና ጊዜ የማይሰጥ እንቅፋት፥ ምናልባትም ፋብሪካው ሊያጋጥሙት ከሚችሉት ተግዳሮቶች ዋነኛው መሆኑን ጠቁመዉ የሚመለከታቸው አካላት አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጡ መልዕክት አስተላልፈዋል።

    Ethiopian millionaire Belayneh Kinde and others awarded for investing in pulses, oilseeds & spices

    የቡሬ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ እና የንግድ፣ ኢንደስትሪ እና ገበያ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ይገርማል ሙሉሰዉ በበኩላቸዉ ፊቤላ ኢንደስትሪያል ኃ/የተ/የግል ማኅበር በሀገር ደረጃ የሚስተዋለዉን የምግብ ዘይት አቅርቦት ችግር ይቀንሳል ብለዋል። ለወጣቶች የሥራ ዕድል ከማስገኘቱ በላይ ለአርሶ አደሩ የገበያ ትስስር በስፋት እንደሚፈጥርም ተናግረዋል።

    የህንጻ እና የመሠረተ ልማት ግንባታዉ ከ95 በመቶ በላይ መጠናቀቁን ጠቅሰዉ የመብራት እና ውሀ አቅርቦት ችግር ካልገጠመው በተያዘው በጀት ዓመት ፋብሪካው ሥራ ይጀምራል። ይሁን እንጂ የመብራት እና የውሀ ችግሩ ስር የሰደደ እና ከከተማ አስተዳደሩ አቅም በላይ በመሆኑ የፌዴራል መንግስት ትኩረት እንደሚያሻዉ አቶ ይገርማል ነግረውናል።

    ፋብሪካው እስከ 1500 ለሚሆኑ ሰዎች በቋሚነት እና በጊዚያዊነት የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር የአማራ ብዙኃን መገናኛ ድርጅትን ዋቢ በማድረግ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ዘግቧል።

    አቶ በላይነህ ክንዴ ማን ናቸው?

    • የተወለዱት በአማራ ክልል፣ ምዕራብ ጎጃም ዞን፣ ሰቀላ ወረዳ (ቡሬ አጠገብ) ነው፤
    • የአስራ ሁለተኛ ክፍል ትምህርታቸውን እንዳጠናቀቁ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ውጤት ስላልመጣላቸው ሁርሳ ወታደራዊ ማሠልጠኛ ገብተው ወታደራዊ ስልጠና ተከታትለዋል፤
    • ነገር ግን በውትድርና ሕይወት ብዙም አልገፉም፤ የደርግ መንግስት ወድቆ የኢህአዴግ መንግስት ስልጣን ሲይዝ የውትድርና ሥራን ትተው እጅግ አናሳ በሆነ ገቢ የቀን ሥራ ላይ ተሰማሩ፤
    • በቀን ሥራ ገፍትው ጥቂት ገንዘብ እንዳጠራቀሙ የማር እና የቅቤ ንግድ ጀመሩ፤
    • በማር እና ቅቤ ንግድ ለአስር ዓመታት ሠርተው ንግዳቸውን በማሳደግ “በላይነህ ክንዴ አስመጪና ላኪ” የሚል ድርጅት መሠረቱ፤
    • ይህንን የአስመጪና ላኪነት ሥራ ከጊዜ ወደጊዜ በካፒታል፣ በሥራ ዘርፍ እና ሠራተኞችን በመቅጠር፣… በአጠቃላይ በሁሉም አቅጣጫዎች በማሳደግ በአሁኑ ጊዜ ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ጥቂት ሚሊየነሮች ተርታ ሊሰለፉ ችለዋል (ይህንንም በዓለም ታዋቂው የቢዝነስ መጽሔት ፎርቤስ/Forbes በ2009 ዓ.ም ዘገባው አንስቷቸው ነበር)፤
    • በአሁኑ ወቅት የአቶ በላይነህ ክንዴ አጠቃላይ ሀብት ከሶስት ቢሊየን ብር (ከ111 ሚሊየን ዶላር) በላይ ሲሆን የተሰማሩበት የንግድና ምርት ዘርፍም አስመጪና ላኪነት፣ ትራንስፖት፣ የግንባታ ምርቶች፣ እርሻ እና ፋይናንስ ሲሆኑ ሀገሪቱ ውስጥ ባሉ ግዙፍ አክሲዮን ማኅበራት፥ ለምሳሌ ያህል ጎልደን ባስ ኢትዮጵያ፣ ኢትዮጵያ ሆቴል፣ አዳማ ራስ ሆቴል፣ ፀሐይ ኢንዱስትሪያል ፣ ኳሊቲ ብረታ ብረት ማምረቻ አክሲዮን ማኅበራት ውስጥ ሁነኛ ድርሻ አላቸው።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እና Mutesi

    በላይነህ ክንዴ

    Semonegna
    Keymaster

    ጨፌ ኦሮሚያ ባደረገው ሶስተኛ አስቸኳይ ጉባዔ ላይ ወ/ሮ ሎሚ በዶ አፈ ጉባዔ ሆነው ሲመረጡ አዲስ በጸደቀ አዋጅም በክልሉ በቁጥር 42 የነበሩት የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ቁጥራቸው ወደ 38 ዝቅ ተደርጎ በአዲስ መልክ እንዲዋቀሩ ተወስኗል።

    አዳማ (ሰሞነኛ)– የኦሮሚያ ክልል ምክር ቤት (ጨፌ ኦሮሚያ) በአዳማ ከተማ እያደረገ ባለው አራተኛ ዓመት፣ አምስተኛ የሥራ ዘመን፣ ሶስተኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ 28 ቀን 2011 ዓ.ም. ባደረገው ውሎ ወ/ሮ ሎሚ በዶን አፈ ጉባዔ አድርጎ መርጧል።

    ወ/ሮ ሎሚ በዶ  በአሁኑ ወቅት የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባዔ የሆኑትን አቶ እሸቱን ደሴን የሚተኩ ሲሆን በጉባዔው ላይ እንደተገለጸው አቶ እሸቱ ደሴ በተደራረበባቸው የሥራ ኃላፊነት ምክንያት ከቦታቸው እንዲነሱ ተደርገዋል።

    በተያያዘ ዜና ጨፌ ኦሮሚያ እያደረገ ባለው የጠቅላላ ጉባዔ ላይ የክልሉን የሥራ አስፈጻሚ አካላት መልሶ ለማደራጀት እና በተለያየ እርከን ደረጃ ያሉትን ሰዎች ስልጣንና ኃላፊነታቸውን ለመወሰን የሚያስችል አዋጅ አጽድቋል።

    በተጨማሪም ጨፌ ኦሮሚያ  የየክልሉን  ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ለማቋቋም የወጣው ረቂቅ አዋጅ አጽድቋል። በዚህ ረቂቅ አዋጅ መሠረት ከዚህ በፊት የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት የፍትህ ቢሮ ተብሎ ይጠራ የነበረው በአዲሱ አደረጃጀት የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ተብሎ ተሰይሟል።

    በክልሉ ውስጥ በርካታ የአስተዳደራዊ ችግሮች መኖራቸውን፣ እነዚህን ችግሮች ለመቅረፍ ብዙ ተግባራትና ማሻሻያዎች ቢከናወኑም ሕዝቡ እያቀረበ ያለውን ቅሬታ አሉታዊ በሆነ መልኩ ቀርፎ ለሕዝቡ እርካታን መፍጠር ስላልተቻለ የመዋቅራዊ አደረጃጀት ለውጥ ማድርግ አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ምክትል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ለማ መገርሳ በጠቅላላ ጉባዔው ላይ አስረድተዋል።

    አቶ ለማ እንዳሉት የተቀላጠፈና ጥራት ያለው አገልግሎት ከመስጠት አኳያ ጉልህ ክፍተት እንዳለና፣ በተለያዩ ቢሮዎች ተሀድሶ ተብለው የተጀመሩ የ አሠራር ለውጦችም በሰራተኞችና አገልግሎት ሰጪዎች ላይ አመለካከት ከመቀየር (ከማደስ) ባለፈ በሕዝቡ ዘንድ በሚያገኘው አገልግሎት እርካታን ሊፈጥር እንዳልቻለ ገልጸዋል።

    በዚህም መሠረት የተጀመሩ ለወጦች አሁንም እንዲቀጥሉና፣ ተጨማሪ ወይም አማራጭ ለውጥ የሚያስፈልጋቸው ቦታውን በተገቢው መንገድ ትግባራቸውን እንዲወጡ መዋቅራዊና አደረጃጀታዊ ለወጥ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ እንደተገኘ አቶ ለማ መገርሳ ተናግረዋል።

    በጸደቀው አዋጅ መሠረት ከዚህ በፊት በቁጥር 42 የነበሩት የክልሉ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት (ቢሮዎች) ወደ 38 ዝቅ ተደርገው የተዋቀሩ ሲሆን በተመሳሳይ መልኩ በክልሉ ውስጥ በዞን፣ በወረዳ እና በቀበሌ ደረጃ የተዋረዱ የአገልግሎት ተቋማትም በአዋጁ መሠረት በአዲስ እንደሚዋቀሩ ከጠቅላላ ጉባዔል ለማወቅ ተችሏል።

    ጨፌ ኦሮሚያ

    Semonegna
    Keymaster

    የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ያስገነባው የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ የግንባታ ሥራው የተጀመረው በጥቅምት ወር 2009 ዓ.ም ሲሆን የቻይናው ግዙፍ ኩባንያ ቻይና ሲቪል እንጂነሪንግ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ግንባታውን ሲያከናውን ነበር።

    አዳማ (Semonegna) – በኦሮሚያ ክልል፣ አዳማ ከተማ የተገነባው የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ በዛሬው ዕለት (መስከረም 27 ቀን 2011 ዓ.ም.) ተመርቋል። በምርቃቱ ስነ ስርዓት ላይም ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) እና የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ምክትል ፕሬዝደንት አቶ ለማ መገርሳ፣ የአማራ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው፣ የእንደስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር አርከበ ዕቁባይ እና የኮርፖሬሽኑዋና ሥራ አስፈጻሚ ወ/ት ሌሊሴ ነሜ እንዲሁም ሌሎች የክልልና የፌደራል ባለስልጣናት ከፍተኛ ተገኝተዋል።

    የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ያስገነባው የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ የግንባታ ሥራው የተጀመረው በጥቅምት ወር 2009 ዓ.ም ሲሆን የቻይናው ግዙፍ ኩባንያ ቻይና ሲቪል እንጂነሪንግ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን (China Civil Engineering Construction Corporation/ CCCC) ግንባታውን ሲያከናውን ነበር።

    ከአዲስ አበበ ከተማ 99 ኪሎ ሜትሮች ርቆ የሚገኘው የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ በተለያየ ዘርፍ ለሚሰማሩ አምራች ኩባንያዎች የሚያገለግሉ በአጠቃላይ 19 (በዝርዝር፦ ስድስት 11 ሺህ ካሬ ሜትር፣ ዘጠኝ 5 ሺህ 500 ካሬ ሜትር፣ አራቱ ደግሞ በ3 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፉ) የመሥሪያ ጠለላዎች ወይም የመሥሪያ ቦታዎችን (shades) የያዘ ነው። የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ በአጠቃላይ ሊለማ ከታቀደው 2 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ በመጀመሪያው ዙር ልማት 354 ሄክታር መሬት የሚይዝ ሲሆን ከዚህ ውስጥ ለምቶ ለዛሬ ምረቃ የበቃው በ100 ሄክታር መሬት ላይ የተገነባው ክፍል መሆኑን፣ ይህም ግንባታ 4.1 ቢልዮን ብር መፍጀቱን፣ እንዲሁም ፓርኩ በመጀመሪያው ምዕራፍ በሙሉ አቅም ወደ ምርት ሲገባ እስከ 25 ሺህ ለሚደርሱ ዜጎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ወ/ት ሌሊሴ ነሜ በምረቃው ንግግራቸው ላይ አስታውቀዋል።

    ◌ RELATED: A visit to Hawassa Industrial Park by Dire Dawa Industrial Park & City’s Administration people

    የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ተመርቆ ሥራ መጀመር በሀገሪቱ ወደማምረት የገቡ የኢንዱስትሪ ፓርክኮች ቁጥር ወደ አምስት የሚያሳድገው ሲሆን፥ ከሌሎቹ አራቱ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ለየት የሚያደርገው ፓርኩ ያለበት ከተማ (አዳማ) በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ትልቅ አስተዋጽዖ ያመጣል ተብሎ የታመነበተና አምና ሥራ የጀመረው የአዲስ አበባ-ጅቡቲ የባቡር መስመር በሚያልፍባት የአዳማ ከተማ መገኘቱ ነው። ይህ የባቡር መስመርና የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ እርስ በርሳቸው ጉልህ የሆነ የጥቅም ግንኙነት ይኖራቸዋል ተብሎ ይታመናል። ከዚህ በተጨማሪ የኢንዱስትሪ ፓሩኩ በከተማ ከሚገኘው የአዳማ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩንቨርሲቲ ጋር በማምረት ዘርፍ እና በመማር፣ ማስተማርና ምርምር ዘርፎች መካከል ቁልፍ የሆነ ግንኙነት ይፈጥራሉ ይጠበቃል።

    የሀገሪቱ የማኑፋክቸሪንግ ሴክተር (manufacturing sector) ከኢትዮጵያ ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) መጠን አራት ነጥብ አምስት በመቶ (4.5%) ድርሻ ብቻ የሚሸፍን ሲሆን፥ መንግስት እስከ 2022 ዓ.ም (እ.ኤ.አ) ይህን አናሳ ድርሻ ወደ ሀያሁለት በመቶ (22%) ለማሳደግ አቅዳለች። ከዚህ በተጨማሪ ኢትዮጵያ እስከ 2025 ዓ.ም (እ.ኤ.አ) አሁን ያሏትን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ቁጥር ከአምስት ወደ ሀያ አምስት የማሳደግ ዕቅድ አላት። በያዝነው ዓመት ስድስት የኢንዱስትሪ ፓርኮች (ድሬ ዳዋ፣ ቂሊንጦ II፣ ቦሌ ለሚ II፣ ጅማ፣ ባህር ዳር እና ደብረ ብርሃን) ግንባታቸው ተጠናቆ ወደምርት ተግባር እንደሚገቡ ዶክተር አርከበ ዕቁባይ አስታውቀዋል። 

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ

    Semonegna
    Keymaster

    የማህፀን ጫፍ ካንሰር በሽታን በዘላቂነት ለመከላከል የማህፀን ጫፍ ካንሰር ክትባትን ከዘጠኝ እስከ 14 ዓመት የዕድሜ ክልል ለሚገኙ ልጃገረዶች እንዲሰጥ መንግስት መወሰኑን የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ተወካይ አመልክተዋል።

    ባህር ዳር (ኢዜአ)፦ ከ450 ሺህ ለሚበልጡ ልጃገረዶች የማህፀን ጫፍ ካንሰር (cervical caner) መከላከያ ክትባት በዘመቻ ለመስጠት ዝግጅት እያደረገ መሆኑን የአማራ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ።

    በቢሮው የጤና ማበልፀግ ዋና የስራ ሂደት መሪ አቶ መልሰው ጫንያለው ለኢዜአ እንደገለጹት የማህፀን ጫፍ ካንሰር በሽታ እንደሀገርም ሆነ እንደክልል ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ ይገኛል።

    ዜጎችን እየጎዳ ያለው ይህንን በሽታ ለመከላከል በክልሉ የተመረጡ 25 ጤና ተቋማት ችግሩን እየለዩ ህክምና እየሰጡ መሆናቸውን ተናግረዋል።

    ምርመራ ከሚያደርጉ እናቶች መካከልም 30 በመቶ የሚሆኑት የበሽታው ተጠቂዎች ሆነው መገኘታቸውን የምርመራ ውጤቱ አረጋግጧል።

    በሽታውን በዘላቂነት ለመከላከልም የማህፀን ጫፍ ካንሰር ክትባትን ከዘጠኝ እስከ 14 ዓመት የዕድሜ ክልል ለሚገኙ ልጃገረዶች እንዲሰጥ መንግስት መወሰኑን አመልክተዋል።

    በቀጣዩ ወር በሚጀምረው ዘመቻም በክልሉም ዕድሜያቸው 14 ዓመት የሞላቸው ከ450 ሺህ በላይ ልጃገረዶች የክትባቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑም ተለይተዋል።

    ክትባቱን የተሳካ ለማድረግ ለጤና ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት ቢሮው ስልጠና መስጠት መጀመሩን የስራ ሂደቱ መሪ ጠቁመዋል።

    “አዲስ የሚጀመረው የክትባት ዘመቻም ስለሚያስገኘው ጠቀሜታ በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች ለህብረተሰቡ ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራ መሰጠት ተጀምሯል” ብለዋል።

    በክልሉ በመጪው ጥቅምት ወር በትምህርት ቤቶች፣ በጤና ተቋማትና አማካኝ በሆኑ ቦታዎች ለሚሰጠው የክትባት ዘመቻ ከአንድ ሺህ በላይ የክትባት መስጫ ጣቢያዎች መዘጋጀታቸውን የገለጹት ደግሞ የጤና ቢሮው የክትባት ፕሮግራም የቴክኒክ አማካሪ አቶ ሙሉጌታ አድማሱ ናቸው።

    RELATED: HEALTH: Breast Cancer Replaces Cervical Cancer as Top Women Illness in Ethiopia

    ክትባቱን በመጀመሪያው ዙር የሚወስዱ ልጃገረዶች ከስድስት ወር በኋላ ክትባቱን ዳግም እንዲወስዱ እንደሚደረግም ተናግረዋል።

    የማህፀን ጫፍ ካንሰር መንስኤው “ሂውማን ፓፒሎማቫይረስ” (Human papillomavirus) በሚባል ኢንፌክሽን የሚመጣ መሆኑን ጠቁመው እናቶች በበሽታው ሲያዙም ሳያውቁት እስከ 20 ዓመታት ሊቆዩ እንደሚችሉ አስረድተዋል።

    ለበሽታው ከሚያጋልጡት ምክንያቶች ውስጥ ልጃገረዶች በለጋነት እድሜያቸው የግብረ ስጋ ግንኙነት መጀመርና ከተለያዩ ሰዎች ጋር ፆታዊ ግንኙነት ማድረግ ተጠቅሰዋል።

    ወደ ህክምና ተቋማት መጥተው ምርመራ በማድረግ ራሳቸውን ከበሽታው መጠበቅ እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

    በሚሰጠው የክትባት ዘመቻም ከአምስት ሺህ በላይ የጤና ባለሙያዎችና ድጋፍ ሰጪ አካላት እንደሚሳተፉም ታውቋል።

    HPV Information Centre የሚባለው ድርጅት እ.ኤ.አ በሀምሌ ወር በ2017 ዓ.ም ባወጣው ሪፖርት ኢትዮጵያ ውስጥ በየ ዓመቱ 7,095 ሴቶች ማህፀን ጫፍ ካንሰር የሚጠቁ ሲሆን፣ በየዓመቱም 4,732 ሴቶች በዚሁ ካንሰር ምክንያት ለሞት እንደሚዳረጉ ዘግቧል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)

    የማህፀን ጫፍ ካንሰር

    Semonegna
    Keymaster

    ኢህአዴግ 11ኛ ድርጅታዊ ጉባኤውን በሀዋሳ ከተማ ጀመረ

    ሀዋሳ ከተማ፣ ደቡብ (ኢዜአ) – የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) ለሶስት ቀናት የሚዘልቀውን ጉባዔውን የደቡብ ክልል ዋና ከተማ በሆነችው ሀዋሳ ማካሄድ ጀምሯል።

    በጉባዔው ቀደም ብለው ድርጅታዊ ጉባዔያቸውን ያጠናቀቁት የኢህአዴግ አራቱ እህት ድርጅቶች (የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ እና የሕዝበ ወያኔ ሀርነት ትግራይ) እና አጋር ፓርቲዎችም ተሳታፊዎች ናቸው፡፡

    በዚህ ጉባዔ ላይ 2 ሺህ የሚጠጉ ተሳፊዎች ታዳሚ ሆነዋል። ከነዚህም 1 ሺህ ያህሉ ተሳፊዎች በድምፅ የሚሳተፉ ናቸው።

    ———————————————-

    ———————————————-

    የውጭ አገራት ወዳጅ ፓርቲዎችን ጨምሮ፣ በአገር ውስጥ ያሉ ተፎካካሪ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማኅበራትና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶችም ከዛሬ ጅምሮ በሚካሔደው ጉባዔ ላይ የሚካፈሉ ይሆናል።

    የኢህአዴግ ሊቀመንበርና የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) 11ኛውን ድርጅታዊ ጉባዔ አስመልክተው በሰጡት መግለጫ በዋናነት በ10ኛው ጉባኤ መግባባት የተደረሰባቸውን አቅጣጫዎች አፈጻጸምን በተመለከተ የበላይ አመራሩ ግምገማ ለጉባኤ ተሳታፊ አባላት የሚቀርብበትና ከዚያም በመነሳት በቀጣይ ሁለት አመታት ተግባራዊ ሊደረጉ የሚገባቸውን ጉዳዮች አቅጣጫ የሚያስቀምጥበት ይሆናል ብለዋል።

    ጉባዔተኛው ከበላይ አመራሩ የሚቅርብለትን መነሻ በመያዝ ባለፉት 27 ዓመታት እንደ ድርጅት ያካሄደውን ጉዞ በመገምገም አገራችን የምትገኝበትን የትግል መድረክ ከግምት ውስጥ በማስገባት ኢትዮጵያ ወደ አዲስ የሰላም፣ የዴሞክራሲና የልማት አቅጣጫ ሊያሸጋግር እንደሚችል በታመነበት አቅጣጫ ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃልም ብለዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵይ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)

    ኢህአዴግ

    ቪድዮ፦ The Oromo Democratic Party (ODP) is the new OPDO, with Abiy Ahmed and Lemma Megersa as its leaders

    Semonegna
    Keymaster

    በኦሮሚያ ውስጥ ከፍተኛ ተቃውሞን ቀስቅሶ የነበረው አዲስ አበባን በዙሪያዋ ካሉ የኦሮሚያ ከተሞች ጋር ያስተሳስራል የተባለው ማስተር ፕላን ተራማጅና አንድ ቀን ተመልሶ ይመጣል ብለው እንደሚያስቡ ኦህዴድ ሊቀ መንበር እና የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት የነበሩት አቶ ኩማ ደመቅሳ ለቢቢሲ ተናገሩ።

    ባለፈው ሳምንት ኦዴፓ (የቀድሞው ኦህዴድ) በጅማ ከተማ ድርጅታዊ ጉባኤውን ባደረገበት ወቅት ተሳታፊ የነበሩት አቶ ኩማ ከቢቢሲ ጋር ባደረጉት አጭር ቆይታ አወዛጋቢ ስለነበሩና እርሳቸው በከፍተኛ የስልጣን ሃላፊነት ላይ በነበሩበት ጊዜ ስለታቀዱና ተግባራዊ ስለተደረጉ ጉዳዮች ምላሽ ሰጥተዋል።

    «ኦሮሞ እና አማራን የሚነጣጥሉ አይሳካላቸውም»

    በተለይ በኦሮሚያ ውስጥ ተቀስቅሶ ለረጅም ጊዜ ለዘለቀው ሕዝባዊ ተቃውሞ መነሻ ምክንያት እንደሆነ የሚነገርለትና ከ2006 ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሎ የነበረው የአዲስ አበባና በዙሪያዋ ያሉ የኦሮሚያ ከተሞች የተቀናጀ ማስተር ፕላንን በተመለከተ የተሳሳተ አመለካከት እንዳለ ተናግረዋል።

    ጉዳዩ ከመፈናቀል ጋር አብሮ ስለመጣ እንጂ «ተራማጅ አስተሳሰብ ነው ብዬ አስባለሁ» በማለት የሚናገሩት አቶ ኩማ፤ ጊዜ ሊወስድ ይችላል እንጂ ማስተር ፕላኑ አንድ ቀን ተመልሶ ይመጣል ብለው እንደሚያስቡ ገልፀዋል።

    ከዚህ በተጨማሪም በተመሳሳይ ኦሮሚያ ውስጥ ለጠንካራ ጥያቄና ተቃውሞ ምክያት የነበረው የአዳማ ከተማን የኦሮሚያ ክልል መዲና እንድትሆንና የክልሉ መስሪያ ቤቶች ወደዚያው እንዲዘዋወሩ መደረጋቸው ይጠቀሳል።

    ስለዚህ ጉዳይ የተጠየቁት አቶ ኩማ ውሳኔው ስህተት እነደሌለበት ያምናሉ። አሁንም ወደኋላ መለስ ብለው ሲመለከቱ «አሁንም ያኔ የነበረኝ አቋም ስህተት ነው ብዬ አላምንም» ካሉ በኋላ፤ «አዳማ የክልሉ ዋና ከተማ ሆና እንደተቀየረች ብትዘልቅ ኖሮ ከተማዋ ታድግ እንደነበር» ሲሉ ገልጸዋል።

    ማንበብዎን ይቀጥሉ፦ «ማስተር ፕላኑ ተመልሶ ይመጣል» አቶ ኩማ ደመቅሳ

Viewing 15 results - 106 through 120 (of 120 total)