ኢህአዴግ 11ኛ ድርጅታዊ ጉባኤውን በሀዋሳ ከተማ ጀመረ

Home Forums Semonegna Stories ኢህአዴግ 11ኛ ድርጅታዊ ጉባኤውን በሀዋሳ ከተማ ጀመረ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #7852
    Semonegna
    Keymaster

    ኢህአዴግ 11ኛ ድርጅታዊ ጉባኤውን በሀዋሳ ከተማ ጀመረ

    ሀዋሳ ከተማ፣ ደቡብ (ኢዜአ) – የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) ለሶስት ቀናት የሚዘልቀውን ጉባዔውን የደቡብ ክልል ዋና ከተማ በሆነችው ሀዋሳ ማካሄድ ጀምሯል።

    በጉባዔው ቀደም ብለው ድርጅታዊ ጉባዔያቸውን ያጠናቀቁት የኢህአዴግ አራቱ እህት ድርጅቶች (የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ እና የሕዝበ ወያኔ ሀርነት ትግራይ) እና አጋር ፓርቲዎችም ተሳታፊዎች ናቸው፡፡

    በዚህ ጉባዔ ላይ 2 ሺህ የሚጠጉ ተሳፊዎች ታዳሚ ሆነዋል። ከነዚህም 1 ሺህ ያህሉ ተሳፊዎች በድምፅ የሚሳተፉ ናቸው።

    ———————————————-

    ———————————————-

    የውጭ አገራት ወዳጅ ፓርቲዎችን ጨምሮ፣ በአገር ውስጥ ያሉ ተፎካካሪ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማኅበራትና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶችም ከዛሬ ጅምሮ በሚካሔደው ጉባዔ ላይ የሚካፈሉ ይሆናል።

    የኢህአዴግ ሊቀመንበርና የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) 11ኛውን ድርጅታዊ ጉባዔ አስመልክተው በሰጡት መግለጫ በዋናነት በ10ኛው ጉባኤ መግባባት የተደረሰባቸውን አቅጣጫዎች አፈጻጸምን በተመለከተ የበላይ አመራሩ ግምገማ ለጉባኤ ተሳታፊ አባላት የሚቀርብበትና ከዚያም በመነሳት በቀጣይ ሁለት አመታት ተግባራዊ ሊደረጉ የሚገባቸውን ጉዳዮች አቅጣጫ የሚያስቀምጥበት ይሆናል ብለዋል።

    ጉባዔተኛው ከበላይ አመራሩ የሚቅርብለትን መነሻ በመያዝ ባለፉት 27 ዓመታት እንደ ድርጅት ያካሄደውን ጉዞ በመገምገም አገራችን የምትገኝበትን የትግል መድረክ ከግምት ውስጥ በማስገባት ኢትዮጵያ ወደ አዲስ የሰላም፣ የዴሞክራሲና የልማት አቅጣጫ ሊያሸጋግር እንደሚችል በታመነበት አቅጣጫ ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃልም ብለዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵይ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)

    ኢህአዴግ

    ቪድዮ፦ The Oromo Democratic Party (ODP) is the new OPDO, with Abiy Ahmed and Lemma Megersa as its leaders

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.