Search Results for 'ኢትዮጵያ'

Home Forums Search Search Results for 'ኢትዮጵያ'

Viewing 15 results - 466 through 480 (of 730 total)
  • Author
    Search Results
  • Anonymous
    Inactive

    በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ለአንድ ተማሪ ሞት ምክንያት የሆነውን ድርጊት የከተማው ነዋሪዎች እና የክልሉ መንግስት አወገዙ።
    —-

    ባሕር ዳር (አብመድ) – በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ለአንድ ተማሪ ሞት ምክንያት የሆነውን ድርጊት የከተማው ነዋሪዎች እና የክልሉ መንግስት አወገዙ። የደብረ ማርቆስ ከተማ ነዋሪዎች ስለ ችግሩ እና ስለ ቀጣይ የተማሪዎች ሰላም ተወያይተዋል።

    ድርጊቱን ያወገዙት ተወያዮቹ ችግር ፈጣሪዎቹን በማጋለጥ ለጸጥታ አካላት እንደሚሰጡም ቃል ገብተዋል። እስካሁን በድርጊቱ የተጠረጠሩ ተማሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውም ነው በውይይቱ የተገለፀው።

    ውይይቱን የተከታተለው ጋሻዬ ጌታሁን እንዳደረሰን መረጃ ሌሎች የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የጸጥታ ስጋት እንዳይደርስባቸው ከጎናቸዉ እንደሚሆኑ ነዋሪዎቹ አረጋግጠዋል።

    በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ እሁድ ግንቦት 18/2011 ዓ.ም የአንድ ተማሪ ህይወት ሲያልፋ ሶስት ተማሪዎች ቆስለዉ በህክምና ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል። የችግሩ መንስኤ እስካሁን እንዳልታወቀም ነው ማብራሪያ የተሰጠው።

    የክልሉ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤትም የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት እና ሕዝብ በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪ ላይ በደረሰዉ የሕይወት መጥፋት ከልብ ከማዘን ባሻገር ድርጊቱን አጥብቀው እንደሚያወግዙት ገልጿል።

    የክልሉ መንግሥት ከሕዝቡና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር ጥቃት አድራሾችን ተከታትሎ ለሕግ እንደሚያቀርብም ነው ያስታወቀው።

    ለሟች ቤተሰቦች፣ ለጓደኞቹና ለዩኒቨርሲቲው ማሕበረሰብም መጽናናትን ተመኝቷል።

    ምንጭ፦ አብመድ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    Anonymous
    Inactive

    ኢትዮጵያና ቻይና የኮሙኒኬሽንና ብሮድካስት ሳተላይት በጋራ ለመገንባት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ
    —–
    ኢትዮጵያና ቻይና የኮሙኒኬሽንና ብሮድካስት ሳተላይት በጋራ ለመገንባት የሚያስችላቸውን ፍሬምወርክ ስምምነት ተፈራረሙ።

    ስምምነቱን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ኢንስቲቲዩት ዳይሬክተር ዶክተር ሰለሞን በላይ እና የቻይና ሮኬት ካምፓኒ ምክትል ፕሬዝዳንት ሃን ቺንፒንግ ተፈራርመውታል።

    ግንባታው በኢትዮጵያና ቻይና ባለሙያዎች ትብብር የሚከናወን ሲሆን÷ 50 በመቶ የሀገር ውስጥ እሴት እንደሚጠቀም ነው የተገለጸው።

    በግንባታው የሚሳተፉ ኢትዮጵውያን ከቻይና የቴክኖሎጂ ልምዱን ይወስዳሉ ነው የተባለው።

    ተጠቃሚ መለየት፣ ማስተባበር፣ ፍላጎትና ቦታ መረጣ የመሳሰሉት ተግባራት ሰኔ ወር ላይ ይጀመራሉ ተብሎ ይጠበቃል።

    የአሁኑ የሳተላይት ግንባታ ፍሬምወርክ ስምምነት ሳተላይትን የስራ እድል መፍጠሪያና ሃብት ማመንጫ ማድረግን ታሳቢ ያዳረገ እንደሆነ ነው የተገለጸው።

    በሁለቱ ሀገራት ትብብር የተሰራችው የመጀመሪያዋ የመሬት ምልከታ ሳተላይት ህዳር 20 ቀን 2012 ዓ.ም ወደ ህዋ ትላካላች ተብሎ እንደሚጠበቅም ነው ከኢፌዴሪ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ የሚያመላክተው።

    ምንጭ፦ ኤፍ.ቢ.ሲ

    Semonegna
    Keymaster

    ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ከዓርብ ጀምሮ እስካሁን በውል ባልታወቀ ምክንያት የተቀሰቀሰው ግጭት እስከዛሬ (ሰኞ ግንቦት 19 ቀን 2011 ዓ.ም.) ድረስ አለመረጋጋቱን ተማሪዎቹ ገልጸዋል።

    ደብረ ማርቆስ (ቢቢሲ አማርኛ)– በአማራ ክልል ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ በተፈጠረ ግጭት አንድ ተማሪ መሞቱን ተማሪዎች ለቢቢሲ ገለጹ። ሟች ሰዓረ አብርሃ እንደሚባልና የሦስተኛ ዓመት የምጣኔ ሀብት ትምህርት ክፍል (economics department) ተማሪ እንደነበረ ቢቢሲ አማርኛ ዘግቧል።

    በዩኒቨርስቲው ከዓርብ ጀምሮ የተቀሰቀሰው ግጭት እስከዛሬ (ሰኞ ግንቦት 19 ቀን 2011 ዓ.ም.) ድረስ አለመረጋጋቱን ተማሪዎቹ ገልጸዋል።

    የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የሕዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ኃላፊ አቶ ደሳለው ጌትነትም በተቋሙ ከባለፈው አርብ (ግንቦት 16 ቀን) 12 ሰዓት ጀምሮ ግጭቶች መኖራቸውን አረጋግጠዋል።

    በዚህም አርብ ግንቦት 16 ላይ 3 ልጆች ጉዳት እንደደረሰባቸው ተናግረው ልጆቹ አሁን ሆስፒታል ይገኛሉ ብለዋል። የተጎዱት ተማሪዎች በባህር ዳር እና አዲስ አበባ ሪፈራል ተጽፎላቸው ወደዚያው መወሰዳቸውንም ጨምረው ያስረዳሉ። በግጭቱ ሁለት ተማሪዎች በድንጋይና በስለት ጉዳት እንደደረሰባቸው የዓይን እማኞቹ ለቢቢሲ አረጋግጠዋል።

    በተፈጸመበት ጥቃት ምክንያት አንደኛው ተማሪ ወዲያውኑ ህይወቱ ማለፉንና ሌላኛው ተማሪ ደግሞ ለሕክምና እርዳታ ወደ ባህር ዳር መወሰዱን ከተማሪዎቹ ለመረዳት ተችሏል።

    የረብሻውን ምክንያት እስካሁን ማረጋገጥ አልቻልንም ያሉት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊው አርብ ዕለት ተሳትፎ የነበራቸውን የተወሰኑ ልጆች ፖሊስ ተከታትሎ ከግቢ ውጭ ይዟቸው ፖሊስ ጣቢያ ስለሚገኙ ጉዳያቸው እየተጣራ ነው በማለት የግጭቱ መንስዔ ከዚያ በኋላ ተጣርቶ የሚታወቅ ይሆናል ብለዋል።

    በአሁኑ ሰዓት በዩኒቨርሲቲው አዳራሽ የተጠለሉ ተማሪዎች እንዳሉ የተገለፀ ሲሆን ትላንት የሟችን አስክሬን ለመሸኘት የተሰበሰቡ ተማሪዎችም “ትምህርቱ ይቅርብን ወደ መጣንበት መልሱን” በማለት ለዩኒቨርሲቱው ፕሬዚዳንት ጥያቄ ማቅረባቸውን ነግረውናል።

    የዚህን ዜና ተጨማሪ መረጃ ቢቢሲ አማርኛ ላይ ማንበብ ይቀጥሉ

    ከዚያው ከአማራ ክልል ሳንወጣ፥ የደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ በምዕራብ እና በማዕከላዊ ጎንደር ዞኖች ለተፈናቀሉ ወገኖች ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ ማድረጉን የአማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት (አብመድ) ዘግቧል። በቀጣይም ከ967 ሺህ ብር በላይ ድጋፍ ለማድረግ መዘጋጀቱን ዩኒቨርሲቲው አስታውቋል።

    ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ለአብመድ በጻፈው ደብዳቤ እንዳመላከተው ተፈናቃዮችን መልሶ ለማቋቋም ከዚህ በፊት በአማራ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ፎረም በኩል የ1 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርጓል። አሁን ደግሞ የዩኒቨርሲቲው ሠራተኞች 967ሺህ 786 ብር ከወር ደመወዛቸው አዋጥተው ድጋፍ አድርገዋል።

    የተፈናቀሉ ወገኖችን ለማቋቋም በሚደረገው አገራዊ እና ክልላዊ የገንዘብ ማሰባሰብ ሂደት ተማሪዎችም የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ማበርከታቸውንም ዩኒቨርሲቲው አስታውቋል።

    ከዚህ በፊት ሠራተኞች እና ዩኒቨርሲቲው የተፈናቀሉ ወገኖችን መልሶ ለማቋቋሙ አንድ ሚሊዮን ብር በአማራ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ፎረም በኩል ድጋፍ ማድረጉም ታውቋል።

    ምንጮች፦ ቢቢሲ አማርኛ እና አብመድ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ


    Semonegna
    Keymaster

    የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ያቀረበውን ይህን ከወለድ ነፃ የዳያስፖራ የቤት መግዣ የፋይናንስ አገልግሎት በውጭ የሚኖሩ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ ሌሎች በዚህ አገልግሎት መጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ ሊጠቀሙበት ይችላሉ።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን ኢትዮጵያ ውስጥ የመኖሪያ ቤት ባለቤት ለማድረግ የሚያስችል ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ይፋ አደረገ። አገልግሎቱ ሙስሊሙን ህብረተሰብ ጨምሮ ሌሎች የወለድ አገልግሎትን የማይፈልጉ ዳያስፖራዎችም እንዲጠቀሙበት የተዘጋጀ ነው።

    የባንኩ የጥራት ቁጥጥር ምክትል ፕሬዚዳንት ወይዘሮ እመቤት መለሰ አዲሱን ከወለድ ነፃ የዳያስፖራ ፋይናንስ አገልግሎት አስመልክተው በሰጡት አስተያየት “ለመኖሪያ ቤት መግዣ የሚውለው ከወለድ ነፃ የዳያስፖራ ፋይናንስ አገልግሎት ከዚህ ቀደም ከቀረቡትና ዳያስፖራውን ከሚመለከቱ የባንክ አገልግሎቶች በተለየ መንገድ ይተገበራል” ብለዋል።

    ዳያስፖራው ወዲዓ’ህ የቁጠባ ሒሳብን በመጠቀም ቢያንስ 20 በመቶ የሚሆነውን ገንዘብ በእንግሊዝ ፓውንድ፣ በአሜሪካን ዶላርና በዩሮ መቆጠብ ከቻለ፣ የፋይናንስ ጥያቄውን ለባንኩ በማቅረብ መስተናገድ እንደሚችል ወይዘሮ እመቤት ተናግረዋል።

    ግንባታው የተጠናቀቀና ጅምር ቤት ለመግዛት የሚውለው የፋይናንስ አገልግሎት በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የመኖሪያ ቤት ችግር እንቅፋት እንዳይሆንባቸው ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ታስቦ ለዳያስፖራው የተዘጋጀ ከወለድ ነፃ የፋይናንስ አገልግሎት ነው። የፋይናንስ አገልግሎቱን መስፈርቶች ማሟላት የሚችሉ ዳያስፖራዎች በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፎች ወይም በሚኖሩበት አገር በሚገኝ የኢትዮጵያ ኤምባሲ በኩል ቀርበው የወዲዓ’ህ ቁጠባ ሒሳብ በመክፈት መቆጠብ የሚችሉ ሲሆን፣ ለአገልግሎቱ የሚያስፈልገውን ቅድመ ክፍያ በአንድ ጊዜ ወይም በተለያዩ ጊዜያት በመቆጠብ መክፈል ይችላሉ። ለቤት መግዣ የሚውለውን ፋይናንስ እስከ 20 ዓመት በሚደርስ የቆይታ ጊዜ ከፍለው መጨረስ እንዲችሉም ተመቻችቷል።

    የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ያቀረበውን ይህን ከወለድ ነፃ የዳያስፖራ የቤት መግዣ የፋይናንስ አገልግሎት በውጭ የሚኖሩ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ ሌሎች በዚህ አገልግሎት መጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ እንዲጠቀሙበት ወይዘሮ እመቤት ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ 
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    ከወለድ ነፃ


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– የኢፌዴሪ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ትምህርት የማቆም አድማ ላይ የተሰማሩ የሕክምና ተማሪዎችን በተመለከተ ያወጣው መግለጫ

    በተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች የሚገኙ የመጨረሻ ዓመት (intern) ተማሪዎችና ስፔሻሊቲ (resident) ተማሪዎች ላነሱዋቸው የተለያዩ ጥያቄዎች ክቡር የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ከሴክተሩ ባለሙያዎች እና ተማሪዎች ጋር ሲወያዩ ተማሪዎች ላነሷቸው ጥያቄዎች በሰጡት አመራር የተለያዩ እርምጃዎች ተወስደዋል።

    በዚሁ መሠረት፦

    1. የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎችን በተመለከተ የሕክምና ተማሪዎች እንደ ሌሎች ተማሪዎች የወጣባቸውን ትክክለኛ ወጪ እንዲጋሩ (cost sharing) እና ከዚህ በፊት አምስት መቶ ሺህ (500,000) ብር ይፈርሙ የነበሩት እንዲቀር መደረጉ፤
    2. የተግባር ትምህርት አተገባበርን በተመለከተ የአዳርና ለረዥም ጊዜ በሥራ ላይ መቆየት ጋር ተያይዞ የሥርዓተ ትምህርት ፍተሻ እንዲደረግና የውሳኔ ሃሳብ እንዲቀርብ፤
    3. የማስተማርያ ሆስፒታሎችን ለሥራ ምቹ ማድረግንና ተያያዥነት ያላቸውን ጥያቄዎች በተመለከተ ተቋማት ባላቸው አቅም በፍጥነት እርምጃ እንዲወስዱ እየተደረገ መሆኑን በተለያዩ አካላት መገለጫ መሰጠቱ ይታወሳል።

    በተጨማሪም እነዚህንና ሌሎች ጉዳዮችን በዝርዝር አጥንቶ ዘላቂ መፍትሔ ለመሰጠት አራት ግብረ ሃይል ተቋቁመው ወደ ሥራ ገብተዋል። ይህ እንዳለ ሆኖ በጥቂት ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርት ያቋረጡ ተማሪዎች ተስተውለዋል። ይህ በፍጹም ተቀባይነት የሌለው መሆኑን ተገንዝበው ተማሪዎቹ በፍጥነት ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ እያልን ከሰኞ ግንቦት 11 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ ወደ ትምህርታቸው የማይመለሱትን ተማሪዎች ተቋማት ባላቸው የመማር ማስተማር (academic) ሕግ ቀጣይ እርምጃ እንዲወስዱ መመሪያ የተላለፈ መሆኑን እንገልጻለን።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    የሕክምና ተማሪዎችን


    Semonegna
    Keymaster

    መንግሥት ሆይ፥ የጤና ባለሙያውን ጥያቄ ከልብህ አድምጥና መፍትሄ ስጥ
    (ዶ/ር አክሊሉ ደበላ)

    አሁን ነገሮች ወዴት እያመሩ እንደሆነ ሁሉም እያየው ነው። አነሰም በዛ መንግሥትም በዚህ ምክንያት መጨነቁ አልቀረ። በዚህ ችግር የሚነካካ አካል ብዙ እንደሆነም አምናሁ። የጤና ባለሙያው፣ መንግሥትና ሕዝብ ሳይወዱ በግድ ባለጉዳዮች ናቸው። የባለሙያው ጥያቄ ግልጽ ሆኖ ቀርቧል። በዚህ ጥያቄ ላይ የተለያየ አስተያየት ያላቸው ሰዎች አሉ። የሚሰጡትም አስተያየቶች ነገሩን የከፋ እንዳያደርጉ መጠንቀቅ ከሁሉም ይጠበቃል።

    የሐኪሙ ጥያቄ ዛሬ የበቀለ የሚመስላቸው ተሳስተዋል። ጥያቄውም ሆነ ተግባር ያልታየበት የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር መልስ ሲንከባለሉ ቆይተው ዛሬ ወደ አደባባይ የወጡ ናቸው። “እስከዛሬ የት ነበራችሁ?” ማለት ቢቻልም በጥልቅ ሲታሰብ ልክ አይሆንም። የመቶ ዓመት ጥያቄ እንኳን ቢሆን የሆነ ጊዜ በሥርዓቱ መመለስ አለበት። ችግሮቹን የፈጠረ የዶ/ር አቢይ መንግሥት ነው ያለ የለም፣ መመለስ ያለበት ግን አሁን እሱ ነው። ሕዝቡ በደፈናው በሐኪሙ ላይ መጥፎ አስተያየት ከመስጠቱ በፊት ነገሩን አዙሮ አዟዙሮ ቢያስብ መልካም ነው። ዛሬ ገንፍሎ የወጣው ጩኸት የፖለቲካ ሁኔታ ምቹ ስለሆነ ብቻ አይደለም (መሆኑ አንድ ነገር ቢሆንም)፤ ይልቅስ እየተባባሰ የመጣው የችግሩ ተፈጥሮ ራሱ የመገንፈል ልክ ላይ ደርሶ ነው እንጂ። እዚህ ላይ የደረሰውን ጉዳይ ሁሉም በጥንቃቄ ካልያዘ ጉዳቱ ከተፈጥሯዊነት ይልቅ ሰው-ሠራሽ አንዳናደርገው።

    ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የተጠየቀውን ነገር ለመመለስ ምን ያህል እምነት የሚጣልበት አካል እንደሆነ አላውቅም። ነገሮችን እየመለሰ ያለበት አኳኋን ግን መልካም አይደለም። እስከሚገባኝ ድረስ በውይይቱም ላይ ለመመለስ ቃል የገባባቸው ጉዳዮች ራሱ ሲፈጽም የነበረ ሕግን የጣሰ አሠራር ነው። የሀገሪቷን ሕግ ጥሶ ወጪ መጋራትን (cost-sharing) ቢያስተካክል ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ሲሠራ የነበረውን የወንጀል ሂሳቡን አወራረደ ይባላል እንጂ የሐኪሙን ጥያቄ መለሰ ተብሎ ለዜና የሚቀርብ ጉዳይ አልነበረም። ወሃ የማይቋጥር ጥቃቅን ነገሮች አስር ጊዜ እንደሰበር ዜና የሚለጥፍበት መንፈስ ግን አስቂኝ ነው። ስጠረጥር ግን ባለሙያውን ንዴት ውስጥ በመክተት ይበልጥ እንዲገፉበት የፈለገም ይመስለላል። ከሳምንታት በፊት ሰምተን ያለቀውን ጉዳይ ዛሬ በሰበር ዜና ባገኘው ሚዲያ ሁሉ ማስተጋባት የቅንነት ልቡን የሚታመን አያደርገውም። ጊዜያዊ ስሜቱን ማብረድም ሆነ ዘላቂ መፍትሄውን በሰከነ መንገድ መመለስ ይጠበቅበታል እንጂ የብልጣብልጥነት ጨዋታ በመገናኛ ብዙሃን (ሚዲያ) በኩል መጫወት አይጠቅምም።

    ሌላው ከዶ/ር አቢይ ጋር ተያይዞ፡- እንደሚታወቀው ባለፈ ከሕክምና ማኅበረሰብ ጋር ያደረገው ውይይት ብዙዎችን አስከፍቷል። በዚህም የተነሳ የብዙ ሐኪሞች የሥራ ሞራል ወርዷል፣ የብዙዎች ስሜት ቀዝቅዟል። በዚህ ብቻም የተነሳ ብዙ ህመምተኞች ይጎዳሉ፤ ተጎድተዋል። ይህ እንግዲህ ከጥያቄዎቻቸው ጋር ቀጥተኛ ተዛምዶ የሌለው ተጨማሪ ችግር ነው። የአንድ አገር መሪ በተናገረው ነገር የሚበላሸው ብዙ ነገር እንደሆነ ግልጽ ነው። የዚህንም ፍሬ አይተነዋል። ለዚህ ትክክለኛው መድኃኒት እርምት ነው። ስለ ባለሙያው ክብርም ባይሆን ስለሚበደሉቱ ህመምተኞች ሲባል፣ የተነገረውም በአደባባይ ስለሆነ፣ የዶ/ር አቢይ መንግሥት በአደባባይ ይቅርታ ቢጠይቅ አገር ትጠቀማለች።

    ሌላው ከሕክምና ስነምግባርና ሀገሪቱ ካለችበት ሁኔታ አንጻር የተለያየ አስተያየት የሚሰጡ ሰዎች አሉ። እርግጥ ነው ሀገሪቷ ገና አልተረጋጋችም፤ እርግጥ ነው የሐኪሞቹን ጥያቄ ለራሳቸው የፖለቲካ አጀንዳ ሊያውሉ የሚፈልጉ አካላት ሊኖሩ ይችላሉ። ይህን ለማስቀረት ኃላፊነት ያለበት ደግሞ ጠያቂው ሐኪም ብቻ ሳይሆን ተጠያቂው መንግሥትና ተመልካቹ ማኅበረሰብም ጭምር ነው። መመለስ ባለበት መንገድ ካልተመለሰ ባልተፈለገ መንገድም ሊወድቅ ይችላል፤ ስጋቱ የሁሉም ነው። ይህን ተፈጥሯዊ ዕጣውን በመዘንጋት ከየአቅጣጫ ጠያቂውን ብቻ መውቀስ ተገቢ አይደለም፤ ጥያቄውንም ማራከስ ይሆናል። እርግጥ ነው ሕክምና በተቻለው መጠን ሁሉ ህመምተኛን ማስቀደምን ይጠይቃል። ይህን ጠያቂዎቹም ያውቃሉ። ይሁንና የሕክምና ሥራ የሚሠራው ሰው ሆኖ መኖር ከተቻለ ብቻ መሆኑን መዘንጋት የለብንም። በብዙ ቦታዎች ያለው እውነታ ደግሞ የደኅንነት ስጋት ጉዳይ ስለሆነ ከሁሉም ይቀድማል– ከሕክምናም። ይህን ችግር ግን ብዙ ሰው የተረዳው አይመስለኝም። ብዙዎቹ ጥያቄዎች ደግሞ ቀጥታ ለህሙማኑ ጥቅም የሚውሉ ናቸው። በአሠራር ብልሹነት መሥራት አልቻልንም ማለት እንደ አገር ቢታሰብ ትልቅ ችግር ነው እንጂ የሕክምና ባለሙያ ጥያቄ ብቻ ተደርጎ ባልተወሰደ ነበር።

    ከማኅበራዊ ድረ-ገጾች ጩኸት እስከ ሥራ ማቆም ተደርሷል። ነገሮች በዚሁ የሚሄዱ ከሆነ ደግሞ ሥራ ማቆሙ እየተስፋፋ ሄዶ የብዙዎቹ ሕይወት እስከ መቅጠፍ ሊደርስ ይችላል። ማኅበራዊ ቀውስ ሊያስከትል የሚችል ጉዳይም ሊሆን ይችላል እና ሁሉም ቆሞ ቢያስብበት ሸጋ ነው። “መንግሥትስ በዚህ አስቸጋሪ ጊዜ ላይ ሆኖ የሕክምና ባለሙያን ጥያቄ መመለስ ይችላል ወይ?” ከተባለ “አዎ ይችላል።” ምናልባትም ጊዜ የሚፈልጉ አንዳንድ ከባድ ጥያቄ የሆኑበትም ካሉ አመላለሱን ያማረ በማድረግ መተማመንን መፍጠር ይችላል። አሁን እየሄደ ባለበት መንገድ ግን አይደለም። ለዚህም ነው “መንግሥት ሆይ፥ የጤና ባለሙያውን ጥያቄ ከልብህ አድምጥና መፍትሄ ስጥ!” የምንለው።

    አክሊሉ ደበላ (የሕክምና ዶ/ር)
    ——
    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    መንግሥት የጤና ባለሙያዎች ጥያቄ


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር በአገራችን በሁሉም አቅጣጫ የተጠናከረ የመዳረሻ ልማት፣ የቅርስ ጥገናና እንክብካቤ ሥራዎችን በተቀናጀ መልኩ ለማከናውን እንዲያስችል በሙያው የተሠማሩ ከመሀንዲሶች እና የሥነ-ሕንፃ ባለሙያዎች ጋር ግንቦት 6 ቀን 2011 ዓ.ም. አዲስ አበባ ውስጥ በጌት ፋም ሆቴል ምክክር ተካሄደ።

    በመክፈቻው ላይ ተገኝተው የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት ክብርት ዶ/ር ሂሩት ካሳው የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ሲሆኑ፣ በመክፈቻ ንግ ግራቸውም የመርሐ ግብሩን ዓላማ “በኢትዮጵያ ሥነ-ሕንፃ ዲዛይን ጥበብ ከጥንት አባቶቻችን ዘመን ጀምሮ የነበረን ብሎም ዓለምን እስከ ዛሬ ድረስ የሚያስደምሙ ሕንፃ ጥበቦች አሁንም አሉን። እንደሚታወቀው በዓለም የሥነ-ሕንፃ ጥበብ ታሪክ የባቢሎናዊያን፣ የግሪኮች፣ የሮማውያን፣ የባይዛንታይን፣ የመካከለኛ ዘመን፣ የዘመናዊው (modern) ሥነ-ሕንፃ ብለን ማየት የምንችል ይሆናል። በኢትዮጵያ ሥነ-ሕንፃ ታሪክ ቅድመ አክሱም (የዳዓማት)፣ የአክሱማውያን ስልጣኔ፣ የዛጉዌ ስርወመንግስት ሥልጣኔ፣ የሰሎሞኒክ፣ የጎንደሮች ዘመን ሥልጣኔን ማውሳት ይቻላል። አንድ ሥነ-ሕንፃ ሲታነፅ በዋናነት የዚያን ዘመን ማኅበራዊ አደረጃጀት እና የተደረሰበትን አጠቃላይ የዕድገት ደረጃ ከማሳየቱም በላይ በየዘመኑ ያሉ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ሁኔታዎችን ፍንትው አድርጎ የማሳየት ጥበብ አለው” ብለዋል።

    ክብርት ሚኒስትሯ አክለውም “በሀገራችን የአርክቴክቱና የኢንጂነሩ የጥበብ አሻራዎች ለዚህ ላለንበት ዓለም እያበረክቱት ያለው ሙያዊ ድጋፍ ቀላል ግምት የሚሰጠው አለመሆኑንና በሀገር በቀል የሥነ-ሕንፃ ጥበባችን ዓለም ወደኛ እንዲመለከተን አስተዋጽኦቸው ከምንም በላይ የሚደነቅ ነው። አርክቴክቱና አንጂነሩ በሙያው የማኅበረሰቡን እምነት፣ ታሪክና ማንነት በሥነ-ሕንፃ ጥበብ ውስጥ በማኖር ማሳየት በመቻሉ ዘመን ተሸጋሪ አደርጎታል። ስለሆነም በዛሬው ዕለት የምናካሂደው ውይይት በመዳረሻ ልማት፣ በቅርስ ጥገናና እንክብካቤ እንዲሁም በኢትዮጵያ እየተገነቡ ያሉ ሕንፃዎች ኢትዮጵያዊ መገለጫነት የሌላቸው በመሆኑ እንዴት አብረን እንሥራ ብለን ስንነሳ በመጀመሪያ ከአርክቴክቶችና አንጂነሮች ጋር በመሆን የጋራ ቅርሶቻችንን የማወቅ፣ የመለየትና የማስተዋወቅ ሥራ፣ የቅርስ ጥገናና እንክብካቤ ሥራ በራስ ዕውቀት እንዲሆን በማድረግ በቅርስ ጥበቃ ኢትዮጵያዊ መልክ እንዲኖራቸው፣ የዕውቀት ሽግግርና ሕዝብ ሕህዝብ የማገናኘት ሥራ በአንድ ላይ ተሰባስበን የምንሠራበትና የጋራ አቅጣጫ የምንይዝበት ነው በማለት መድረኩን ክፍት አድርገዋል።

    SEMONEGNA on Social Media: FacebookTwitterInstagramPinterest | Video | Forum

    በመቀጠል ሦስት ርዕሰ ጉዳዮች የመወያያ ጥናታዊ ጽሑፎች የቀረቡ ሲሆን፣ እነዚህም በአገራችንን ቅርሶች ነባራዊ ሁኔታ ዳሰሳዊ ጥናት በአቶ ኃይሉ ዘለቀ ከቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን፣ በዘመናዊ የቅርስ አመራርና አስተዳደር ወቅታዊ ቁመና በረ/ፕሮፌሰር ሀሰን ሰዒድ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና በተጠናከረ የመዳረሻ ልማት በአቶ ቴዎድሮስ ደርበው ከባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር የቱሪስት አገልግሎቶች ብቃት የማረጋገጥ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ናቸው።

    ጥናታዊ ጽሑፎችን ያቀረቡ ባለሙያዎች ተንተን ባለመልኩ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ የቅርስ አስተዳደር ሁኔታ ምን ይመስል እንደነበረ ከታሪካዊ ዳራው ጀምሮ የሀብቱ ጥበቃና እንክብካቤ የመንግስትና የሕዝብ ፍላጎት ላይ የተመሠረቱ መሆኑ አመላክተዋል። የሀብቱ ጥበቃና እንክብካቤ በግለሰብ፣ በማኅበረሰብ እና የባለሙያው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑን በተያዘላቸው ጊዜ ቅደም ተከተል ገለፃ አድርገዋል።

    በውይይቱም እያንዳንዱ ባለሙያው በቅርስ ጥገናና እንክብካቤ ዙሪያ በዕውቀትም፣ በሀሳብም በጉልበትም መደግፍ እንዲችል በተደራጀ መልኩ አቅም እንዲፈጠርለት የተጠየቀ ሲሆን በመዳረሻ ልማት (በከተማ ግንባታ) እየታዩ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ በውይይቱ የተሳተፉ መሀንዲሶች እና የሥነ-ሕንፃ ባለሙያዎች እንደአገር የሚሠሩ የሥነ-ሕንፃ ሥራዎችን የዲዛይን ውድድር ውስጥ መሳተፍ እንዲችሉ ዕውቅና በመስጠት አገራዊ ቅርጽ እንዲይዙ ማድረግ ወሳኝ መሆኑ፣ በመዳረሻ ልማት ዘርፍ የሚሠማሩ ዜጎች የኢትዮጵያዊ ማንነት መገለጫ ያላቸው ሕንፃዎች እንዲኖረን በሕንፃ ግንባታ መስክ ትኩረት የሚሰጥ አስገዳጅ ቅድመ ትኩረታዊ ስልት (strategy) እንደአገር ሊኖረን ይገባል።

    ምንጭ፦ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር


    Semonegna
    Keymaster

    ዋትስአፕ (WhatsApp) ሰኞ፣ ግንቦት 5 ቀን 2011 ዓ.ም. ይፋ እንዳደረገው፥ ጥቃቱ የተመረጡ የዋትስአፕ ተጠቃሚዎችን (“select number” of users) ዒላማ ያደረገ ነበር፤ የተቀነባበረውም የላቀ ችሎታ ባላቸው ሀከሮች ነው ተብሏል።

    አዲስ አበባ (ኢመደኤ)– የኮምፒውተር መረጃ መዝባሪዎች (ሀከርስ) የዋትስአፕ መተግበሪያን (WhatsApp app) ተጠቅመው ስልኮችና ሌሎችም የኤሌክትሮኒክስ መገልገያዎች ላይ መሰለያ ጭነው እንደነበረ ተረጋገጠ።

    መሰለያውን የጫኑት የዋትስአፕ መተግበሪያ ላይ ያለ ክፍተትን ተጠቅመው ነው ተብሏል።

    በዓለም ላይ 2.3 ቢሊዮን ሰዎችን ተጠቃሚ በማድረግ ቀዳሚ ማኅበራዊ ሚዲያ (social media) በሆነው ፌስቡክ (Facebook) ስር የሚተዳደረው ዋትስአፕ ይፋ እንዳደረገው፥ ጥቃቱ የተመረጡ የዋትስአፕ ተጠቃሚዎችን (“select number” of users) ዒላማ ያደረገ ነበር፤ የተቀነባበረውም የላቀ ችሎታ ባላቸው ሀከሮች ነው ተብሏል።

    የለንደኑ ዓለም አቀፍ ጋዜጣ ፋይናንሽያል ታይምስ እንደዘገበው፥ ጥቃቱ የተሰነዘረው ‘ኤንኤስኦ ግሩፕ’ (NSO Group) በተባለ የእስራኤል የደኅንንት ተቋም ነው። ባለፈው ሀሙስ (ግንቦት 1 ቀን 2011 ዓ.ም.) ዋትስአፕ የተፈጠረውን ችግር ማስተካከል ችያለሁ ብሏል።

    ጥቃቱ እንደተሰነዘረ የታወቀው በያዝነው ወር መባቻ ላይ ሲሆን፥ ሰኞ ዕለት (ግንቦት 5 ቀን 2011 ዓ.ም.)  ዋትስአፕ 1.5 ቢሊየን ተጠቃሚዎቹ የተሻሻለውን መተግበሪያ እንዲጭኑ (‘update’ እንዲያደርጉ) ጠይቆ ነበር።

    መሰለያ የጫኑት አካሎች በዋትስአፕ መሰለል ወደሚፈልጉት ግለሰብ ይደውላሉ። ከዛም መሰለያውን ይጭናሉ። ግለሰቡ ስልኩን ባያነሳም እንኳን መሰለያውን ከመጫን አያግዳቸውም ተብሏል። ፋይናንሽያል ታይምስ እንዳለው ከሆነ ጥሪ ያደረገው አካል ማንነት ከደዋዮች ዝርዝር (call log) ይጠፋል።

    ዋትስአፕ ለቢቢሲ እንዳሳወቀው፥ ለመጀመርያ ጊዜ ይህ ክፍተት መፈጠሩን ያስተዋለው የድርጅቱ የደኅንነት ክፍል (security team) ነበር። ወዲያው ለሰብአዊ መብት ተሟጋች ቡድኖች እንዲሁም ለአሜሪካ የፍትህ ቢሮ (Department of Justice) አሳውቀዋል።

    “ጥቃቱ ከግል ድርጅት መሰንዘሩን የሚያሳይ ምልከት አለ። ከመንግሥት ጋር በመሆን ያልተፈለገ የስለላ ሶፍትዌር (spyware) በመጠቀም ስልክ መቆጣጠር የሚያስችል ነው” ሲሉ የዋትስአፕ ባለስልጣናት ለመገናኛ ብዙኀን ገልጸዋል።

    ‘ኤንኤስኦ ግሩፕ’ ከመንግሥት ፍቃድ የተሰጣቸው ተቋማት ወንጀልን ለመከታከልና የሽብር ጥቃት እንዳይደርስ ለማድረግ እንዲያውሉት አልሞ የሠራው ነው። ሆኖም አሠራሩ ያላግባብ ጥቅም ላይ ውሎ ከሆነ ምርመራ ይደረጋል ተብሏል።

    ዋትስአፕ ምን ያህል ሰዎች ጥቃቱ እንደደረሰባቸው ለማወቅ ጊዜው ገና ነው ብሏል።

    ከዚህ ቀደም በ’ኤንኤስኦ ግሩፕ’ ጥቃት ደርሶብኝ ነበር ያለው የመብት ተከራካሪው አምነስቲ ኢንተርናሽናል (Amnesty International)፤ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች መሰል ጥቃት ሊደረስባቸው እንደሚችል ስጋት ነበረን ብሏል።

    የአምነስቲ ኢንተርናሽናል የቴክኖሎጂ ክፍል ዳይሬክተር ዳና ሌግሌተን (Danna Ingleton) እንዳሉት፥ ታዋቂ የመብት ተሟጋቾችና ጋዜጠኞችን ለመቆጣጠር በመንግሥታት ጥቅም ላይ የሚውል አሠራር ነው።

    የእስራኤል መከላከያ ሚንስትር የ’ኤንኤስኦ ግሩፕ’ን ፍቃድ እንዲቀማ ለመጠየቅ በአምነስቲ ኢንተተርናሽናል የተመራ የፊርማ ስብስብ ቴል አቪቭ ፍርድ ቤት ይቀርባል።

    ምንጭ፦ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ (ኢመደኤ) / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ዋትስአፕ


    Semonegna
    Keymaster

    በምክክር በድረኩም የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ አዲሱ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሐብታሙ አበበ ዩኒቨርሲቲውን በታታሪነት፣ በታማኝነት እና በቅንነት በማገልገል ዩኒቨርሲቲውን የልሂቃን ተቋም እና የመጀመሪያ ተመራጭ ዩኒቨርሲቲ ለማድረግ ተግተው እንደሚሠሩ ገልጸዋል።

    ሆሳዕና ከተማ (ሰሞነኛ)– ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ለአራት ወራት ያህል ለዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንትነት መረጣ ሲያካሂድ ቆይቶ፥ ለመጨረሻ ዙርም ዶ/ር ሐብታሙ አበበ፣ ዶ/ር ኑሪ ላፌቦ እና ዶ/ር አብርሃም አለማየሁ አልፈው ነበር። ከእነዚህ ሦስት ዕጩ ተወዳዳሪዎች መካከልም ዶ/ር ሐብታሙ አበበ በአጠቃላይ ውጤት 69.57% በማስመዝገብ ለዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንትነት ብቁ መሆናቸውን አስመስክረው፣ የኢፌዴሪ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚያዝያ 24 ቀን 2011 ዓ.ም. ለዩንቨርሲቲውና ለሚመለከታቸው ቢሮዎች በፃፈው ደብዳቤ ዶ/ር ሐብታሙ አበበን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ሆነው ተሹመዋል።

    የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ሆነው የተሾሙት ዶ/ር ሐብታሙ አበበ ለፕሬዝዳንትነት ሲወዳደሩ ያቀረቡትን የዩኒቨርሲቲውን የእድገት ስልታዊ ዕቅድ (University’s Development Strategic Plan) በይበልጥ ለማስገንዘብ እና በዩኒቨርሲቲው ውስጥ የላቀ ታታሪነት፣ ትብብር እና ስኬታማ የመማር ማስተማር፣ የምርምር እና የማኅበረሰብ አገልግሎት ስኬቶችን ለማስመዝገብ የሚያስችላቸውን የመጀመሪያ ዙር ምክክር ከማኅበራዊ ሳይንስ፣ ንግድ እና ምጣኔ ሀብት (Business and Economics)፣ ከግብርናና ከተፈጥሮ ሀብት ኮሌጆች እና ከሕግ ትምህርት ቤት ጋር ግንቦት 5 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምረዋል።

    በምክክር በድረኩም ፕሬዝዳንቱ ዩኒቨርሲቲውን በታታሪነት፣ በታማኝነት እና በቅንነት በማገልገል ዩኒቨርሲቲውን የልሂቃን ተቋም እና የመጀመሪያ ተመራጭ ዩኒቨርሲቲ ለማድረግ ተግተው እንደሚሠሩ በመግለጻቸው ከተሰብሳቢ መምህራን አድናቆት ከመቸራቸውም በላይ በጋራ ራዕያቸውን ለማሳካት ተግተው አብረዋቸው እንደሚሠሩ መምህራኑ ቃል ገብተውላቸዋል።

    ፕሬዝዳንቱ እያደረጉት ያለውን የምክክር መድረክ ቀጥለው ግንቦት 6 ቀን 2011 ዓ.ም. በዩንቨርሲቲው ዱራሜ ካምፓስ፣ ግንቦት 7 ቀን በዋናው ካምፓስ ምህንድስና (Engineering)፣ ጤና እና የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ (Natural and Computational Sciences) ኮሌጆች፣ በመጨረሻም ግንቦት 8 ቀን በዩንቨርሲቲው የንግስት እሌኒ መሐመድ መታሰቢያ ሆስፒታል እና ከዩኒቨርስቲው የአስተዳደር ሠራተኞች ጋር እእንደሚቀጥል ታውቋል።

    ዶ/ር ሐብታሙ አበበ በሐምሌ ወር 2011 ዓ.ም. አንድራ ፕራዴሽ (Andhra Pradesh) ግዛት (ደቡም ምስራቃዊ ህንድ) ውስጥ ከሚገኘው አንድራ ዩኒቨርሲቲ (Andhra University) የዶክትሬት ዲግሪያቸውን አግኝተዋል።

    ምንጭ፦ ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ሐብታሙ አበበ


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– በአማራ ክልል የተለያዩ ወረዳዎች የአተት ወረርሽኝ (acute watery diarrhea /AWD/) ምልክት መታየቱን የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ የአተት ወረርሽኙን አስመልከቶ በሰጠው መግለጫ፥ በአማራ ክልል በሰሜን ጎንደር እና ዋግህምራ ዞኖች በተለያዩ ወረዳዎች እየተደረጉ ባሉ የቅኝት ሥራዎች የአተት ወረርሽኝ መከሰቱ የታወቀ ሲሆን የወረርሽኙን መንስዔ ለማረጋገጥ የላብራቶሪ ምርመራ እየተካናወነ መሆኑን አስታውቋል።

    ከዚህ ጋር ተያይዞ የአንድ ታማሚ ናሙና ቫይብርዮ ኮሌራባክቴሪያ (Vibrio cholera bacteria) የተገኘበት ሲሆን ወረርሽኙን ለማረጋገጥ በተጨማሪ ናሙናዎች ላይ የላብራቶሪ ምርመራ እንደሚከናወንም ኢንስቲትዩቱ አስታውቋል።

    ከሚያዝያ 27 ቀን ጀምሮ በአማራ ክልል በዋግህምራ ዞን በአበርጌሌ ወረዳ 58 ሰዎች በበሽታው የተጠረጠሩ ሲሆን በሰሜን ጎንደር ዞን በጠለምት ወረዳ 90 ሰዎች፣ በበየዳ ወረዳ ደግሞ 4 ሰዎች በበሽታው ተጠርጥረዋል።

    እንደ ኢንስቲትዩቱ መግለጫ፥ በአጠቃላይ በክልሉ በበሽታው 151 ሰዎች የተጠረጠሩ ሲሆን ሁሉም በበሽታው የተጠረጠሩ ህሙማን በአቅራቢያው ለዚህ አገልግሎት ብቻ ተብሎ በተቋቋሙ ጊዚያዊ የሕክምና ማዕከላት በቂ ሕክምና እንዲያገኙ የተደረገ ሲሆን፤ በጠለምት ወረዳ ግን 3 ታካሚዎች በሕክምና ላይ እያሉ ህይወታቸው አልፏል።

    በፌደራል፣ በክልልና በዞን ደረጃ ፈጣን ምላሽ ሰጪ የሕክምና ቡድን ወደ አበርጌሌ፣ ጠለምትና በየዳ ወረዳዎች ተልኮ ምላሽ በመስጠት ላይ እንደሚገኝና የዓለም ጤና ድርጅትና ድንበር የለሽ የሃኪሞች ቡድንም በቦታው በመገኘት ድጋፍ እየሰጡ መሆኑም ተገልጿል።

    ከላይ ወደተጠቀሱት ወረዳዎች አስፈላጊ የሕክምና መስጫ መሣሪያዎች፣ መድኃኒቶችና መመርመሪያዎች እንዲቀርቡ መደረጉም ነው የተጠቆመው።

    በአጎራባች ወረዳዎች ወረርሽኙ ቢከሰት በቂ ሕክምና ለመስጠት የሚያስችሉ መድኃኒቶችና የሕክምና ግብአቶች በፍጥነት ማቅረብ እንዲቻል በጎንደር፣ በደሴና በሽሬ በሚገኙ የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅርቦት ኤጀንሲ መጋዘኖች እንዲከማቹ መደረጉንም ኢንስቲትዩቱ አስታውቋል።

    ከዚህ ጋር ተያይዞ ሕብረተሰቡ፡ ወረርሽኙን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የመፀዳጃ ቤት በመሥራት እና በአግባቡ በመጠቀም፣ የመመገቢያ፣ የመጠጫ እና የውሃ ማስቀመጫ እቃዎችን በንጹህ ውሃ በማጠብ እና ከድኖ በማስቀመጥ ከዝንቦችና ከበካይ ነገሮች በመጠበቅ፣ ለማንኛውም አገልግሎት የሚውልን ከጉድጓድ፣ ከምንጭ፣ ከወንዝ እና ከመሳሰሉት የተቀዳ ውሃን በማከም ወይም በማፍላት በመጠቀም፣ ምግብ ከማዘጋጀት፣ ከማቅረብ፣ ከመመገብ በፊት፣ ከመፀዳጃ ቤት መልስ እና ሕፃናትን ካፀዳዱ በኋላ እጅን በመታጠብ፣ ምግብን በሚገባ አብስሎ በመመገብ፣ ከድኖ እና በንጹህ ቦታ በማስቀመጥ ከዝንቦችና ከሌሎች ነፍሳት ንክኪ በመጠበቅ ራሱንና ቤተሰቡን ከተላላፊ በሽታዎች በመከላከል የበኩሉን ሚና እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።

    የአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት (አተት) ወረርሽኝ በተበከለ ውሃ ወይም ምግብ አማካይነት የሚከሰት ሲሆን ይህንንም ከሚያመጡ ተህዋሲያን መካከል ኮሌራን የሚያስከትለው ቪቢሮ ኮሌሬ የተሰኘው ባክቴሪያ ይገኝበታል።

    በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ የኮሌራ ወረርሽኝ በህንድ፣ በየመን፣ በኔፓል ፣ በካናዳ ቫንኮቨር ደሴት እንዲሁም በአህጉራችን አፍሪካ በዘጠኝ ሀገራት ማለትም በካሜሩን፣ በኬኒያ፣ በሶማሊያ፣ በሞዛምቢክ፣ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮነጎ፣ በታንዛኒያ፣ በሊቢያ፣ በዙምባብዌ እና በዛምቢያ የተከሰተ ሲሆን ሀገራቱ ችግሩን ለመቅርፍ እየሰሩ ናቸው።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የአተት ወረርሽኝ A WHO/UNICEF Risk Communication team member explains AWD prevention and control to health workers (PHOTO: WHO Africa)


    Semonegna
    Keymaster

    በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ በተካሄደው የሰላም ንቅናቄ ላይ ከተለያዩ ቦታዎች የመጡ እና በተለያዩ ሙያዎች ላይ የተሰማሩ የአገራችን ታዋቂ ሰዎች ስለ ሰላም እና በሰላም እጦት ምክንያት የሚከሰቱ አስከፊ ጉዳቶች ለታዳሚው አቅርበዋል።

    ወልቂጤ (ሰሞነኛ)– “ጥበብ ለሰላም” በሚል መሪ ቃል በጉራጌ ዞን ከሚገኙ 17 ወረዳዎችና ከ4 ከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ ወጣቶች፣ ሴቶች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ የአገራችን ታዋቂ የኪነ ጥበብ ሰዎች፣ አመራሮች፣ የሲቪል ሰርቪስ (civil service) ሠራተኞች እና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት በወልቂጤ ከተማ ትልቅ ስብሰባ/ውይይት በድምቀት ተካሂዷል።

    በዚህም ዞን አቀፍ የሰላም ንቅናቄ የአገራችን ታዋቂ ሰዎች (በጥቂቱ ለመጥቀስ ያህል ደራሲና መምህር ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ፣ ደራሲ እንዳላጌታ ከበደ፣ ደራሲ ህይወት ተፈራ፣ የኢትዮጵያ ቱሪዝም ድርጅት ዳይሬክተር ጀነራልና የሙዚቃ ሀያሲው አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት እና ደራሲ ተስፋዬ ጎይቴ ስለ ሰላም እና በሰላም እጦት ምክንያት የሚከሰቱ አስከፊ ጉዳቶች ለታዳሚው አቅርበዋል። የሁሉም የመቋጫ ሀሳብ የአገራችን ህዝቦች አጥር ሳይገድባቸው በብሔር፣ በዘር፣ በጎሳ፣ በሀይማኖትና በመሳሰሉ ከፋፋይ ጉዳዮችን ትተው በአንድነትና በሰብዓዊነት ስሜት ተዋደውና ተቻችለው እንደቀድሞው አብረው ሊኖሩ እንደሚገባ ነው።

    በዚህ ታላቅ የሰላም ንቅናቄ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ ጀማልና የባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ወ/ሮ መሠረት አመርጋ ሰላም ለሁሉም ጉዳዮች መሠረት መሆኑ እና ሰላም በሌለበት ምንም ሊኖር እንዳማይችል ገልፀው የዞኑ ህዝብ በሙሉ ለሰላም ዘብ መቆም እንዳለባቸው አሳስበዋል።

    “ጥበብ ለሰላም” በሚል በተካሄድው በዚህ መርሀግብር ታዋቂ የአገራችን ደራሲያን፣ የጉራጌ ዞን የባህል ኪነት ቡድን፣ ከወልቂጤና ከቡታጅራ ከተማ አስተዳደሮች የኪነ ጥበብ ክበባት የተውጣጡ አማተር ኪያንያን ድንቅ የሙዚቃ፣ ድራማና የሥነ ግጥም ሥራዎቻቸውን አቅርበዋል። እንዲሁም በሱዑዱ አብደላ የተሳሉ ድንቅ የሥነ ስዕል ሥራዎቹን አቅርቧል። የ11ኛ ክፍል ተማሪ ይዘዲን የፈጠራ ሥራዎች በመድረኩ ከቀረቡ ሥራዎች ይገኝበታል።

    በመጨረሻም ለፕሮግራሙ መሳካት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት የዞኑ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ያዘጋጃቸው ባህላዊ ስጦታዎች፣ የማበረታቻ ሽልማትና የምስጋና የምስክር ወረቀት አበርክቷል።

    ምንጭ፦ የጉራጌ ዞን አስተዳደር የሕዝብ ግንኙነት ቢሮ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    ጥበብ ለሰላም መድረክ በጉራጌ ዞን


    Anonymous
    Inactive

    አሁን የተወሰደውን እርምጃ በማፋጠን ጣቢያውን በሙሉ አቅሙ ወደ ሥራ ለማስገባት የሚያስችል የመለዋወጫ አቅርቦት ስምምነትም ጣቢያውን ከገነባው ኩባንያ ጋር በመፈራረም ወደ ሥራ መገባቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር አብርሃም በላይ ተናግረዋል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– በተከዜ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ከነበሩት አራት ተርባይኖች ሦስቱ ወደ ሥራ እንዲገቡ መደረጉን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር አብርሃም በላይ አስታወቁ።

    በተከዜ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የሥራ ጉብኝት ያደረጉት ዶ/ር አብርሃም፥ ለጣቢያው በተሰጠው ትኩረትና በተወሰደው የማስተካከያ እርምጃ ቀደም ሲል በአንድ ተርባይን ብቻ ኃይል ያመነጭ የነበረው ጣቢያው በአሁኑ ሰዓት ሦስት ተርባይኖቹ ወደ ሥራ እንዲገቡ መደረጉን ገልፀዋል።

    አሁን የተወሰደውን እርምጃ በማፋጠን ጣቢያውን በሙሉ አቅሙ ወደ ሥራ ለማስገባት የሚያስችል የመለዋወጫ አቅርቦት ስምምነትም ጣቢያውን ከገነባው ኩባንያ ጋር በመፈራረም ወደ ሥራ መገባቱን ተናግረዋል።

    እንደ ዶ/ር አብርሃም በላይ ገለፃ፥ በኃይል ማመንጫው የተከሰቱ ችግሮች በወቅቱ ተለይተው መፍትሄ እንዲያገኙ ባለመደረጉ ተቋሙ ተጨማሪ ወጪ ለማውጣት ተገዷል። በመሆኑም ተመሳሳይ ችግር በሌሎች የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች እንዳያጋጥም ትምህርት ሊወሰድበት እንደሚገባም አንስተዋል።

    ዶ/ር አብርሃም ከጣቢያው ሠራተኞች ጋር የተወያዩ ሲሆን በተቋሙ እየተካሄዱ ያሉ የለውጥ ሥራዎች ያሉበትን ደረጃ በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

    ተቋሙ የተሻለ አቅም እንዲኖረው እና በአገልግሎት ጥራቱ ተወዳዳሪ እንዲሆን ለማድረግ የሚያስችሉ የሰው ሃብት ልማት ሥራዎች እየተሠሩ በመሆኑ የተቋሙ ሠራተኞች የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

    ተቋሙ ዋናው የኦፕሬሽን ተልዕኮውን ለማሳካት የሚያስችሉ የተልእኮ ግልፅነት የመፍጠር፣ የኮርፖሬት ቢዝነስ አስተሳሰብ የመገንባት፣ አገልግሎት የሚሰጡ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን በሙሉ አቅማቸው ወደ ሥራ የማስገባት፣ የግሪድ ሞደርናይዜሽን፣ የሀብት አስተዳደርና የፋይናንስ ስርዓቱን የማዘመን የለውጥ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውም በውይይቱ ተብራርቷል።

    በ2002 ዓ.ም. ተመርቆ አገልግሎት መስጠት የጀመረው የተከዜ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የደጋን ቅርፅ ያለው ሲሆን በግንባታው ዘርፍ በአፍሪካ ጉልህ የኢንጂነሪንግና ዲዛይን ፋይዳ ካላቸው አስር የውሃ ኃይል ማመንጫዎች ውስጥ አንዱ ያደርገዋል።

    185 ሜትር ከፍታና 710 ሜትር ርዝመት ያለው የተከዜ ግድብ 300 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው ሲሆን በዓመት በአማካይ 1431 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ያመነጫል።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶር አብርሃም በላይ


    Semonegna
    Keymaster

    ባለፉት ስድስት የሽልማት መርሀግብሮች አገራችን የምትኮራባቸውን የላቀ አርአያነት ያለው ተግባር ላከናወኑ ሰዎች እውቅና የተሰጠው ከሕዝብ በቀረበ ጥቆማ መሠረት ሲሆን፥ የዘንድሮው የበጎ ሰው ሽልማት ፕሮግራም ለአገራቸው እድገት አርአያነት ያለው አስተዋፅኦ ያበረከቱ ዲያስፖራዎች ዕውቅና የሚያገኙበት መሆኑ ልዩ ያደርገዋል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)–ሰባተኛው የበጎ ሰው ሽልማት ፕሮግራም የዕጩዎች ጥቆማ ግንቦት 2 ቀን 2011 ዓ.ም. እንደጀመረ እና እስከ ሰኔ 3 ቀን 2011 ዓ.ም. ድረስ እንደሚከናወን የሽልማት አስተባባሪ ኮሚቴው አስታወቀ።

    ኮሚቴው በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ለአገርና ለሕዝብ አርአያነት ያለው ታላቅ ተግባርን ያከናወኑ ሰዎችን ዕውቅና የሚሰጠው የበጎ ሰው ሽልማት ሰባተኛው መርሃ ግብር ነሀሴ 26 ቀን 2011 ዓ.ም. በኢንተርኮንቲኔንታል ሆቴል ይካሄዳል።

    ሽልማቱም በመምህርነት፣ በሳይንስ፣ በኪነ-ጥበብ፣ በበጎ አድራጎት ሥራ፣ በቢዝነስ ሥራ ፈጠራ፣ በመንግስት የሥራ ተቋማት ኃላፊነት፣ በቅርስና ባህል፣ በማኅበራዊ ጥናት፣ በሚዲያና ጋዜጠኝነት ዘርፎች እና ለኢትዮጵያ እድገት አስተዋፅኦ ያበረከቱ ዲያስፖራዎችን የሚያካትት እንደሆነ ኮሚቴው ገልጿል።

    ለእያንዳንዱ የሽልማት ዘርፍ ሦስት ዳኞች ተመርጠው ምርጫው የሚከናወን ሲሆን ዳኞቹም የረጅም ጊዜ ልምድ ያላቸውና በታማኝነት ምርጫውን ያከናውናሉ ተብለው የታመነባው እንደሆኑ በመግለጫው ወቅት ተጠቅሷል።

    ኮሚቴው እንደገለፀው፥ ባለፉት ስድስት የሽልማት መርሀግብሮች አገራችን የምትኮራባቸውን የላቀ አርአያነት ያለው ተግባር ላከናወኑ ሰዎች እውቅና የተሰጠው ከሕዝብ በቀረበ ጥቆማ መሠረት መሆኑን ገልፆ፥ መርሀግብሩን ለዚህ ያበቃው በሂደቱ የሕዝብ ተሳትፎ በመኖሩ ስለሆነ ይህም አሁንም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ ቀርቧል።

    የበጎ ሰው ሽልማት ዋና ዓላማ ለአገራችን መልካም የሠሩ፣ አገራዊ ተልዕኳውን በብቃት የተወጡ፣ የሕዝብን ኑሮ ለማሻሻል ለውጥ አምጪ ተግባራትን ያከናወኑ፣ የአገሪቱን ታሪክ፣ ቅርስ፣ ባህል እንዲጠበቅና የሀገራቸው ስልጣኔ ከፍ እንዲል የሠሩ ኢትዮጵያዊያንን በማበረታታት ዕውቅና በመስጠት ሌሎች በጎ ሥራዎችን ለሀገራቸው ማበርከት እንዲችሉ ማስቻል ነው።

    ይህንን የበጎ ሰው ሽልማት ዓላማ ከግምት ውስጥ በማስገባት ህብተረሰቡ ጥቆማውን ከግንቦት 2 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ በስልክ፣ በቫይበር (Viber)፣ በቴሌግራም (Telegram)፣ በኋትሳፕ (WhatsApp)፣ በኢሜይል (e-mail)፣ በፖስታና በአካል በመቅረብ መጠቆም እንደሚቻል ኮሚቴው ያሳወቀ ሲሆን፥ ለዚህም አገልግሎት በስልክ ቁጥር 0940140813begosewprize@gmail.com እና ፖስታ ሳጥን ቁጥር 150035 አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ መጠቀም ይቻላል ተብሏል።

    የዘንድሮው የሽልማት ፕሮግራም ለአገራቸው እድገት አርአያነት ያለው አስተዋፅኦ ያበረከቱ ዲያስፖራዎች ዕውቅና የሚያገኙበት መሆኑ ልዩ ያደርገዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የበጎ ሰው ሽልማት


    Anonymous
    Inactive

    ብርሃኑ ነጋ የመረጠውን ሕይወት ለመምረጥ የጨዋ ልጅ መሆን ይጠይቃል፣ የህሊና ሰው መሆን ይጠይቃል፣ ራስን ማክበር ይጠይቃል። የብርሃኑ ነጋን ፅናትና የአቋም ሰውነቱን መካድ ነውር ነው! እሱን በፍርሃትና በአቋም የለሽነት ማማት ብልግና ነው። እሱን በዘርና በጎሳ ጉሊት መመደብ ውለታ ቢስነት ነው!

    የነጋ ቦንገር ልጅ!
    («ዘውድዓለም ታደሠ»)

    የልደቱ አያሌው ድብን ያልኩ አድናቂ ስለሆንኩና ብርሃኑ በልደቱ ጉዳይ የወሰደው አቋም አግባብነት ያለው (fair) ነው ብዬ ስለማላምን ትንሽ አዝኜበታለሁ። ሆኖም ግን እውነት እውነት ነችና ስለብሬ [ብርሃኑ ነጋ] የማልክዳቸው ሃቆች አሉ! (ስለእሱ የሰማኋቸውን “ሴራዎችን” (conspiracies) እዚህ ጋር አላነሳቸውም።)

    ብርሃኑ ነጋ እንደብዙዎቹ ፖለቲከኞቻችን ‘ፖለቲካ ክፍት የሥራ ቦታ ነው’ ብሎ ወደተመታው የኢትዮጵያ ፖለቲካ አልተቀላቀለም። በደርግ ዘመን ብዙዎች በወላጆቻቸው ሽካ ከብሔራዊ ውትድርና አምልጠው ማታ ማታ ገዳም ሰፈር ከቆነጃጅት ጋር ቡጊ ቡጊ ሲጨፍሩ ብሬ በዚያ እድሜው የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ሆኖ በአገሩ ጉዳይ ከሞት ጋር ሌባና ፖሊስ ይጫወት ነበር። (የሚወዳት እህቱንም አጥቷል።)

    በኢህአዴግም ግዜ ከመለስ፣ ከታምራትና ከበረከት ጋር ባለው ልዩ ወዳጅነት (special friendship) ተሞዳሙዶ ቢያሻው ስልጣን፣ ቢያሻው መሬት ሸምቶ፣ ቢያሻው ሚኒስትር፣ ቢያሻው ቀጭን ኢንቨስተር ሆኖ ዘንጦ መኖር ሲችል ላመነበት ነገር ጎምበስ ቀና ሳይል የተቃዋሚውን ጎራ ተቀላቅሏል።

    ምንም እንኳ በየትኛውም ዓለም ቢሄድ እጁን ስመው የሚቀበሉት ምርጥ ምሁር ቢሆንም ከምቾቱ ይልቅ ወደወህኒ ወርዶ ሞት ተፈርዶበታል። እስር ቤት ውስጥ የረሃብ አድማ አድርጓል። በስተርጅና ዘመኑም እንዳቅሚቲ የትጥቅ ትግል ለማድረግ ተሟሙቷል። በተደጋጋሚ በርሃ ወርዷል። የፖለቲካ አኪያሄዱን ወደድነውም ጠላነውም በሚችለው አቅም ለአገሩ ህዝብ ድምፅ ሆኗል! ይሄ የማይካድ ሃቅ ነው!

    ከግማሽ ምእተ-ዓመት በላይ የሃብት ማማ ላይ ከተቀመጠ ቤተሰብ ተወልዶ፣ ዩኒቨርሲቲ ደሞዙን ለምስኪን ተማሪዎች እየሰጠ አስተምሮ፣ እድሜውን ሙሉ ባለሰባት ኮከብ (seven-star) ሆቴል እንደፓፍ ዳዲ አምስት ቺኮች አቅፎ መዝናናት እየቻለ ያሻው አገር ሄዶ በዕውቀቱ ተከብሮ መሥራት እየቻለ፣ በአፍሪካ ገናና የሆነ የጦር ኃይል አለኝ የሚልን ኃይል በጦርነት አሸንፋለሁ ብሎ በወኔ የተነሳ፣ ቤተሰቡን ጥሎ በእስር የማቀቀ፣ አገሩ ላይከፍተኛ ዕውቅና እንዳለው ግለሰብ (VIP standard) መኖር ሲችል በአሸባሪነት ተፈርጆ ብላክ ሊስት (black list) ውስጥ የገባ አንድ ሰው ባፈላልግ ያገኘሁት ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋን ብቻ ነው!

    አሁን ደግሞ ብሬ በተጋዳላይ ታርጋ የሚንቀሳቀስ ፓርቲውን አክስሞ አዲስ ፓርቲ በማቋቋም ከመጀመሪያው “ሀ” ብሎ (from the scratch) ሊነሳ ነው። ይህን ሁሉ የሚያደርገው ለምንድን ነው? ለሀብት እንዳንል እንኳን እሱ ዘር ማንዘሩም ሃብታም ነው። ለስልጣን እንዳንል ገና ድሮ በቀላሉ ማግኘት ይችል ነበር! እና ለምንድነው ህይወቱን እንዲህ በከባድ ወጥ ውረዶች የተሞላ (tragedy) ያረገው?… መልሱ ቀላል ነው። ብሬ (ብርሃኑ ነጋ) የአቋም ሰው ነው! ብሬ ላመነበት ነገር ከገገመ ገገመ ነው! አዲዮስ!

    እኔ ከላይ እንደነገርኳችሁ ‘ለብሬ እሰዋለታለሁ፣ ብርሃኑ ነጋ ያማልዳል፣…’ ምናምን የምል አድናቂው አይደለሁም። ነገር ግን አክባሪው ነኝ። ፅናትና የአቋም ሰውነቱን መካድ ነውር ነው! እሱን በፍርሃትና በአቋም የለሽነት ማማት ብልግና ነው። እሱን በዘርና በጎሳ ጉሊት መመደብ ውለታ ቢስነት ነው!

    […] የባቄላ ፍሬ የምታህል ዛኒጋባ ቤት ሳትኖርህ ቫንዳም፣ ቫንዳም መጫወት፣ የምታጣው ነገር ሳይኖር ኃላፊነት (risk) መውሰድና ከባዱን የሕይወት መንገድ መምረጥ’ኮ ያለና የነበረ ነው። ነገር ግን ሁሉ ሞልቶልህ ብርሃኑ ነጋ የመረጠውን ሕይወት ለመምረጥ የጨዋ ልጅ መሆን ይጠይቃል፣ የህሊና ሰው መሆን ይጠይቃል፣ ራስን ማክበር ይጠይቃል! ይኸው ነው!

    ረጅም ዕድሜ ለነጋ ቦንገር ልጅ!

    [ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና አቶ አንዱአለም አራጌ የኢትዮጵያ ዜጎች ማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ መሪና ምክትል መሪ በመሆን ተመረጡ። ግንቦት 2 ቀን 2011 ዓ.ም. በተካሄደው ምርጫ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ 912 ድምፅ በማግኘት የፓርቲው መሪ በመሆን ተመርጠዋል። በተመሳሳይ አቶ አንዱአለም አራጌ የፓርቲው ምክትል መሪ በመሆን ተመርጠዋል። እንደዚሁም አቶ የሺዋስ አሰፋ 722 ድምፅ በማግኘት ሊቀመንበር ሆነው ሲመረጡ፥ ዶ/ር ጫኔ ከበደ ምክትል ሊቀመንበር በመሆን ተመርጠዋል። — ሰሞነኛ ኢትዮጵያ]

    ብርሃኑ ነጋ የኢትዮጵያ ዜጎች ማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ


     

    Semonegna
    Keymaster

    ተከሳሽ ዓለም ታምራት ከተለያዩ ዓለም ሀገራት ወደ ኢትዮጵያ የሚደረጉ ጥሪዎችን በማስተላለፍ ኢትዮ ቴሌኮም የዘረጋውን መሠረተ ልማት ወደ ጎን በመተው ዓለም አቀፍ የቴሌኮም አገልግሎት በመስጠት ጥፋተኛ ተብላለች።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– ዓለም ታምራት የተባለችው ተከሳሽ የቴሌኮም መሣሪያዎችን ወደ ሀገር ውስጥ በማስገባት፣ ለመጠቀም እና የቴሌኮም አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ሕጋዊ ፍቃድ ሳይኖራት ወደ ሕገወጥ ተግባሩ መግባቷ ተጠቁሟል። ወንጀሉ በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 ልዩ ስሙ ገርጅ አካባቢ መፈጸሙ ታውቋል።

    የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀል የወጣውን አዋጅ ቁጥር 761/2004 አንቀጽ1/ለ ስር የተመለከተውን በመተላለፍ ተከሳሽ ከቀድሞው ኢፌዲሪ መገናኛ እና ኢንስፎርሜሽን ሚኒስቴር በተሰጠ ፍቃድ ብቻ ወደ ሀገር ውስጥ ለመጠቀም የሚቻሉትን የኮል ተርሚኔሽን (call termination)፣ ኮል ባክ (call back)፣ ጥሪ የመቀበል እና ጥሪ የመላክ አገልግሎት መስጠት እንደነበር ተነግሯል።

    ሆኖም ግለሰቧ ከሕግ አግባብ ውጪ ኢትዮ ቴሌኮም ሲም ካርዶችን በውስጣቸው በማስገባት በአንድ ጊዜ ብዛት ያላቸውን እቃዎች በቅናሽ በመግዛት እና ጥሪዎችን ማስተላለፍ የሚችሉ ብዛታቸው 4 የሆኑ ጌትዌይ (gateway) የቴሌኮም መሣሪያዎችን በድብቅ በማስገባት ወንጀል ፈጽመዋል።

    በድብቅ የገቡ መሣሪያዎችን ከበይነመረብ (internet) የግንኙነት አውታር ጋር በማገናኘት የሚያገኙትን ኔትወርክ (network) በማብዛት ወደ ዋየርለስ ኔትወርክ (wireless network) እንዲቀየር በማድረግ የራሳቸውን ኔትወርክ መፍጠር የሚችሉ 15 ቶፒ ሊንክ የተባሉ መሣሪያዎችን ከሌሎች አጋዥ መሣሪያዎች ጋር መጠቀማቸው በክሱ ቀርቧል።

    ግለሰቧ ከውጭ ሀገር ወደ ሀገር ውስጥ የሚደረጉ የስልክ ጥሪዎችን ኢትዮ ቴሌኮም በዘረጋው ኔትወርክ በኩል እንዲያልፉ በማድረግ ኢትዮ ቴሌኮምን 6,379,342.19 ብር ማሳጣቷ ተጠቅሷል።

    ተከሳሽ ዓለም ታምራት ከተለያዩ ዓለም ሀገራት ወደ ኢትዮጵያ የሚደረጉ ጥሪዎችን በማስተላለፍ ኢትዮ ቴሌኮም የዘረጋውን መሠረተ ልማት ወደ ጎን በመተው ዓለም አቀፍ የቴሌኮም አገልግሎት በመስጠት ጥፋተኛ ተብላለች።

    ጉዳዩን ተመለከተው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 14 ወንጀል ችሎትም አቃቤ ሕግ ያቀረበውን የሰው እና የሰነድ ማስረጃዎችን በመመልከት በሚያዝያ 14 ቀን 2011 ዓ.ም. በዋለው ችሎት በ12 ዓመት ጽኑ እስራት እና በ63 ሚሊዮን የገንዘብ መቀጮ አሳልፎባታል።

    ምንጭ፡- የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ / የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ሌሎች ዜናዎች፦

    ኢትዮ ቴሎኮም


Viewing 15 results - 466 through 480 (of 730 total)