Search Results for 'ኢትዮጵያ'

Home Forums Search Search Results for 'ኢትዮጵያ'

Viewing 15 results - 526 through 540 (of 730 total)
  • Author
    Search Results
  • Anonymous
    Inactive

    የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 737-8 ማክስ የተሰኙት አውሮፕላኖቹ ከበረራ አገልግሎት እንዲወጡ መወሰኑን አስታወቀ
    —–

    የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 737-8 ማክስ የተሰኙት አውሮፕላኖቹን በሙሉ ላልተወሰነ ጊዜ ከበረራ አገልግሎት እንዲወጡ መወሰኑን አስታወቀ።

    የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዛሬው እለት ባወጣው መግለጫው ነው አውሮፕላኖቹን ላልተወሰነ ጊዜ ከበረራ ማስወጣቱን ያስታወቀው።

    አየር መንገዱ ከዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰውም በትናንትናው እለት ቦይንግ 737-8 ማክስ በበረራ ቁጥር ኢቲ 302 የደረሰበትን የመከስከስ አደጋ ተከትሎ መሆኑንም አስታውቋል።

    በዚህም መሰረት የአደጋው መንስኤ ተጣርቶ እስኪታወቅ ድረስ ለመንገደኞች ደህንነትና ጥንቃቄ ሲባል ቦይንግ 737-8 ማክስ የተሰኙት አውሮፕላኖቹን በሙሉ ከዛሬ ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ ከበረራ አገልግሎት እንዲወጡ መወሰኑን ገልጿል።

    አየር መንገዱ ቦይንግ 737-8 ማክስ የተሰኙት አምስት አውሮፕላኖች ያሉት ሲሆን፥ በትናንትናው እለት የተከሰከሰውም ከአራት ወራት በፊት የተረከበው 4ኛው አውሮፕላኑ ነበር።

    በተመሳሳይ ዜና ቻይናም በሀገሯ የሚገኙ ቦይንግ 737-8 ማክስ የተሰኙት አውሮፕላኖቿ በሙሉ ላልተወሰነ ጊዜ ከበረራ አገልግሎት እንዲወጡ መወሰኗም ተነግሯል።

    የቻይና የአቪዬሽን ተቆጣጣሪ ባለስልጣን የቻይናን አየር መንገዶች ቦይንግ 737-8 ማክስ የተሰኙት አውሮፕላኖችን ለበረራ መጠቀም እንዲያቆሙ አስታውቋል።

    ቦይንግ 737-8 ማክስ የተሰኘው አውሮፕላን ባለፉት አምስት ወራት የመከስከስ አደጋ ሲያጋጥመው የትናንቱ ለሁለተኛ ጊዜ ነው።

    ከአምስት ወራት በፊት ላዮን ኤየር የተሰኘ የኢንዶኔዢያ አየር መንገድ ንብረት የሆነ ተመሳሳይ ሞዴል አውሮፕላን ለበረራ በተነሳ በደቂቃዎች ውስጥ ተከስክሶ 189 ሰዎች ህይወት ማለፉ ይታወሳል።

    ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ

    Anonymous
    Inactive

    ምክር ቤቱ ያወጀው ብሄራዊ የሀዘን ቀን ተጀምሯል
    —–

    የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ብሄራዊ የሃዘን ቀን እንዲሆን ማወጁን ተከትሎ ብሄራዊ የሀዘን ቀኑ ተጀምሯል።

    ምክር ቤቱ ብሄራዊ የሀዘን ቀኑን ያወጀው ዛሬ ንብረትነቱ ኢትዮጵያ አየር መንገድ የሆነ ቦይንግ 737 አውሮፕላን ተከስክሶ የ157 ሰዎች ህይወት ማለፉን ተክትሎ ነው።

    የምክር ቤቱ ፅህፈት ቤት ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በላከው መግለጫ በአደጋው ህይወታቸውን ላጡ ኢትዮጵያውያን እና የውጭ ሐገር ዜጎች ዛሬ የአንድ ቀን ብሄራዊ የሐዘን ቀን እንዲታወጅ በሰንደቅ አላማ አዋጅ ቁጥር 654/2001/ በአዋጅ ቁጥር 863/2006 እንደተሻሻለ አንቀጽ 22 ንዑስ አንቀጽ (2) መሰረት መወሰኑን አስታውቋል።

    ስለሆነም የሪፐብሊኩ ሰንደቅ አላማ በዛሬው እለት በመላው የአገሪቱ ግዛቶች፣ በኢትዮጵያ መርከቦች እና በውጭ ሐገር በሚገኙ ኤምባሲዋች የቆንስላ ጽህፈት ቤቶች ዝቅ ብሎ የሚውለበለብ ይሆናል።

    ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ

    Semonegna
    Keymaster

    በአደጋው የሁሉም ህይወት (157 ሰዎች) ያለፈ ሲሆን፥ ከተሳፋሪዎቹ መካከል 32ቱ ኬኒያዊያን ሲሆኑ፤ 17ቱ ኢትዮጵያዊያን ቀሪዎቹ ደግሞ የሌሎች አገራት ዜጎች መሆናቸውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታውቋል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– በዛሬው ዕለት የተከሰከሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ተሳፋሪዎች በሙሉ ህይወታቸው ማለፉ ተገለጸ።

    ከአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ (ኬንያ) ሲጓዝ በምሥራቅ ሸዋ ዞን ጊምቢቹ ወረዳ ላይ የተከሰከሰው የበረራ ቁጥር ET302 የሆነው ቦይንግ 737 የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን የ33 አገራት 149 መንገደኞችና ስምንት የበረራ አስተናጋጆችን ይዞ ነበር።

    ከተሳፋሪዎቹ መካከል 32ቱ ኬኒያዊያን ሲሆኑ፤ 17ቱ ኢትዮጵያዊያን ቀሪዎቹ ደግሞ የሌሎች አገራት ዜጎች መሆናቸውን አየር መንገዱ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት አስታውቋል።

    አውሮፕላኑ አደጋው የደረሰበት ዛሬ ማለዳ ከቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት በተነሳ በስድስት ደቂቃ ልዩነት መሆኑ የተገለጸ ሲሆን የአደጋው መንስዔ እስካሁን አልታወቀም።

    በአደጋው የሁሉም ህይወት (157 ሰዎች) ያለፈ ሲሆን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት በአደጋው የተሰማውን ሀዘን በመግለጽ ለሟች ቤተሰቦችና ወዳጅ ዘመዶች መጽናናትን ተመኝቷል።

    የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 737 በረራ ዛሬ ጠዋት ከአዲስ አበባ ተነሥቶ ወደ ኬንያ ናይሮቢ ይበር በነበረው አውሮፕላን በደረሰው የመከስከስ አደጋ ወዳጅ ዘመዶቻቸውን ላጡ ሁሉ የጠ/ሚር ጽ/ቤት በኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት ስም ኀዘኑን ይገልጻል።የኢትዮጵያ ተቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ያሰፈረው።

    በተመሳሳይ የኬኒያው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በአደጋው የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸው ለአደጋው ሰለባ ቤተሰቦች መፅናናትን ተመኝተዋል።

    የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በአደጋው ህይወታቸውን ላጡ ሰዎች ቤተሰቦች የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል። ፕሬዝዳንቷ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ከአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ በመጓዝ ላይ እያለ አደጋ አጋጥሞት የመከስከሱን ዜና በከፍተኛ ድንጋጤና መሪር ሀዘን እንደሰሙ ገልጸዋል።

    ፈጣሪ አምላክ በቸርነቱ ለቤተሰቦቻቸው በሙሉ፣ ከብዙ በጥቂቱ ናይሮቢ ለማውቃቸው ለካፒቴን ያሬድ ወላጆች፣ ዶ/ር ጌታቸውና ዶ/ር ራያን፣ ለሆስተስ ሣራ ባለቤትና ሕጻን ልጆቿ፣ ከጥቂት ሳምንታት በፊት ላየኋት የጂቡቲዋ ራሻ ቤተስብ… መጽናናትን ይስጥልን። ዛሬ በ157 ሟች ቤተሰቦች ላይ የወደቀው መሪር ሐዘን እኔና ቤተሰቤ ኮሞሮስ በደረሰው አደጋ ያየነው በመሆኑ የሚያሳልፉትን ከባድ ፈተና ከማንም በላይ እረዳዋለሁ። 149 መንገደኞችና 8 የበረራ ሠራተኞችን ይዞ ከአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ ሲግዋዝ የነበረው [ET 302] በረራ ላይ በደረሰው የመከስከስ አደጋ በውስጡ የነበሩት ኢትዮጵያውያንና የ33 አገሮች ዜጎች ሕይወት ማለፍ ልቤን ሰንጥቆታል፤ እጅግ በጣም ነው ያዘንኩት።ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በትዊተር ገጻቸው ላይ ያሰፈሩት።

    “ለኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊያን ትልቅ የሀዘን ቀን ነው” ያሉት ፕሬዝዳንቷ “በዜጎቻችንና ሌሎች የአየር መንገዱ ደንበኛ መንገደኞች ላይ በደረሰው አደጋ ልቤ ተሰብሯል” ብለዋል። በአደጋው ተጎጂ ለሆኑ ቤተሰቦች ፣ ወዳጅ ዘመዶችና ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብም መጽናናትን ተመኝተዋል።

    በተመሳሳይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ ሲበር በተከሰከሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 737 አውሮፕላን አደጋ ጥልቅ ሀዘን እንደተሰማው ገልጾ በአደጋው ቤተሰቦቻቸውን ላጡ መፅናናትን ተመኝቷል።

    የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባርም (ኢህአዴግ) እንዲሁ በአደጋው የተሰማውን ሀዘን በመግለጽ የሟች ወገኖች ነፍስ በአፀደ ገነት እንዲያርፍ ፣ ለወዳጅ ዘመድ ቤተሰቦቻቸውና ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብም መፅናናትን ተመኝቷል።

    የኢትዮጵያ አየር መንገድ በበኩሉ በደረሰው አደጋ የሰው ሕይወት በመጥፋቱ የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን ገልጿል። አውሮፕላኑ ምንም ዓይነት ቴክኒካዊ ችግር እንዳልነበረበትም አመልክቷል።

    የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ተወልደ ገብረማርያም በሰጡት መግለጫ፤ በአውሮፕላኑ መከስከስ የመንገደኞችና የአውሮፕላኑ ሠራተኞች ሕይወት በማለፉ ከፍተኛ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልጸዋል። ህይወታቸው ያለፉት ቤተሰቦችና ወገኖች ማስተናገጃ በአዲስ አበባ እና በናይሮቢ ቢሮ መከፈቱን ተናግረዋል።

    በአጠቃላይ 1ሺ 200 ሰዓታትን የበረራ ሰዓት ያስመዘገበው አውሮፕላን ከአዲስ አበባ ለበረራ የተነሳው 2 ሰዓት ከ38 ደቂቃ ሲሆን፤ 2 ሰዓት ከ40 ላይ ችግር እንዳጋጠመውና ከራዳር እይታ ውጪ እንደሆነም ገልጸዋል።

    የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከቦይንግ ኩባንያ ከተረከበው አራት ወር የሆነው ቦይንግ 737 ወደ ኬንያ የሚያደርገወን ጉዞ ከመጀመሩ በፊት ከጆሃንስበርግ ደቡብ አፍሪካ ተመልሶ ለሦስት ሰዓት ያህል አርፏል።

    ይሄው በዋና አብራሪ ካፒቴን ያሬድ ሙሉጌታ ወደ ኬንያ እየተጓዘ የነበረው አውሮፕላን፤ ቀደም ብሎ በተካሄደ የቴክኒክ ፍተሻ ምንም ዓይነት ችግር እንዳልነበረበት አመልክተዋል። ረዳት አብራሪው አህመድ ኑር መሃመድ ኑር የሚባል ሲሆን፤ ከ200 ሰዓታት በላይ መብረሩም ተገልጿል።

    የአደጋው መንሰኤ አለማቀፍ የአቬሽን ሕግን በተከተለ መልኩ ዓለምአቀፍ ምርመራ ተካሂዶ ዝርዝር መረጃው ወደፊት እንደሚገለጽ አመልክተዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የኢትዮጵያ አየር መንገድ


     

    Semonegna
    Keymaster

    የአቶ ገዱ አንዳርጋቸውን የስልጣን መልቀቅ ጥያቄ ተከትሎ የአዴፓ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል እና የጠቅላይ ሚኒስትር የመሠረተ ልማት እና የከተማ ልማት አማካሪ ሚኒስትር የሆኑት ዶ/ር አምባቸው መኮንን ርዕስ መስተዳደር ሆነው ተሹመዋል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው መልቀቂያ ጥያቄ አቀረቡ። ርዕሰ መስተዳድሩ እየተካሄደ ባለው የክልሉ ምክር ቤት ስብሰባ ላይ ነው ጥያቄውን ያቀረቡ ሲሆን፥ ምክር ቤቱም ጥያቄያቸውን ተቀብሏል። የአማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (አዴፓ)በበኩሉም የርዕሰ መስተዳድሩን ጥያቄ መቀበሉን የ አማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት እና ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ዘግበዋል።

    አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ባለፈው ዓመት የካቲት ወር ለሦስተኛ ዙር በርዕሰ መስተዳድርነት ተመርጠው ሲያገለግሉ እንደነበር ይታወሳል። በአጠቃላይም ከታህሳስ ወር 2006 ዓ.ም. ጀምሮ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር በመሆን አገልግለዋል።

    አቶ ገዱ አንዳርጋቸው “ታላቁን የአማራ ሕዝብ ለመምራት ዕድል የሰጠኝን ፓርቲዬን አመሠግናለሁ፤ በስልጣን ዘመኔ በሰጠኋቸው ውሳኔዎች ያስከፋኋችሁ ካላችሁ ከልብ ይቅርታ እጠይቃለሁ። ወኔና ጉልበት ሆኖኝ የኖረውን የአማራ ሕዝብ አመሠግናለሁ፤ ለአዲሱ ርዕሰ መስተዳድርም መልካም የሥራ ዘመን እመኛለሁ” ብለዋል በመሰናበቻ ንግግራቸው።

    የአቶ ገዱ አንዳርጋቸውን የስልጣን መልቀቅ ጥያቄ ተከትሎ ምክር ቤቱ የአዴፓ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል የሆኑትን ዶ/ር አምባቸው መኮንንን ርዕስ መስተዳደር አደርጎ ሾሟል። ዶ/ር አምባቸው ከአዴፓ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነታቸው በተጨማሪ የጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮን የመሠረተ ልማት እና የከተማ ልማት አማካሪ ሚኒስትር በመሆን እያገለገሉ ነበር።

    እድገታቸው ጋይንት፣ ጎንደር ውስጥ የሆነው ዶ/ር አምባቸው መኮንን የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ ሆነው ከመሾማቸው በፊት በተለያዩ የመንግስት ቦታዎች ለ28 ዓመታት ሠርተዋል።

    ዶ/ር አምባቸው ከኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩንቨርሲቲ በኢኮኖሚክስ፣ ቀጥሎም ደቡብ ኮርያ ከሚገኘው ከኮርያ የልማት ኢንስቲትዩት (Korea Development Institute) በፐብሊክ ፖሊሲ የማስተርስ ዲግሪ፣ ከዚያም እንግሊዝ ሀገር ካንተርበሪ ከተማ ከሚገኘው ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ኬንት (University of Kent) ሌላ ማስተርስ ዲግሪ እና የዶክትሬት ዲግሪያቸውን አግኝተዋል።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    ዶ/ር አምባቸው መኮንን


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – በዛሬው ዕለት (የካቲት 27 ቀን 2011 ዓ.ም.) በአዲስ አበባ 51 ሺህ 229 የጋራ መኖሪያ ቤቶች (ኮንዶሚኒየም ቤቶች) ዕጣ ማውጣት ሥነ ስርዓት ተካሄደ።

    ዕጣ ከወጣባቸው ቤቶች ውስጥም 32 ሺህ 653 ቤቶች የ20/80 ቤቶች ሲሆኑ፥ ቀሪዎቹ 18 ሺህ 576 ደግሞ የ40/60 ቤቶች ናቸው። በዚህም መሠረት የ20/80 ፕሮግራም ኮንዶሚኒየም ቤቶች ውስጥ 1 ሺህ 248 ስቲዲዮ፣ 18 ሺህ 823 ባለ አንድ መኝታ፣ 7 ሺህ 127 ባለ ሁለት መኝታ እና 5 ሺህ 455 ቤቶች ደግሞ ባለ ሦስት መኝታ ክፍሎች ናቸው። በእነዚህ የ20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ ውስጥ የሚካተቱት በ1997 ዓ.ም ተመዝግበው በ2005 ዓ.ም በነባር መደብ የተመዘገቡና በ2005 ዓ.ም የአዲስ ባለ ሦስት መኝታ ክፍል ተመዝጋቢዎች ናቸው።

    በዕጣ አወጣጥ ሥነ ስርዓቱ ላይ የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ እንደተናገሩት፥ በግንባታ ሂደት ሁሉም ተጠቃሚ እንደሚሆን ቢታሰብም በጥንቃቄ ጉድለት ለጉዳትና ማኅበራዊ ቀውስ የተዳረጉ የህብረተሰብ ክፍሎች አሉ። ኢንጅነር ታከለ ልማት በጋራ ተጠቃሚነት ካልተመኅረተ ተጎጅና ተጠቃሚን የሚፈጥርም ነው ብለዋል። በተለይ ለቤቶች ግንባታ ሲባል ከእርሻ ቦታቸው የለቀቁ አርሶ አደሮችና የአርሶ አደር ልጆች የሁላችንም ህመም ነው ብለዋል። በዚህም የከተማ አስተዳደሩ ካቢኔና የቤቶች አሰተዳደር ቦርድ አርሶ አደሮችና የአርሶ አደር ልጆች ያለ ዕጣ እንዲሰጣቸው መወሰኑን ይፋ አድርገዋል።

    ተሰርዞ የነበረው የ20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ ወጣ (የዕድለኞች ስም ዝርዝር) 

    ኢንጂነር ታከለ በቀጣይም የቤት ልማትን ከአርሶ አደሩ ተጠቃሚነት ጋር ለማስኬድ ትኩረት በማድረግ ይሠራል ነው ያሉት። በቤት ልማቱ የመንግስትን ተሳትፎ በመቀነስ የግሉንና የባለሀብቱን ተሳትፎ የማሳደግ ሥራ እንደሚከናወንም ጠቁመዋል። ከንቲባው በዘርፉ የመንግስትና የባላሀብቶችን ግንኙነትን ለማጠናከር በትኩረት ለመንቀሳቀስ ኮሚቴ መዋቀሩን ነው ያስታወቁት።

    የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስትር አቶ ዣንጥራር አባይ በበኩላቸው፥ መንግስት በቤት ልማት ዘርፍ የሚታየውን ችግር ለመቅረፍ በርካታ ሥራዎች ሲያከናውን መቆየቱን የተናገሩ ሲሆን፥ በዚህ ወጤቶች መመዝገባቸውን አንስተዋል። በቤት ልማት ዘርፉ የፍላጎቱን ያህል ባይሠራም የተሻለ ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።

    አቶ ዣንጥራር በኢትዮጵያ ያለው የቤት ልማት ዘርፍ ህዝቡን የቤት ባለቤት ከማድረግ ባለፈ ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል የፈጠረ መሆኑን አስታውቀዋል። ባለፉት 13 ዓመታት በአዲስ አበበና በመላ ሀገሪቱ ከ385 ሺህ በላይ ቤቶች እንደተገነቡና በግንባታ ላይ እንደሚገኙ የገለፁ ሲሆን፥ በዚህም 1 ሚሊየን ለሚጠጉ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር እንደተቻለ ተናግረዋል።

    በተለያዩ ወገኖች በተደረገ ጥናት መሠረት ካለው የቤት ፍላጎት አንፃር ከ2007 እስከ 2017 ዓመተ ምኅረት ባለው ጊዜ ውስጥ 471 ሺህ ቤቶችን በየዓመቱ እየገነቡ ማቅረብ ይገባ ነበር። ሆኖም መንግስት በፋይናንስ እና በግንባታ ፕሮጀክት የማስፈፀም አቅም ባለበት ክፍተት ምክንያት ይህን ማድረግ እንዳልተቻለ በመጠቆም በቀጣይ የግሉን ዘርፍ በማሳተፍ ፍላጎቱን ለማሟላት እንደሚሠራ ነው አቶ ዣንጥራር በንግግራቸው ላይ ያነሱት።

    ኮንዶሚኒየም ቤቶች ዕጣ የወጣላቸው ዕድለኞች ስም ዝርዝር

    13ኛ ዙር የ20/80 ፕሮግራም ባለ ስቱዲዮ ቤት የዕድለኞች ስም ዝርዝር
    13ኛ ዙር የ20/80 ፕሮግራም ባለ አንድ መኝታ ክፍል የዕድለኞች ስም ዝርዝር
    13ኛ ዙር የ20/80 ፕሮግራም ባለ ሁለት መኝታ ክፍል የዕድለኞች ስም ዝርዝር
    13ኛ ዙር የ20/80 ፕሮግራም ባለ ሦስት መኝታ ቤት የዕድለኞች ስም ዝርዝር
    የ40/60 መርሃ ግብር ባለ አንድ መኝታ ቤት የዕድለኞች ስም ዝርዝር
    የ40/60 መርሃ ግብር ባለ ሁለት መኝታ የዕድለኞች ስም ዝርዝር
    የ40/60 መርሃ ግብር የባለ ሦስት መኝታ ቤት የዕድለኞች ስም ዝርዝር

    ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ኮንዶሚኒየም ቤቶች


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ የተከፈተው ቆንስላ ጽ/ቤት ቆንሱል ጄኔራል አምባሳደር እውነቱ ብላታ ቆንስላ የጽ/ቤቱ መከፈት በሚኒሶታ ግዛት ለሚኖሩ በሺዎች ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ዳያስፖራ አባላት ምቹ ሁኔታና መነቃቃትን እንደሚፈጥር ገልጸዋል።

    ዋሽንግተን፥ ዲሲ (ሰሞነኛ) – የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ (ኢፌዴሪ) መንግስት በሀገረ አሜሪካ በሎስ አንጀለስ ከተማ (ካሊፎርንያ ግዛት) ከሚገኘው ቆንጽላ ጽ/ቤት ቀጥሎ ሁለተኛውን ቆንጽላ ጽ/ቤት በሴይንት ፓል ከተማ (ሚኖሶታ ግዛት) ከፍቷል።

    ቆንስላ ጄኔራል ጽ/ቤቱ የተከፈተው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ዓመት ነሃሴ ወር ላይ በአሜሪካ ባደረጉት ጉብኝት በገቡት ቃል መሠረት ነው።

    በመክፈቻ ሥነ-ስርዓቱ ላይ የኦሮሚያ ክልል መንግስት ፕሬዝዳንት አቶ ለማ መገርሳ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ብርቱካን አያኖ፣ የሴይንት ፓል ከተማ ከንቲባ ሚስተር ሜልቪን ካርተር፣ ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንዲሁም በርካታ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የዳያስፖራ አባላት ተገኝተዋል።

    ክቡር አቶ ለማ መገርሳ እንደገለጹት የቆንስላ ጽ/ቤቱ መከፈት ለአካባቢው ብሎም በመላው አሜሪካ የሚኖረውን ዳያስፖራ ለማገልግል የጎላ ፋይዳ ይኖረዋል። ዳያስፖራው በኢትዮጵያ እየተካሄደ ባለው የኢኮኖሚና ፖለቲካ ለውጥ የበኩሉን ሚና እንዲወጣ፣ ለዚህም የኢትዮጵያ መንግስት ከምንጊዜውንም በላይ ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸዋል።

    አዲስ የተከፈተው ቆንስላ ጽ/ቤት ቆንሱል ጄኔራል አምባሳደር እውነቱ ብላታ በበኩላቸው የጽ/ቤቱ መከፈት በሚኒሶታ ግዛት ለሚኖሩ በሺዎች ለሚቆጠሩ የዳያስፖራ አባላት ምቹ ሁኔታና መነቃቃትን እንደሚፈጥር ገልጸዋል።

    የሴይንት ፖል ከተማ ከንቲባ ሚስተር ማልቪን ካርተር በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር ከቆንስላ ጄኔራል ጽ/ቤቱ ጋር ተቀራርቦ ለመሥራትና አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል። የካቲት 23 ቀን 2011 ዓ.ም. (ማርች 2 ቀን 2019) በከተማ ደረጃ “የኢትዮጵያ ቀን” ተብሎ እንዲከበር መወሰኑንም ጠቁመዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ኤምባሲ፤ ዋሽንግተን፥ ዲሲ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    ቆንስላ ጽ/ቤት


    Semonegna
    Keymaster

    ለመሆኑ እንቦጭን ለማስወገድ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎች የሚሠሩ የአረም ማስወገጃ ማሽነሪዎች ምን አገልግሎት እየሰጡ ነው? አሁን ሥራ ላይ ያሉት የእንቦጭ ማስወገጃ ማሽኖች ቁጥርስ ምን ያክል ነው?

    ባሕር ዳር – በጣና ኃይቅ ላይ የተከሰተውን የእንቦጭ አረም ለማስወገድ አራት ማስወገጃ መንገዶች በአማራጭነት አገልግሎት ላይ እንዲውሉ ምክረ-ሐሳብ ይቀርባል። ከእነዚህ ማስወገጃ መንገዶች እስካሁን ሁለቱ (የሕዝብ ጉልበት እና ማሽነሪዎች) ጣና ሐይቅ ዙሪያ አገልግሎት ላይ እየዋሉ ነው።

    ለመሆኑ እንቦጭን ለማስወገድ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎች የሚሠሩ የአረም ማስወገጃ ማሽነሪዎች ምን አገልግሎት እየሰጡ ነው? አሁን ሥራ ላይ ያሉት የማሽኖች ቁጥርስ ምን ያክል ነው? ስንል የአማራ ክልል የአካባቢ ደንና ዱር እንስሳት ጥበቃና ልማት ባለስልጣንን ጠየቅን።

    በዚህ ወቅት አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙት ሁለት ማሽኖች ብቻ እንደሆኑ የነገሩን በአካባቢ ደንና ዱር እንስሳት ጥበቃና ልማት ባለስልጣን የጣና ሐይቅ ሥርዓተ ምኅዳር ጥበቃ ዳይሬክተር አቶ መዝገቡ ዳኘው ሁለቱ ማሽኖች ካናዳና እሥራኤል ሀገር በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና በአማጋ ኃላፊነቱ ተወሰነ የግል ማኅበር ድጋፍ የተገዙ ናቸው ብለዋል።

    “በባሕር ዳር እና ጎንደር ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት (ዩኒቨርሲቲዎች) እየተዘጋጁ ያሉ የእንቦጭ ማስወገጃ ማሽኖች መኖራቸውን አውቃለሁ” ያሉት አቶ መዝገቡ፥ እስካሁን ድረስ ግን ከተቋማቸው ጋር ርክክብ ፈፅመው ወደ ሥራ አለመግባታቸውን ገልጸዋል።

    አብመድ የተሰሩት ማሽኖች ለምን ርክክብ ተፈፅሞ አገልግሎት መስጠት አልጀመሩም ሲል ሁለቱን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አነጋግሯል። የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ኢንስቲቲዩት ከሙላት ኢንድስትሪያል ኢንጂነሪንግ ጋር በመተባበር የሠራው የእንቦጭ ማስወገጃ ማሽን ጥቅምት 24 ቀን 2011 ዓ.ም. የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው በተገኙበት ቢመረቅም ይህ ዜና እስከሚጠናቀርበት ጊዜ ድረስ አገልግሎት አይሰጥም።

    “ማሽኑ አገልግሎት ለመስጠት ምንም ዓይነት ችግር የለበትም፤ በቅርቡም ለሦስት ወራት ያክል የሙከራ ትግበራ ከተደረገ በኋላ ከሚመለከተው አካል ጋር ርክክብ ይደረጋል” ያሉት የቴክኖሎጂ ኢንስቲቲዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ዶ/ር ሰይፉ አድማሱ የዘገየው ማሽኑን ለማንቀሳቀስ የሚሠራ ራሱን የቻለ የሰው ኃይል አደረጃጀት ባለመኖሩ ቅጥርና ምልመላ ለመፈፀም ጊዜ በመውሰዱ መሆኑን አስታውቀዋል።

    ከሙላት ኢንዳስትሪያል ኢንጅነሪንግ ጋር በመተባበር ለባለሙያዎቹ ስልጠና ለመስጠት ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን ያስታወቁት ዶ/ር ሰይፉ ስልጠናው ከተጠናቀቀ በኋላ ወደ ተግባር እንደሚገቡም ገልፀውልናል። ማሽኑን በዘላቂነት ለማስተዳደርና ሥራውን ለማስተባበር ራሱን የቻለ ተቋማዊ አደረጃጀት እንደሚያስፈልገውም ገልጸዋል።

    በጎርጎራ ወደብ አካባቢ የሚገኘው ሌላው የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የአረም ማስወገጃ ማሽንም ከአካባቢ ደንና ዱር እንስሳት ጥበቃና ልማት ባለስልጣን ጋር ርክክብ ያልተፈፀመበት ማሽን ነው። የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክተር ኢንጅነር ሰለሞን መስፍን “ለአካባቢ ደንና ዱር እንስሳት ጥበቃና ልማት ባለስልጣን ርክክብ እንዲፈፀሙ ደብዳቤ ልከናል” ብለዋል። የተዘጋጀው ማሽን አገልግሎት ለመስጠት ሙሉ በሙሉ ዝግጁ መሆኑን የገለጹት ዳይሬክተሩ፥ ማሽኑን የሚያንቀሳቅስ የሰው ኃይል (ኦፕሬተር) ማዘጋጀት የአካባቢ ደንና ዱር እንስሳት ጥበቃና ልማት ባለስልጣን ድርሻ እንደሆነም አስታውቀዋል።

    የአካባቢ ደንና ዱር እንስሳት ጥበቃና ልማት ባለስልጣን በበኩሉ ማሽኖቹን ለመረከብና የሰው ኃይል ለመቅጠር በተግር ሲሠሩ ማየት እፈልጋለሁ ብሏል።

    በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ እና በሙላት ኢንድስትሪያል ኢንጅነሪንግ የተዘጋጀው ማሽን ከ19 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ እንደተደረገበትም ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። በዚህ ሳምንት ውጭ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ድጋፍ የተገዛ ሌላ የእንቦጭ ማስወገጃ ማሽን ጣና ሐይቅ ላይ ደርሶ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።

    ምንጭ፦ አብመድ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የእንቦጭ ማስወገጃ ማሽን


    Semonegna
    Keymaster

    በተሽከርካሪ ላይ የሚገጠመው የተቀናጀ የተሸከርካሪ ፍጥነት መቆጣጠሪያ መሣሪያ ከዓለም አቀፍ ስርዓት አቅጣጫ (GPS) ጋር የተጣመረ ሆኖ ወደ ተሸከርካሪው ሞተሩ የሚገባውን ነዳጅ አሊያም አየር በመቀነስ የተሸከርካሪውን ፍጥነት የሚቆጣጠር መሣሪያ ነው።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– የመንገድ ትራፊክ አደጋ እያደረሰ ያለውን የሰው ልጅ ሞት፣ የአካል ጉዳትና የንብረት ውድመት ለመቀነስ እየተሠራ ቢሆንም አደጋው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ይገኛል። ለመንገድ ትራፊክ አደጋ መከሰት በርካታ ምክንያቶች የሚጠቀሱ ሲሆን ከተወሰነው የፍጥነት ገደብ በላይ ማሽከርከር በቀዳሚነት ከሚጠቀሱ ምክንያቶች ውስጥ በቀዳሚነት ይገኛል።

    የፌደራል ትራንስፖርት ባለስልጣን አሽከርካሪዎች ፍጥነታቸውን ቀንሰው በጥንቃቄ በማሽከርከር አደጋውን መቀነስ እንዲችሉ የግንዛቤ ሥራዎችን ከመሥራት ጎን ለጎን የተሸከርካሪዎችን ፍጥነት መገደብ እንደሚገባ በማመን በተሸከርካሪዎች ላይ የፍጥነት መገደቢያ መሣሪያ ስለመግጠም እና ስለማስተዳደር የሚገልጽ መመርያ አዉጥቷል።

    በተሽከርካሪ ላይ የሚገጠመው የተቀናጀ የተሸከርካሪ ፍጥነት መቆጣጠሪያ መሣሪያ ከዓለም አቀፍ ስርዓት አቅጣጫ (GPS) ጋር የተጣመረ ሆኖ እንደተሸከርካሪው ሁኔታ ወደ ሞተሩ የሚገባውን ነዳጅ ወይም አየር በመቀነስ የተሸከርካሪ ፍጥነት በህግ ከተደነገገ በላይ እንዳይፈጥን የሚቆጣጠር መሣሪያ ነው።

    የሚገጠመው የፍጥነት መቆጣጠሪያ ጣሪያም የፍጥነት ወሰን ህጉ በሚደነግገው ከፍተኛ የፍጥነት ወሰን ጣሪያ መሠረት ይሆናል። አሽከርካሪው በትራፊክ መቆጣጣሪያ ደንብ መሠረት ፍጥነቱን ከተፈቀደለት የፍጥነት ወሰን በታች ማሽከርከር የሚገባው ሁኔታ ሲኖር ፍጥነቱን ቀንሶ ማሽከርከር እንደሚገባ ይገልፃል።

    የፍጥነት መገደቢያው የሚገጠምላቸው ተሸከርካሪዎች የምርት ዘመናቸው እንደ አውሮፓውያን ዘመን አቆጣጠር ከ2000 እና በኋላ ያሉ ተሽከርካሪዎች ናቸው። ከተካተቱት ውጪ ያሉ ተሽከርካሪዎች ላይ የፍጥነት መገደቢያ መሣሪያው ስለሚገጠምበት ሁኔታ ባለስልጣኑ ወደፊት የሚወስን ሲሆን ይህ መመሪያ ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡና በሀገር ውስጥ የሚመረቱ ተሸከርካሪዎች ባለስልጣኑ ፍቃድ ከሰጠው አካል የፍጥነት መገደቢያ መሣሪያ የተገጠመላቸዉ ብቻ ይሆናሉ።

    ምንጭ፦ የፌደራል ትራንስፖርት ባለስልጣን / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    የተሸከርካሪ ፍጥነት


    Semonegna
    Keymaster

    የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የሴቶችን ጫና በሚያቀልሉ ቴክኖሎጂዎች ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየመከረ መሆኑን የሚኒስቴሩ የሴቶች፤ ህፃናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ኤልሳቤጥ ገብረሥላሴ አስታውቀዋል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር በ7 ክልሎች ውስጥ በቴክኖሎጂ ውጤቶች ሊደገፉ የሚችሉ ሴቶች ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደሩ ያሉ ሥራዎችን በጥናት ለይቷል።

    ችግሮቹ የተለዩት በአፋር፤ በቤኒሻንጉል፤ በጋምቤላ፤ በደቡብ፤ በአማራ፤ በትግራይና በሶማሌ ክልል በተጠናው ጥናት መሠረት መሆኑን ሚኒስቴሩ አስታውቋል።

    በፀሐይ ኃይል የሚሠራ የምግብ ማብሰያ፤ በሬ ለምኔ ዘመናዊ ማረሻ እና የቆጮ መፋቂያ ማሽን በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ሥራ እንደሚገቡ ተገልጿል። ዘመናዊ የበቆሎ መፈልፈያና የአፋ አሊ (የአፋር ቤት) መሥሪያ በመካከለኛ ጊዜ ወደ ሥራ ለማስገባት የታቀደ ሲሆን በመስመር መዝሪያ እና ከጉድጓድ ውሃ ማውጫ መሣሪያ ደግሞ በረጅም ጊዜ ወደ ሥራ ለማስገባት በዕቅድ ተይዟል።

    የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የሴቶችን ጫና በሚያቀልሉ ቴክኖሎጂዎች ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየመከረ ነው። የሚኒሰቴሩ የሴቶች፤ ህፃናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ኤልሳቤጥ ገብረሥላሴ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የሴቶችን የሥራ ጫና የሚያቃልሉና ምርታማ የሚያደርጉ ቴክኖሎጂዎች ላይ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል። ለስኬታማነቱ የሚመለከታቸው ሁሉ ድጋፋቸውን እንዲያደርጉም ዳይሬክተሯ ጥሪ አቅርበዋል።

    ምንጭ፦ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ 
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    የሴቶችን ጫና የሚያቃልሉ የቴክኖሎጂ ውጤቶች


    Semonegna
    Keymaster

    በቤተ ጉራጌ ዘንድ በወጌሻ ሕክምና ሙያቸው ስማቸው እጅግ ከፍ ብሎ የሚጠራው አቶ ፈንቅር ሳረነ ሲሆኑ፥ ይህም ሙያ ከእርሳቸው አልፎና ከልጅ ልጆቻቸው ተዋርሶ፣ አሁን የልጅ ልጆቻቸው በቤተ ጉራጌ ብቻ ሳይሆን በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች እያገለገሉ ይገኛሉ። አቶ መኮንን አመርጋ ደግሞ የአቶ ፈንቅር ሳረነ አራተኛ የልጅ ልጅ ናቸው።

    ኑሬ ረጋሳ (የጉራጌ ዞን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ)

    ወልቂጤ (ሰሞነኛ) – ከባህላዊ የሕክምና ዘዴዎች ውስጥ የወጌሻ ሕክምና አንዱ ነው። የሰዉ ልጆች በተለያዩ ምክንያቶች በአካላቸዉ ላይ የተለያዩ አደጋዎች ይገጥማቸዋል። በአንድ ወቅት በወጌሻ ፈንቅር ሳረነ በሰውነታቸው ላይ እባጭ ወጥቶባቸው ሁለተኛ ወገን ባለማግኘታቸው በቻሉት አቅም ራሳቸውን አክመው እባጩን በማዳናቸው ምክንያት አድርገው የጀመሩት የባህላዊ ወጌሻ ሙያ ከልጅ ልጅ እየተላለፈ አሁንም ድረስ የፈንቅር ሳረነ የልጅ ልጆቻቸው ከቤተ ጉራጌ ክልል አልፈው በሌሎችም ቦታዎች ህብረተሰቡን እያገለገሉ ይገኛሉ።

    አቶ ፈንቅር ሳረነ የተወለዱት በ1814 ዓ.ም. በጉራጌ ዞን ኧዣ ወረዳ የወግወረ በቢባል አካባቢ ነበር። የአካባቢው ማህበረሰብ አንደግባ የሚል የክብር ስም ሰጥቷቸዋል። በባህላዊ ሕክምና ህዝቡን የማገልገል እሳቤ ይዘው ወደ ወጌሻነት ሙያ የገቡት ፈንቅር ሳረነ ለዘመናት ህዝቡን አገልግለዋል። የወጌሻነ ሕክምና አገልግሎታቸው እና ከተለያዩ እፅዋት በባህላዊ መንገድ በመቀመም የሚያዘጋጇቸው መድኃኒቶች እስከ በጊዜው እስከ ቤተ መንግስት ድረስ አድርሷቸዋል። ፈንቅር ሳረነ የ8 ወንድ ልጆችና የአንድ ሴት ልጅ ወላጅ አባት ሲሆኑ ለአብነት ያህል ካቤ ፈንቅር ሳረነ፣ ጫሚሳ ፈንቅር፣ ድድራ ፈንቅር፣ ገብረማሪያም ፈንቅር፣ እንዱሁም ሌሎችም ይጠቀሳሉ። ወጌሻ መኮንን አመርጋ የአራተኛ የልጅ ልጅ (ማለትም ፈንቅር፣ መኮንን አመርጋ ጫሚሳ ፈንቅር) ሲሆኑ፥ እሳቸውም በሚሰጡት የወጌሻነት ሕክምና አገልግሎት አንቱታን አትርፈዋል።

    ወጌሻ መኮንን አመርጋ እንደሚሉት በባህላዊ ሕክምና ሙያ፣ ልምድና ዕውቀት የቀሰሙት የልጅ ልጅ በሆኑት በወጌሻ ወልዴ ጫሚሳ እንደሆነና ወጌሻ ወልዴ ጫሚሳ ከቤተ ጉራጌ ክልል አልፈው እስከ ስልጢ ድረስ እየዞሩ ያገለግሉ እንደነበረም ተናግረዋል። ድርድራ ፈንቅር ከጅማ እስከ ከፋ ድረስ የባህላዊ ሕክምና ሲሰጥ እንደነበረ እንዲሁም የካቤ ፈንቅር ልጆች (ለምሳሌ ዜናዬ ካቤ፣ መዝገበ ካቤ) አዲስ አበባ ላይ አገልግሎት እንደሰጡ፤ በወሊሶና አካባቢው ደግሞ ተክሌ ሙራረ በአግባቡ የወጌሻነት አገልግሎት ለህብረተሰቡ ይሰጡ እንደነበረም አስረድተዋል። የልጅ ልጅ የሆኑትን ወይዘሮ ዙሪያሽ ደግሞ አጠቃላይ ቤተ ጉራጌ በአካለለ መልኩ ቸሃ ላይ መቀመጫ አድርገው ይሠሩ እንደነበረም ጠቅሰዋል።

    የEBS ቴለቭዥን አርአያ ሰብ መርሀግብር በፈንቅር ሳረነ የሕይወት ታሪክ ላይ የሠራውን ጥንቅር እዚህ ጋር ይመልከቱ

    የወጌሻነት ሙያ ከአጎታቸው የተማሩት መኮንን አመርጋ ወልቂጤ ከተማ ላይ በመምጣት ለህብረተሰቡ አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ። ወልቂጤና አካባቢዋ የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎችን በማገልገል ተጠቃሽ የሆነው ወጌሻ መኮንን አመርጋ ለበርካታ ዓመታት ቤታቸው ውስጥ በተለያዩ ምክንያቶች የተጎዱ የህብረተሰብ ማለትም በስፖርታዊ ውድድሮች ተሰብሮና እግሩ ወልቆ ለሚመጣ፣ የተሸከርካሪ አደጋ ለደረሰበት፣ ውልቃትና መሰል አደጋ ለደረሰበት ሰው አገልግሎት በመስጠት ይታወቃሉ።

    ወጌሻ መኮንን አመርጋ የወልቂጤ ከነማ እግር ኳስ ክለብ ብሔራዊ ሊግ እያለ ለሁለት ዓመት ከመንፈቅ ያህል በወጌሻነት በማገልገል ለስፖርተኞች ጥሩ ወንድማዊ ፍቅርን በመለገስ በጫወታ ወቅት የሚደርስባቸው ጉዳት በማከም ስፖርተኞች ውጤታማ እንዲሆኑና አሁን ለደረሱበት ከፍተኛ ሊግ በሙያቸው የበኩላቸውን ሚና ተወጥተዋል። ከዚህም በተጨማሪ ለበርካታ ዓመታት የወረዳውና የዞን ውድድሮችን እንዲሁም በየዓመቱ በሚደረጉ የትምህርት ቤቶች ውድድሮች ላይ ሳይሰለቹ በቅንነት በማገልገል ስማቸው ከምስጋና ጋር ይነሳል።

    ለሙያው እና ለተገልጋዩ ህብረተሰብ ባላቸው ክብር የተነሳ በጣም ጉዳት ደርሶበት ውይም ደርሶባት መኖሪያ ቤቱ መምጣት የማይችሉት ጉዳተኞች እስከ መኖሪያ ቤታቸው ድረስ በመሄድ ሙያዊ እገዛ በማድረግ ይታወቃሉ – ወጌሻ መኮንን። አንድ ባለ ጉዳይ አገልግሎቱን ለማግኘት ከመጣ ገንዘብ እንኳን ባይኖረውም መጎዳትና አካለ ስንኩል መሆን የለበትም በማለት አገልግሎቱን በነጻ በመስጠት በጎነታቸው የሚታወቁት መኮንን ዓመርጋ፥ የወጌሻነት ሙያ ወደ ልጆቻቸው ለማስረጽ ሙያውን ሙሉ ለሙሉ እንዲያውቁት ለማድረግ የዕውቀትና የሙያ ሽግግር የማድረግ ዓላማ ይዘውም ይሠራሉ።

    በዚህም የበኩር ልጃቸው የአባቱን የወጌሻነት የጥበብ ትምህርት የእረፍት ጊዜውን በመጠቀም አባቱን በማገዝና ለህብረተሰቡ የሚሰጡትን አገልግሎት በመቅሰም ወይም ትምህርት በመውሰድ፣ ወጌሻ መኮንን ራቅ ወዳለ ቦታ ከሄዱ አገልግሎት ፈልገው ለሚመጡ ደንበኞች አገልግሎት እየሰጠ እንደሆነና ሙያውን ሙሉ ለሙሉ አውቆ በእረፍት ጊዜው እየሠራበት እንደሆነም ወጌሻ መኮንን ገልጸዋል።

    መንግስት የባህላዊ ሕክምናው ዘርፍ ለማዘመን ነጻ የትምህርትና ስልጠና እድል በማመቻቸት የሕክምናውን ሳይንስ እንዲያውቁት በማድረግ ረገድ ውስንነት መኖሩን አስታውቀው፥ የጤናውን ትምህርት ባይወስዱም ህብረተሰቡን እያገለገሉበት ያለውን የወጌሻ ሙያ ዕውቀታቸውን የበለጠ ለማዳበር ቴክኖሎጂ በመጠቀም እና ሀኪም ጓደኞቻቸውን በማማከር ትምህርት እየተማሩ እንደሆነና በሥራ ላይ የሚገጥማቸውን ውስንነት እየቀረፉ እንደሆነም አስረድተዋል። በሳምንት በርካታ ሕመምተኞች በቀላልና ከባድ አደጋ ቤት ድረስ መጥተው አገልግሎት እንደሚያገኙ የተናገሩት መኮንን ዓመርጋ በከተማው ለበርካታ ዓመታት አገልግሎት የሚሰጡት በመኖሪያ ቤታቸው ሲሆን መንግስት በከተማው ሴንተር ቦታዎች ላይ ቋሚ መሥሪያ ቦታ ቢያመቻችላቸው የበለጠ ለህብረተሰቡ ቀልጣፋና ውጤታማ አገልግሎት መስጠት ያስችላቸዋል።

    የወጌሻ ሙያ ከጀመሩ ብዙ ዓመታትን ያስቆጠሩት መኮንን በሥራ ላይ ብዙ ገጠመኞች እንደገጠማችው አስታውሰው ለአብነት ያህል በአንድ ወቅት በእግር ኳስ ሜዳ ላይ አንድ አጥቂ ጎል ለማግባት ሲል እርስ በእርስ ተጋጭተዉ ላንቃው ሙሉ ለሙሉ ተዘግቶ ምላሱን ማንቀሳቀስ አቅቶት ሊሞት ሲል አንደምንም ርብርብ አድርገን አፉን በመክፈት በባንድራ እንጨት አፉን በመክፈት ወደ ሕክምና ማእከል በመውሰድ እንዳዳኑትም ተናግረዋል።

    አቶ ኢሳያስ ናስር ቀደም ሲል የወልቂጤ ከነማ ሥራ አስኪያጅ የነበሩ ሲሆ ወጌሻ መኮንን ዓመርጋ ከሕክምናው ሙያው በተጨማሪ ክለቡን ውጤታማ እንዲሆን ከፍተኛ መስዋትነት የከፈሉ ምርጥ ባለሙያ ናቸው ብለው ይመስክሩላቸዋል። አክለውም፥ ስፖርተኞች የከፋ አደጋ እንኳን ቢደርስባቸው ጊዜያቸውንና ዕውቀታቸውን በመጠቀም የተቻላቸውን ጥረት በማድረግ ጉዳት የደረሰባቸው ሲታደጉ ነው የሚታዩት። ከስፖርተኞች ጋር ጥሩ ፍቅር በማሳየት ከብሔራዊ ሊግ ጀምሮ ክለቡ አሁን ለደረሰበት ሁኔታ የአንበሳውን ሥራ ሰርተዋል፤ አሁንም ድረስ በበጎ ፍቃደኝነት በሙያው አገልግሎት በመስጠት ናቸው በማለት የወጌሻ መኮንን አመርጋ ታታሪነት ይመሰክራሉ። አቶ ኢሳያስ በመቀጠልም የሙያና የዕውቀት ሽግግር እንዲኖር ለማድረግ መንግስት እነዚህ የወጌሻ ባለሙያተኞች በተገቢው ምቹ የሥራ ቦታ ቢያመቻችላቸው የተሻለ ሥራ እንዲሠሩ ያስችላቸዋል ብለዋል።

    አንዳንድ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ የህብረተሰብ ክፍሎች በሰጡት አስተያየት ወጌሻ መኮንን ዓመርጋ ቅንና ለሙያው ክብር ሰጥተው የሚሠሩ ባለሙያ እንደሆኑ፣ ሰውን ለማዳን እንጂ ገንዘብ ማትረፍን ዓላማ አድርገው የማይሠሩና አቅም ለሌላቸው በነጻ ሕክምና እንዲያገኙ በማድረግ ከህመማቸው እንዲድኑ ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት የሚያደርጉ ባለሙያ መሆናቸውን ይመሰክሩላቸዋል። የዚህ ጹሁፍ አዘጋጅም ወጌሻ መኮንን ዓመርጋ በሙያው ያላቸውን የካበት ልምድ እና ህብተረሰቡን ለማገልገል ያላቸውን ከፍተኛ ፈላጎት ከግምት ውስጥ በማስገባት ለሙያው ያላቸውን መልካም ፍቃድ የበለጠ አጠናክሮ እንዲሰራበትና በተለያዩ ምክንያቶች የአካል ጉዳት የሚደርስባቸው የህብረተሰብ ክፍሎችን እንዲታደግ እያልኩኝ ወጌሻ መኮንን ዓመርጋ መንግስት በዘርፉ ውጤታማ ሥራ እንዲሰራ የመስሪያ ቦታ እንዲያመቻችለት እና ተተኪ ባለሙያተኞች መፍጠር ይኖርበታል።

    ምንጭ፦ የጉራጌ ዞን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    መኮንን ዓመርጋ


    Semonegna
    Keymaster

    ለገጣፎ ለገዳዲ ከተማ መኖሪያ ቤታቸው ለፈረሱባቸው ዜጐች ተገቢዉን ድጋፍ እና ተመጣጣኝ ካሳ በአስቸኳይ እንዲያደርጉና በሠላም የመኖር መብታቸውን እንዲያስጠብቁላቸው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ (ሰመጉ) ጠይቋል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – በአዲስ አበባ ዙሪያ ኦሮሚያ ልዩ ዞን፣ ለገጣፎ ከተማ፣ የዜጐች መኖሪያ ቤት መፍረሱ በእጅጉ እንዳሳሰበው የገለፀው የተባበሩት መንግስታት (ተመድ)፥ ጉዳዩን በትኩረት እንደሚመረምር አስታውቋል። በተባበሩት መንግስታት የመኖሪያ ቤት ምጣኔ ኃላፊዋ ለይላኒ ፋራህ (Ms. Leilani Farha) እንደገለፁት፥ በለገጣፎ 12ሺህ ቤቶች እንዲፈርሱ መወሰኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን ቤት አልባ አድርጐ፣ ለእንግልት ይዳርጋል፤ ይህም ግልጽ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ነው ብለዋል።

    ስለ ቤቶቹ መፍረስ መረጃው ለተቋማቸው መድረሱን ያረጋገጡት ለይላኒ ፈራህ፥ በቀጣይ ጉዳዩ በልዩ መርማሪዎች ተመርምሮ፣ በዚህ ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት ላይ የተሳተፉ ወገኖች እንዲጋለጡ ይደረጋል ብለዋል። የዜጐችን መኖሪያ ቤት በዚህ መልኩ ማፍረስ በተባበሩት መንግስታት፣ ሀገራት ቃል ኪዳን የገቡለትን የማንኛውም ዜጋ፣ መጠለያ መኖሪያ ቤት የማግኘት መብት በእጅጉ የሚፃረር ነው ብለዋል – ኃላፊዋ።

    በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ (ሰመጉ) በለገጣፎ ዜጐች መጠለያ አልባ መደረጋቸውን በጽኑ አውግዞ፥ ቤት ለፈረሰባቸው ወገኖች፣ የፌደራል መንግስትና የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ተገቢውን ድጋፍና ተመጣጣኝ ካሣ በአስቸኳይ እንዲያቀርብ እንዲሁም እየተካሄደ ያለው የመኖሪያ ቤቶችን የማፍረስና ዜጐችን የማፈናቀል ተግባር በአስቸኳይ እንዲቆም ጠይቋል።

    የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ በጉዳዩ ላይ ያወጣው መግለጫ የሚከተለው ነው።

    ዜጐችን ማፈናቀል በአስቸኳይ ይቁም!!

    በኦሮሚያ ክልል አዲስ አበባ ዙሪያ ልዩ ዞን የለገጣፎ ለገዳዲ ከተማ አስተዳደር በ01 እና 02 ቀበሌዎች፣ ጭላሎ፣ ወበሪ፣ ለገዳዲ ቄራ፣ ገዋሳ፣ እና በከተማዋ ውስጥ በሚገኙ የተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ መኖሪያ ቤቶችን “ህገወጥ ግንባታዎች ናቸው፤ ለአረንጓዴ ልማት ይፈለጋሉ” በማለት ከየካቲት 12 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ በኃይል በማፍረስ ላይ ይገኛል። የከተማዋ ከንቲባ ለመገናኛ ብዙሃን እንደገለፁትም በቀጣይም ከ12 ሺህ በላይ ቤቶችን እንደሚያፈርሱም አረጋግጠዋል። ሰመጉ ስለጉዳዩ የከተማዋን ከንቲባ ለማነጋገር ያደረገው ጥረት አልተሳካም።

    ሰመጉ ያነጋገራቸው ቤቶቻቸው የፈረሱባቸው በርካታ ዜጐች እንዳስረዱት ከ1997 ዓ.ም. ጀምሮ በመንግስት ላይ እምነታቸውን ጥለው በተለያየ ወቅት በገዙት ቦታ ላይ የገነቡትን መኖሪያ ቤቶች በመገንባት እና አካባቢ በማልማት ከተማዋን ለእድገት አብቅተዋታል። በእነዚሁ ዓመታት ውስጥም የአካባቢው የመንግስት ኃላፊዎች እያወቁት የመብራት እና ውሃ አገልግሎት ተጠቃሚዎች መሆናቸውን፣ ግብር ሲከፍሉ መቆየታቸውን፤ በተለያዩ አስተዳደራዊና የልማት እንቅስቃሴ ላይ የነቃ ተሳትፎ ሲያደርጉ መቆየታቸውንም አስረድተዋል። ይሁን እንጂ የከተማዋ አስተዳደር ከክልሉ ፖሊስ ጋር በመተባበር ከነዋሪዎች ጋር በቂ ምክክር ሳያደርግ እና ሊመጣ የሚችለውን ሰብዓዊ ቀውስ ላይ ምንም ዓይነት ቅድመ ዝግጅት ሳይኖረው ቤቶችን በማፍረስ ህፃናት፣ ሴቶችና አቅመ ደካሞችን ጨምሮ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጐች ሜዳ ላይ እንዲወድቁ አድርጓል። በዚህም የዜጐችን ለኑሮ አመቺ በሆነ አካባቢ የመኖርን መብት፣ ንፁህ የመጠጥ ውሃና ምግብ የማግኘት መብት፣ የአካል ደህንነት መብት እንዲሁም ሌሎች ተያያዥ መብቶች ተጥሰዋል።

    የከተማው አስተዳደር የወሰደውን የኃይል እርምጃ ይበልጥ አስከፊ እና አጠያያቂ የሚያደርገው ከመኖሪያቸው በ7 ቀናት የማስጠንቀቂያ ጊዜ በኃይል እንዲፈናቀሉ ለተደረጉ ዜጐች ምንም ዓይነት አማራጭ የመኖሪያ ስፍራም ሆነ ጊዜያዊ የመጠለያ ስፍራ ያልተዘጋጀላቸውና ሰብዓዊ እርዳታም ያልተደረገላቸው መሆኑ ነው።

    የፌዴራል መንግስትም ሆነ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በዜጐች ላይ እየተፈፀመ ያለውን መጠነ ሰፊ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ተገቢውን ትኩረት በመስጠት፤ እየተካሄደ ያለውን የመኖሪያ ቤቶች ማፍረስና ዜጐችን ማፈናቀል በአስቸኳይ እንዲያስቆሙ፣ መኖሪያቸው ለፈረሱባቸው ዜጐች ተገቢዉን ድጋፍ እና ተመጣጣኝ ካሳ በአስቸኳይ እንዲያደርጉና በሠላም የመኖር መብታቸውን እንዲያስጠብቁላቸው ሰመጉ ይጠይቃል።

    ምንጮች፦ አዲስ አድማ ጋዜጣሰመጉሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ


    Anonymous
    Inactive

    የኢትዮጵያ የምግብ፣ የመድኃኒት እና ጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን አገልግሎቱን በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ማዘመኑን ይፋ አደረገ
    —–

    የኢትዮጵያ የምግብ፣ የመድኃኒት እና ጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን የምግብና መድኃኒት ፈቃድ አሰጣጥ፣ የመድሃኒት ግዢ ፈቃድ፣ የምግብና መድኃኒት የብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ አሰጣጥን ቀልጣፋና ግልፅ የሚያደርግ ዘመናዊ አሰራርን መተግበር ጀምሬያለሁ ብሏል፡፡ዛሬ በሒልተን ሆቴል በተካሄደው የአገልግሎቱ ማስታወቂያ መርሃ ግብር ተገኝተን እንደሰማነው እስካሁን በማኑዋል የነበረው የተቋሙ አሰራር በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ታግዞ የተሻለ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል፡፡

    eRIS የተባለው ኤሌክትሮኒክ የቁጥጥርና የመረጃ ስርዓት ወደ አገር ውስጥ የሚገቡ የምግብና የመድኃኒት ምርቶችን ደህንነት የማረጋገጥ ስራውን የሚያሻሽል ነው ተብሏል፡፡የምዝገባ ሥርዓቱን ማዘመን የመድሃኒት አቅርቦት እጥረትን ለመቀነስ ያስችላል የሚል ተስፋም ተጥሎበታል ተብሏል፡፡ የካቲት 20 ቀን 2011 ዓም ይፋ የተደረገው ዘመናዊ አሠራር በቅርቡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፀደቀው የምግብና መድሃኒት ቁጥጥር አዋጅ አንድ አካል መሆኑንም ሸገረ ኤፍ ኤም ራድዮ ዘግቧል፡፡

    ምንጭ፦ ሸገረ ኤፍ ኤም ራድዮ

    Anonymous
    Inactive

    የሞጆ ሃዋሳ የፍጥነት መንገድን በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው
    —–

    በተለያዩ ምክንያቶች ግንባታው የተጓተተውን የሞጆ ሃዋሳ የፍጥነት መንገድን በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን አስታወቀ።

    ከሞጆ ተነስቶ ሀዋሳ ከተማን መዳረሻው የሚያደርገው የፈጣን መንገድ ፕሮጀክት በ2008 ዓ.ም ነበር ግንባታው የተጀመረው።

    201 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነውን መንገድ በፍጥነት ለማጠናቀቅም በአራት ምዕራፍ በመከፋፈል ለመገንባት ታቅዶ ወደ ስራ ተገብቷል።

    ሆኖም የፍጥነት መንገዱ በተያዘለት ጊዜ ግንባታው እየተከናወነ አለመሆኑን ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በተለያየ ጊዜ ባደረገው ቅኝት መታዘብ ችሏል።

    ከሞጆ መቂ፣ ከመቂ ባቱ፣ ከባቱ አርሲ ነጌሌ እና ከአርሲ ነጌሌ ሃዋሳ ለተለያዩ ተቋራጮች የተሰጠው ፕሮጀክት፥ የወሰን ማስከበር ችግር፣ በግብዓት አቅርቦትና መሰል ችግሮች ሳቢያ በፍጥነት መገንባት አለመቻሉን የባለስልጣኑ የኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሳምሶን ወንድሙ ተናግረዋል።

    የሞጆ መቂው የመንገዱ አንድ ምዕራፍ አሁን ላይ አፈጻጸሙ 70 በመቶ የደረሰ ሲሆን፥ በአንጻሩ 37 ኪሎ ሜትር ከሚረዝመው ከመቂ ባቱ መንገድ ውስጥ እስካሁን 14 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር ብቻ መስራት እንደተቻለ ነው የተናገሩት።

    57 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለውና ከባቱ አርሲ ነጌሌ ከሚደርሰው የፍጥነት መንገዱ አካልም ከ1 ነጥብ 5 በመቶ በላይ ስራውን ማከናወን አልተቻለም።

    በሌሎቹ የመንገዱ አካል የተስተዋለው ችግርም በባቱ አርሲ ነጌሌ መንገድ ተደግሟል የሚሉት ዳይሬክተሩ፥ የመንገዱ ግንባታ የተደቀነበት ስጋት እንዳይቀጥል መፍትሄ ተቀምጧል ብለዋል።

    ከየአካባቢው መስተዳድር ጋር ውይይት በማድረግም በቅርብ ክትትል ፈጣን መንገዱን ለማጠናቅቅ ባለስልጣኑ እየሰራ መሆኑንም አንስተዋል።

    አሁን ላይም በፕሮጀክቱ ከዚህ ቀደም ያጋጠመውን የወሰን ማስከበርና መሰል ችግሮችን በመቅረፍ ግንባታው እየተፋጠነ ይገኛልም ነው ያሉት አቶ ሳምሶን ወንድሙ።

    201 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የሞጆ – ሃዋሳ የፍጥነት መንገድ በ14 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር እየተገነባ ሲሆን በ2013 ዓ.ም እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል።

    የመንገዱ ግንባታ የሃገሪቱን የወጪ ንግድ ከማሳለጥ ባለፈም ቀጠናዊና አህጉራዊ ትስስርን ለመፍጠር ግብ ላላት አፍሪካ ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ተብሏል።

    ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ

    Anonymous
    Inactive

    ለ123ኛው የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል የሚደረገው ዝግጅት መጠናቀቁን የአዲስ አበባ አስተዳደር አስታወቀ
    —–

    123ኛው የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል ምክንያት በማድረግ ለበዓሉ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ።

    የከተማ አስተዳደሩ የኪነ ጥበብ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ዛሬ በሰጠው መግለጫ በዓሉ የአድዋ ድልን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ በሚያስችሉ የተለያዩ መርሃ ግብሮች ታስቦ ይውላል ብለዋል።

    የቢሮው ኃላፊ ረዳት ፕሮፌሰር ነብዩ ባዬ በሰጡት መግለጫ የአድዋ ድል የአባቶች ተጋድሎ መስዋዕትነት የሚዘከርበት በዓል ነው ብለዋል።

    በዋዜማው በጣይቱ ሆቴል የኪነጥበብ ድግስ መዘጋጀቱም በመግለጫው ተገልጿል።

    በተመሳሳይ በዋዜማው በሚኒሊክ አደባባይ የተለያዩ ትያትር ቤቶች የባህል ትሪዒቶችን ጨምሮ የተለያዩ ዝግጅቶችን ያቀርባሉ።

    በዕለቱም በሚኒሊክ አደባባይ ድሉን በማስመልከት የተለያዩ መርሃግብሮች ይከናወናሉ።

    በምኒሊክ አደባባይ የሚኖረው መርሃግብር ከተጠናቀቀ በኋላም ከሚኒሊክ አደባባይ እስከአድዋ ድልድይድረስ የእግር ጉዞ ይካሄዳል።

    ድሉን ከትውልድ ወደ ትውልድ ለማስተላለፍ በማሰብ በተጨማሪም በዕለቱ በእንጦጦ ቤተመንግስት ግብር የማብላት ስነስርዓት ይከናወናል።

    ከ8 ሰዓት ጀምሮ ደግሞ በመስቀል አደባባይ አንጋፋና ወጣት አርቲስቶች የተለያዩ ዝግጅቶችን እንደሚያቀርቡም ይጠበቃል።

    በተያያዘም 123 የአድዋ ድል ለማሰብ የደራሼ ባህል ቡድን አባላት አዲስ አበባ ገብተዋል።

    የአድዋ ድል ከ123 ዓመታት በፊት በአድዋ ተራሮች ላይ የተደረገ ኢትዮጵያውን አባቶች አውሮፓዊውን ቅኝ ገዢ ጣሊያንን መክተው የመለሱበት መሆኑ ይታወሳል።

    ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ

    Anonymous
    Inactive

    ኢትዮጵያ በጣሊያን ወራሪ መንግስት ለተፈፀመባት ዘግናኝ እልቂት ተገቢ ካሳ እንድትጠይቅ ጥሪ ቀረበ
    —–

    ከ82 ዓመታት በፊት ኢትዮጵያ በወራሪው የኢጣሊያን መንግስት በተፈፀመባት ወረራ በግፍ ለተሰውት ንፁሃን ዜጐችና ለወደመባት ንብረት ተገቢ ካሳ ሊከፈላት እንደሚገባ የሚጠይቅ አለም አቀፍ ንቅናቄ መጀመሩ ይፋ ሆነ፡፡

    አለምአቀፍ ህብረት ለፍትህ የኢትዮጵያ ጉዳይ (Global alliance for Justice the Ethiopian Case) የተባለው አለም አቀፍ ድርጅት ይፋ ያደረገው ይኸው መረጃ እንደሚያመለክተው፤ የየካቲት 12/1929 ዘግናኝ እልቂትን ጨምሮ ጣሊያን በአምስት ዓመቱ የወረራ ዘመን ከአንድ ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያንን በግፍ የጨፈጨፈች ሲሆን ለዚህ ኢ-ሰብአዊ ድርጊቷ ለኢትዮጵያ መንግስት ተገቢ ካሳ ልትከፍልና ህዝቡን በይፋ ይቅርታ ልትጠይቅ ይገባል ተብሏል፡፡

    በድርጅቱ ይፋ የተደረገው መረጃ እንደሚያመለክተው፤ አገራት በተለያዩ ጊዜያት ወረራ በመፈፀም በግፍ ለጨፈጨፏቸው ንፁሀን ዜጐችና ላወደሙት ንብረት በቢሊዮኖች የሚቆጠር ካሳ እየከፈሉና ህዝቡን በይፋ ይቅርታ እየጠየቁ ይገኛሉ። በደል የተፈፀመባቸው አገራትም ሊከፈላቸው የሚገባውን የካሳ መጠን በመግለጽ፣ ጥያቄ እያቀረቡ ሲሆን የኢትዮጵያ መንግስት ግን እስከአሁን ምንም አይነት ጥያቄ ሳያቀርብ ቀርቷል፡፡

    ሙሉ ታሪኩን አዲስ አድማስ ላይ ያንብቡ

Viewing 15 results - 526 through 540 (of 730 total)