Search Results for 'ጎንደር ዩኒቨርሲቲ'

Home Forums Search Search Results for 'ጎንደር ዩኒቨርሲቲ'

Viewing 5 results - 31 through 35 (of 35 total)
  • Author
    Search Results
  • Semonegna
    Keymaster

    ግንባታው ስድስት ዓመታትን የፈጀው የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በቀን 2000 የሚሆኑ ታካሚዎችን ሊያስተናግድ የሚችል፣ 11 የቀዶ ሕክምና ክፍሎች እና 500 አልጋዎች አንዳሉት ተገልጿል።

    ባሕር ዳር (ሰሞነኛ ኢትዮጵያ) – የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በ207 ሚሊዮን ብር ወጪ ያስገነባው ጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ነገ በሦስት አገሮች መሪዎች ይመረቃል።

    የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘ እና የሕክምና ኮሌጅ የሥራ አፈጻጸም ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር የሺጌታ ገላው በጋራ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ዩኒቨርሲቲው የግንባታ ወጪው 207 ሚሊዮን ብር የፈጀውና ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ የሆነውን ጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የፌደራልና የክልል ባለስልጣናት በተገኙበት ህዳር 1 ቀን 2011 ዓ.ም. በድምቀት እንደሚያስመርቅ ገልጸዋል።

    በምረቃ ሥነ ስርዓቱ ላይ ከሦስቱ መሪዎች በተጨማሪ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸውና ሌሎችም ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ ባለስልጣናትና ጥር የተደረገላቸው እንግዶች ይገኛሉ ፕሮፌሰር የሺጌታ ተናግረዋል።

    ከዚሁ መግለጫ ጋር አብሮ እንደተጠቀሰው በዩኒቨርሲቲው የሕክምና ኮሌጅ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ 148 የህክምና ተማሪዎችም ከኮሌጁ ለስድስተኛ ጊዜ ይመረቃሉ።

    በእነዚህ የሆስፒታሉ እና የተማሪዎቹ ምረቃ መርሀ ግብር ላይ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ (ኢፌዴሪ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)፣ የኤርትራ ሀገረ ግዛት ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂና የሱማልያ ፌደራላዊ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት መሐመድ አብዱላሂ መሐመድ በተገኙበት ይከናወናሉ።

    የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንቱ ዶክተር ፍሬው ተገኘ እንደገለጹት በመሪዎቹ የሚመረቀው ሆስፒታሉ የቀዶ ህክምና የሚጠይቁና ወደ ክፍተኛ ሕክምና መስጫ ቦታ የተላኩ (referral) በሽታዎችን የሚያክምና በተለያዩ የትምህርት ክፍሎች (ዲፓርትመንቶች) ውስጥ በሕክምና እና በጤና ባለሙያነት ተማሪዎችን የሚያሰለጥን ነው።

    Ethiopia: Are Ethiopian hospitals constructed in environment-suitable and climate-friendly way?

    ግንባታው ስድስት ዓመታትን የፈጀው ጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በቀን 2000 የሚሆኑ ታካሚዎችን ሊያስተናግድ የሚችል፣ 11 የቀዶ ሕክምና ክፍሎች ያሉት፣ 500 አልጋዎችን መያዝ የሚችል መሆኑን ፕሮፌሰር የሺጌታ አብራርተዋል። በክልሉ ካሉት ስፔሻላይዝድ ሆስፒታሎች በጥራትም ሆነ በአገልግሎት የተሻለ ሆኖ ለመገኘት መዘጋጀቱንም ገልጸዋል።

    ሀምሌ 7 ቀን 2006 ዓ.ም. ከተመረቀው የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ሆስፒታል በመቀጠል በክልሉ ስድስተኛ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እንደሚሆን አስታውቀዋል። አያይዘውም ሆስፒታሉ ለምርቃቱ ቀን ይብቃ እንጅ እጅግ ዘመናዊ የሆኑ የህክምና ቁሳቁሶችና ሌሎች መሟላት ያለባቸው ነገሮች ስላሉ ከመንግስት በተጨማሪ ለጋሽ አካላትና በዚህ ዙሪያ የሚሠሩ ወገኖችን ትብብር የሚጠይቅ መሆኑን ገልጸዋል።

    ሚያዝያ 28 ቀን 1992 ዓ.ም በኢፌዴሪ የትምህርት ሚኒስቴር ስር በሙሉ ዩኒቨርሲቲነት የተመረቀው የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሀገሪቱ ውስጥ ካሉት ግዙፍ ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ ሲሆን፥ በ2010 ዓ.ም  52,830 ተማሪችዎችን፣  219 የትምህርት  ዘርፎች (69 በመጀመሪያ/ባችለር ዲግሪ፣ 118  በሁለተኛ/ማስተር  እና 32 በሶስተኛ/ዶክትሬት ዲግሪዎች) ተቀብሎ ያስተምራል። ዩኒቨርሲቲው ስምንት ካምፓሶች ሲኖሩት፥ በውስጣቸውም አምስት ኮሌጆች፣ አራት ተቋማት (institutes)፣  ሁለት ፋኩልቲዎችና አንድ የሕግ ትምህርት ቤት (School of Law)  አሉት።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል

    Semonegna
    Keymaster

    ሐረማያ (ሐዩ) – ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የምርምር ተቋም የተገኙ 78 ምርጥ የአዝዕርት ዝርያዎችን ከአርሶ አደሩ ጋር በማብዛት እንዲሰራጭ እያደረገ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገለጸ።

    በዞኑ በማኅበር የተደራጁ አርሶ አደሮች ከዩኒቨርሲቲው የግብርና እና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ ጋር በመሆን ምርጥ ዘር የማባዛት ሥራ ላይ ተሰማርተው ውጤታማ እየሆንን እንገኛለን ሲሉ ተናግረዋል።

    የዩኒቨርሲቲው የተቀናጀ የዘር ዘርፍ ልማት ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ አቶ ደንደና ገልሜሳ “ከሐረማያ ዩኒቨርሲቲና ከአገሪቱ የተለያዩ የምርምር ተቋማት የተገኙ ምርጥ ዘሮችን በማሳ የተግባር ሥራ በማከናወን የመምረጥና የማባዛት ሥራ ከአርሶ አደሩ ጋር እየተከናወነ ይገኛል” በማለት ገልጸዋል።

    በምዕራብና ምሥራቅ ሐረርጌ ዞን በስምንት ወረዳ 38 ቀበሌ ገበራት ውስጥ ማኅበር በሚከናወነው ሥራ 3ሺህ አርሶ አደሮች በማኅበር ተደራጅተው በስንዴ፣ በቆሎ፣ ማሽላ፣ ቦሎቄ እና ሌሎች ሰብሎች ላይ የዘር መረጣና ብዜት ሥራ ላይ ተሳታፊ መሆናቸውን አቶ ደንደና ተናግረዋል፤ ከነዚህ ውስጥም 1ሺ 200 ሴት አርሶ አደሮች መሆናቸውን ጠቁመዋል።

    ሰብሎቹም የዝናብ እጥረትን እና በሽታን ተቋቁመው ምርት የሚሰጡ መሆናቸውን ጠቁመው በአሁኑ ወቅትም አርሶ አደሩ የሚስማማውን የአዝዕርት ዓይነት እየለየ እና ለሌሎች አርሶ አደሮች ዘሩን እያሰራጨ እንደሚገኝ ጠቁመው በዚህም 23 በዘር ብዜት የተሰማሩ የአርሶ አደር ማህበራት ከፍተኛውን ሚና እያበረከቱ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

    ባለፉት ጊዜያት ምርጥ ዘሩን ያለምንም የሙከራ ሥራ ለአርሶ አደሩ ይሰራጭ ነበር ያሉት አቶ ደንደና የአሁኑ ቴክኖሎጂ ግን አርሶ አደሩ በማሳው ላይ ሰብሉን አብቅሎ ውጤቱን በመመልከት የሚበጀውን ለይቶ እንዲመርጥ እየተደረገ በመሆኑ ቴክኖሎጂው ለየት እንደሚያደርገው አስረድተዋል። በዚህም በዞኖቹ የሚገኙ የዘር አቅራቢ ማህበራት፣ ምርጥ ዘር አቅራቢ ድርጅቶች የግብርና ቢሮዎችና ባለሞያዎች ከዩኒቨርሲቲው ተመራማሪዎችና ከቴክኖሎጂው ልምድ እንዲቀስሙ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።

     

    በምሥራቅ ሐረርጌ ዞን የኩርፋ ጨሌ ወረዳ የግብርና ባለሞያ የሆኑት አቶ ግዛው ልኬለው እንደሚገልጸው ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በወረዳው ህዳሴ፣ ኪንግ በርድና ኦበራ የተባሉ ሶስት የስንዴ ዝርያዎቸ እንዲሁም ከደቡብ ጬንቻ የመጣውን አፕል ዝርያዎችን ከአርሶ አደሩና ከግብርና ባለሞያ ጋር በተግባር ሥራ እየመረጥን እንገኛለን ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

    ተመራማሪው፣ የግብርና ባለሞያና አርሶ አደሩ በጋራ እየሠራን በሚገኘው ተግባር ተኮር የዘር መረጣ የአካባቢውን የዝናብ እጥረት እጥረትን እና በሽታ ተቋቁሞ ምርት የሚሰጠውን ህዳሴ የተባለውን ዝርያ አርሶ አደሩ መርጧል እኛም እንዳየነው ትክክል ሆኖ አግኝተነዋል በማለት አቶ ግዛው ስለተገኘው ውጤት ያስረዳሉ። የአፕል ዝርያም ለ16 አርሶ አደሮች ተሰጥቶ ሙከራ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመው እንዲህ ዓይነቱ ተግባር ተኮር ቴክኖሎጂ አርሶ አደሩን እያነሳሳ ስለሚገኝ መበረታታት አለበት ብለዋል።

    ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በተለይ ከሴት አርሶ አደሮች ጋር በሚሠራው ተግባር ተኮር የዘር መረጣ እኛ ሴቶች ተጠቃሚ ሆነናል፤ በአንድ ዓመትም 25 ኩንታል ምርጥ የስንዴ ዘር በማምረት ለአካባቢው አርሶ አደሮች አንዱን ኩንታል በ4ሺ ብር ሸጠናል ያለችው በሜታ ወረዳ ዱርሲቱ ቢሊሱማ ቀበሌ ገበሬ ማኅበር በዘር ብዜት ሥራ በማኅበር የተደራጀችው ሴት አርሶ አደር ሚሥራ አደም ናት።

    በቀርሳ ወረዳ ወተር ቀበሌ ገበሬ ማኅበር በዘር ብዜት ሥራ የተሰማራው ሌላው አርሶ አደር ሸረፍ ኡመሬ ከዩኒቨርሲቲው ጋር በቦሎቄ፣ ስንዴ፣ ድንች እና ሌሎች ምርጥ የሰብል ዝርያዎችን በተግባር የምርምር እያመረቱ እና ለአካባቢው ተስማሚ የሆነውን ዝርያ ለሌሎች እያሰራጨን እንገኛለን፤ በዚህም ቀደም ሲል ይጠቀሙት የነበረው የድንችና የስንዴ በክረምት ወቅት ብቻ የሚበቅል እና በሽታን የመቋቋም አቅሙ ደካማ እንደነበር ገልጸው በአሁኑ ወቅት ግን በተግባር የሰሩት ኪንግ በርድ የተባለው የስንዴና ቡቡ የተሰኘው የድንች ዝርያ በሽታን ተቋቁሞ የተሻለ ምርት የሚሰጥ በመሆኑ መምረጣቸውን ተናግረዋል።

    ምንጭ፦ የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ

    ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ

    Semonegna
    Keymaster

    ጂንካ ዩኒቨርሲቲ እስካሁን ድረስ በ14 የትምህርት ክፍሎችን በመክፈት ተማሪዎችን እያስተማረ መሆኑንና የኒቨርሲቲው የትምህርት ክፍሎቹን ወደ 41 ለማሳደግ ዕቅድ ይዞ እየሠራ መሆኑንም የኒቨርሲቲው ፕሬዚደንት ተናግረዋል።

    ጂንካ፣ ደቡብ ኦሞ ዞን (ዋልታ) – ጂንካ ዩኒቨርሲቲ በ2011 ዓ.ም የትምህርት ዘመን 1ሺ 500 አዳዲስ ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጅት እያደረገ መሆኑን አስታወቀ።

    የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ፕሮፌሰር ገብሬ ይንቲሶ ለዋልታ እንደገለጹት በዘንድሮ የበጀት ዓመት እና የትምህርት ዘመን የተማሪዎችን ቅበላ የተሳካ ለማድረግ በሁለት ዘርፍ የተከፈሉ ዝግጅቶች እየተካሄዱ ይገኛሉ።

    የኒቨርሲቲው የዘንድሮ ዓመትን የመማርና ማስተማር ሂደቱን ለማስጀመር የመምህራን ዝግጅትን ጨምሮ የተማሪዎች የአገልግሎት መስጪያ ተቋማት የሆኑት ቤተ መጽሐፍትና የመመዝገቢያ ሥፍራዎች በቴክኖሎጂ የታገዙ እንዲሆኑ የማስቻል ሥራዎች ተከናውነዋል ብለዋል ፕሬዚደንቱ።

    በጂንካ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች አገልግሎት መስጪያ ህንጻዎች ግንባታ መዘግየታቸውን የገለጹት ፕሮፌሰር ገብሬ አዳዲስ ተማሪዎችን በጊዚያዊ የመጠሊያ ህንጻዎች እንዲገቡ ለማድረግ ዝግጅት እየተደረገ ነው ብለዋል። የጂንካ ዩኒቨርሲቲ የዘንድሮ ዓመት የተማሪዎች የመግቢያ ቀንም እስካሁን አለመቆረጡን ፕሬዚደንቱ አያይዘው ገልጸዋል።

    ጂንካ ዩኒቨርሲቲ እስካሁን ድረስ በ14 የትምህርት ክፍሎችን በመክፈት ተማሪዎችን እያስተማረ መሆኑንና የኒቨርሲቲው የትምህርት ክፍሎቹን ወደ 41 ለማሳደግ ዕቅድ ይዞ እየሠራ መሆኑንም ፕሬዚደንቱ አብራርተዋል።

    አዳዲስ የሚከፈቱት የትምህርት ዘርፎችም በደቡብ ኦሞ ዞን የሚታዩ የሙያ ክፍተቶችን ለመሙላት በሚያስችል መልኩ የሚከፈቱ መሆኑም ተገልጿል።

    የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ባለፈው ዓመት 1ሺህ 100 ያህል ተማሪዎችን የተቀበለ ሲሆን በዘንድሮ ዓመት 1ሺ500 አዳዲስ ተማሪዎችን በመቀበል በአጠቃላይ ተማሪዎችን 2ሺህ 600 ለማድረስ እየሠራ ይገኛል።

    በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል (ደብብሕክ)፣ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና ከተማ በሆነችው ጂንካ የሚገኘው ጂንካ ዩኒቨርሲቲ በ2010 ዓ.ም. በትምህርት ሚኒስቴር ስር ከተከፈቱት 11 አዳዲስ የሕዝብ ዩኒቨርሲቲዎች (public universities) አንዱ ነው።

    ምንጭ፦ ዋልታ

    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    ጂንካ ዩኒቨርሲቲ

     

    Semonegna
    Keymaster

    ወደ 300 የሚጠጉ አባላት ያሉት ‹ንጋት› የዘር ብዜትና መሰረታዊ ሁለገብ የገበሬዎች ሕብረት ሥራ ማኅበር በ14 ሺህ ብር ካፒታል ሥራውን ጀምሮ የተለያየ ዓይነት ዝርያ ያላቸውን ዘሮች በማባዛት ሌሎች አባል ያልሆኑ አርሶአደሮች የምርጥ ዘር ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከፍተኛ አስተዋፅዖ እያበረከተ ይገኛል። በአሁኑ ሰዓት 700 ሺህ ብር ካፒታል የደረሰው ማኅበሩ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በምርምር የታገዘ ድጋፍ ይደረግለታል።

    ጎንደር (ጎዩ) – ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ጊዜያት በተለያዩ ዘርፎች የማህበረሰብ አገልግሎትን እየሰጠ የሚገኝ አንጋፋ የትምህርትና የምርምር ተቋም ነው።

    ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር እና ምርምር ሥራ ባሻገር፥ የተለያዩ የህክምና አገልግሎቶችን በመስጠጥ፣ የጤና በለሙያዎችን በማሰልጠን፣ ልዩ ልዩ የቁሳቁስ ድጋፍ በመስጠት፣ ለኅብረተሰቡ የስልጠና እና የልምድ ልውውጥ ዕድሎችን በማመቻቸት መጠነ-ሰፊ የማኅበረሰብ አገልግሎቶችን እያከናወነ ይገኛል።

    በጎንደር ዩኒቨርሲቲ በግብርናና ገጠር ትራንስፎርሜሽን ኮሌጅ የገጠር ልማትና ሰብል ስርፀት ትምህርት ክፍል ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ ድጋፍና ክትትል እያደረገላቸው ከሚገኙት ማኅበራት ‹ንጋት› የዘር ብዜትና መሰረታዊ ሁለገብ የገበሬዎች ሕብረት ሥራ ማኅበር አንዱ ነው። ማኅበሩ በማዕከላዊ ጎንደር ወገራ ወረዳ ደብር ቀበሌ የሚገኝ ሲሆን በ2002 ዓ.ም በኦክስፋምና በአመልድ ሁለት ድርጅቶች ትብብር የተመሠረተ መሆኑን ከተለያዩ ማኅበሩ ከመዘገባቸው ማስረጃዎች (ዶክዩሜንቶች) ማረጋገጥ ተችሏል።

    ወደ 300 የሚጠጉ አባላት ያሉት ‹ንጋት› የዘር ብዜትና መሰረታዊ ሁለገብ የገበሬዎች ሕብረት ሥራ ማኅበር በ14 ሺህ ብር ካፒታል ሥራውን ጀምሮ የተለያየ ዓይነት ዝርያ ያላቸውን ዘሮች በማባዛት ሌሎች አባል ያልሆኑ አርሶአደሮች የምርጥ ዘር ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከፍተኛ አስተዋፅዖ እያበረከተ ይገኛል። በአሁኑ ሰዓት 700 ሺህ ብር ካፒታል የደረሰው ማኅበሩ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በምርምር የታገዘ ድጋፍ እየተደረገለት መሆኑን በአካል ማረጋገጥ ተችሏል።

    በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የተለያዩ ዳይሬክተሮች፣ የሥራ ኃላፊዎችና የጋዜጠኞች አባላት ያሉት ቡድን በወገራ ወረዳ ደብር ቀበሌ ማኅበሩ እያከናወነ ያለውን ተግባር መስከረም 24/2011 ዓ.ም ጎብኝቷል። በጉብኝቱ በተለያዩ የአርሶ አደሮች ማሳ ላይ በመዘዋወር በቢራ ገብስ ላይ እየተካሄደ ያለውን የዘር ማባዛት ሂደት ተመልክቷል። በተጨማሪም ማኅበሩ ያካሄደውን ዓመታዊ ርፖርትና ግምገማ ቡድኑ አዳምጧል።

    በመጨረሻም በጎንደር ዩኒቨርሲቲ በግብርናና ገጠር ትራንስፎርሜሽን ኮሌጅ የገጠር ልማትና ሰብል ስርፀት ትምህርት ክፍል መምህርና የተቀናጀ የዘር ዘርፍ ልማት ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ በየነ ደርሶና የዕፀዋት ሳይንስ ትምህርት ክፍል መምህርና የፕሮግራሙ አባል አቶ ዳንኤል ታደሰ በቀረበው ሪፖርት የማጠቃለያ አስተያየት ሰጥተው ፕሮግራሙ ተጠናቋል።

    ዘገባ፡-በላይ መስፍን፣ የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት፣ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ (ጎዩ)

    ጎንደር ዩኒቨርሲቲ

    Semonegna
    Keymaster

    ወደ 300 የሚጠጉ አባላት ያሉት ‹ንጋት› የዘር ብዜትና መሰረታዊ ሁለገብ የገበሬዎች ሕብረት ሥራ ማኅበር በ14 ሺህ ብር ካፒታል ሥራውን ጀምሮ የተለያየ ዓይነት ዝርያ ያላቸውን ዘሮች በማባዛት ሌሎች አባል ያልሆኑ አርሶአደሮች የምርጥ ዘር ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከፍተኛ አስተዋፅዖ እያበረከተ ይገኛል። በአሁኑ ሰዓት 700 ሺህ ብር ካፒታል የደረሰው ማኅበሩ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በምርምር የታገዘ ድጋፍ ይደረግለታል።

    ጎንደር (ጎዩ) – ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ጊዜያት በተለያዩ ዘርፎች የማህበረሰብ አገልግሎትን እየሰጠ የሚገኝ አንጋፋ የትምህርትና የምርምር ተቋም ነው።

    ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር እና ምርምር ሥራ ባሻገር፥ የተለያዩ የህክምና አገልግሎቶችን በመስጠጥ፣ የጤና በለሙያዎችን በማሰልጠን፣ ልዩ ልዩ የቁሳቁስ ድጋፍ በመስጠት፣ ለኅብረተሰቡ የስልጠና እና የልምድ ልውውጥ ዕድሎችን በማመቻቸት መጠነ-ሰፊ የማኅበረሰብ አገልግሎቶችን እያከናወነ ይገኛል።

    በጎንደር ዩኒቨርሲቲ በግብርናና ገጠር ትራንስፎርሜሽን ኮሌጅ የገጠር ልማትና ሰብል ስርፀት ትምህርት ክፍል ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ ድጋፍና ክትትል እያደረገላቸው ከሚገኙት ማኅበራት ‹ንጋት› የዘር ብዜትና መሰረታዊ ሁለገብ የገበሬዎች ሕብረት ሥራ ማኅበር አንዱ ነው። ማኅበሩ በማዕከላዊ ጎንደር ወገራ ወረዳ ደብር ቀበሌ የሚገኝ ሲሆን በ2002 ዓ.ም በኦክስፋምና በአመልድ ሁለት ድርጅቶች ትብብር የተመሠረተ መሆኑን ከተለያዩ ማኅበሩ ከመዘገባቸው ማስረጃዎች (ዶክዩሜንቶች) ማረጋገጥ ተችሏል።

    ወደ 300 የሚጠጉ አባላት ያሉት ‹ንጋት› የዘር ብዜትና መሰረታዊ ሁለገብ የገበሬዎች ሕብረት ሥራ ማኅበር በ14 ሺህ ብር ካፒታል ሥራውን ጀምሮ የተለያየ ዓይነት ዝርያ ያላቸውን ዘሮች በማባዛት ሌሎች አባል ያልሆኑ አርሶአደሮች የምርጥ ዘር ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከፍተኛ አስተዋፅዖ እያበረከተ ይገኛል። በአሁኑ ሰዓት 700 ሺህ ብር ካፒታል የደረሰው ማኅበሩ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በምርምር የታገዘ ድጋፍ እየተደረገለት መሆኑን በአካል ማረጋገጥ ተችሏል።

    በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የተለያዩ ዳይሬክተሮች፣ የሥራ ኃላፊዎችና የጋዜጠኞች አባላት ያሉት ቡድን በወገራ ወረዳ ደብር ቀበሌ ማኅበሩ እያከናወነ ያለውን ተግባር መስከረም 24/2011 ዓ.ም ጎብኝቷል። በጉብኝቱ በተለያዩ የአርሶ አደሮች ማሳ ላይ በመዘዋወር በቢራ ገብስ ላይ እየተካሄደ ያለውን የዘር ማባዛት ሂደት ተመልክቷል። በተጨማሪም ማኅበሩ ያካሄደውን ዓመታዊ ርፖርትና ግምገማ ቡድኑ አዳምጧል።

    በመጨረሻም በጎንደር ዩኒቨርሲቲ በግብርናና ገጠር ትራንስፎርሜሽን ኮሌጅ የገጠር ልማትና ሰብል ስርፀት ትምህርት ክፍል መምህርና የተቀናጀ የዘር ዘርፍ ልማት ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ በየነ ደርሶና የዕፀዋት ሳይንስ ትምህርት ክፍል መምህርና የፕሮግራሙ አባል አቶ ዳንኤል ታደሰ በቀረበው ሪፖርት የማጠቃለያ አስተያየት ሰጥተው ፕሮግራሙ ተጠናቋል።

    ዘገባ፡-በላይ መስፍን፣ የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት፣ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ (ጎዩ)

    ጎንደር ዩኒቨርሲቲ

Viewing 5 results - 31 through 35 (of 35 total)