Search Results for 'ዳንኤል ክብረት'

Home Forums Search Search Results for 'ዳንኤል ክብረት'

Viewing 5 results - 1 through 5 (of 5 total)
  • Author
    Search Results
  • Anonymous
    Inactive

    8ኛው የበጎ ሰው ሽልማት ስምንት ግለሰቦችንና ተቋማትን የዓመቱ በጎ በማለት ሸልሟቸዋል

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – በልዩ ሁኔታና መስፈርት ጳጉሜን 1 ቀን 2012 ዓ.ም በኢንተርኮንቲነንታል አዲስ ሆቴል የተከናወነው 8ኛው የበጎ ሰው ሽልማት ስምንት የተለያዩ ግለሰቦችን፣ ድርጅቶችንና ማኅበራትን በጎ ተሸላሚዎች በማለት ዕውቅና ተሰጥቷቸዋል።

    የዘንድሮውን የስምንተኛውን ዙር የበጎ ሰው ሽልማት እንደቀደሙት ዓመታት ሁሉ በተለመዱት በአስሩ ዘርፎች እና በተለየ ድምቀት እንዳይካሄድ በዓለምአቀፍ ደረጃ የተከሰተው የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ (ኮቪድ-19) የሽልማቱ አዘጋጆችን እንደገታቸው ጋዜጠኛና የሥራ አመራ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ወ/ሮ ሕሊና አዘዘ በመግቢያ ንግግሯ ላይ ገልጻለች።

    የዚህን ዓመት ሽልማት ለማከናወን ከየካቲት 1 እስከ መጋቢት 15 ቀን 2012 ዓ.ም. ባለው ጊዜ ከ200 በላይ የዕጩዎች ጥቆማ ከሕዝብ መቀበላቸውን እና የሽልማት ድርጅቱ የሥራ አመራር ቦርድ የዕጩዎቹን ታሪካቸውንና አብርክቷቸውን በማጥናት ላይ እያለ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ በመከሰቱ ምክንያት የተሟላ ዝግጅት ሊያደርጉ አለመቻላቸውን ጋዜጠኛ ሕሊና ጠቅሳለች።

    የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ (ኢ.ፌ.ዲ.ሪ) ፕሬዝደንት ክብርት ወ/ሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ ካርዲናል ብርሃነኢየሱስ፣ እንዲሁም የበጎ ሰው ሽልማት የበጎ አድራጎት ድርጅት መሥራችና የቦርድ ሰብሳቢ እንዲሁም የአግዮስ መጻሕፍት ሥራ አስኪያጅ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት በሽልማት ሥነ ሥርዓቱ ላይ በክብር እንግድነት ተገኘተዋል።

    የ8ኛው የበጎ ሰው ሽልማት ተሸላሚዎች የሚከተሉት ናቸው፡-

    1. አቶ ካሊድ ናስር

    የመጀመሪያ ልዩ ተሸላሚ ባለፉት አምስት ወራት በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት የገዛ መኖሪያ ግቢያቸውን ሳይቀር በመስጠት፣ መጠለያ የሌላቸውን (የጎዳና ተዳዳሪዎችን) በመደገፍ የበጎ አድራጎት ሥራ የሠሩት አቶ ካሊድ ናስር ናቸው።

    1. አቶ ኪሮስ አስፋው

    አቶ ኪሮስ አስፋው ላለፉት ዘጠኝ ዓመታት ያለማቋረጥ መቶ ጊዜ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ቦንድ የገዙ እና በደም መፍሰስ የሚሞቱ እናቶችን ለመታደግ ለ21 ጊዜ ደም የለገሱ ግለሰብ ናቸው።

    1. አቶ ብንያም ከበደ

    የኢትዮጵያ ልጆች ቴሌቪዥን መሥራች ጋዜጠኛ ብንያም ከበደ የ8ኛው የበጎ ሰው ሽልማት 3ኛ ልዩ ተሸላሚ ሆኗል። ጋዜጠኛ ብንያም ከበደ በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ወቅት ልጆች በየቤታቸው ሲሆኑ የሚመለከቱት የሚመጥናቸውና በተለያየ ቋንቋ መሰናዶዎች የሚቀርብበት የኢትዮጵያ ልጆች ቴሌቭዥንን ከመክፈት ጀምሮ ያደረጉት አስተዋጽዖም የበጎ ሰው ሽልማት ተሸላሚ አድርጓቸዋል።

    1. ጋዜጠኛ መሀመድ አል-አሩሲ (محمد العروسي / Mohammed Al-Arousi)

    በአረብኛ ቋንቋ የኢትዮጵያን ሀሳብና እውነት (በተለይም በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ዙሪያ) በዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ሲያስረዳና ሲከራከር የቆየው አቶ መሐመድ አል-አሩሲ (محمد العروسي / Mohammed Al-Arousi) የዘንድሮ የበጎ ሰው ልዩ ተሸላሚ ሆኗል። ከኢትዮጵያዊ ቤተሰቦች በሳዑዲ አረቢያ የተወለደው መሐመድ አል አሩሲ፥ የሕዳሴ ግድብን በሚመለከት ስለኢትዮጵያ በተለያዩ ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኃን ሙግት በማድረግ ይታወቃል።

    1. ዶ/ር ያዕቆብ አርሳኖ

    በሕዳሴ ግድብ ላይ እንዲሁም በአባይ ወንዝ ላይ ኢትዮጵያ ባላት የልማት ተጠቃሚነት ዙሪያ የተለያዩ ጥናቶችን ያደረጉትና በተለያዩ ሚዲያዎች ላይ ስለሕዳሴ ግድብ ተግተው በመሞገት የሚታወቁት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ ዶ/ር ያዕቆብ አርሳኖ የዘንድሮው የበጎ ሰው ተሸላሚ ሆነዋል።

    1. ኢትዮ ቴሌኮም

    ኢትዮ-ቴሌኮም በዓመቱ ውስጥ በተለይ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል መልዕክት በማስተላለፍ፣ ማዕድ በማጋራት፣ እንዲሁም የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል በሠራቸው የበጎ አድራጎት ሥራዎቹ የ2012 ዓ.ም የበጎ ሰው ሽልማት ተሸላሚ ሆኗል። ድርጅቱን በመወከል የተገኙት ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ወ/ት ፍሬሕይወት ታምሩ ሽልማቱን ተረክበዋል።

    1. የሕክምና ባለሙያዎችና ድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች

    የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በሀገራችን ከተከሰተ ጀምሮ ራሳቸውን አደጋ ላይ ጥለው የዜጎችን ደኅንነት ለመጠበቅ ከፊት የተሰለፉ የጤና ባለሞያዎችና ድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች የ2012 ዓ.ም የዓመቱ የበጎ ሰው ልዩ ተሸላሚ ሆነዋል። የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ በመድረኩ የጤና ባለሞያዎችንና የድጋፍ ሰጪ ሠራተኞችን በመወከልም ሽልማቱን ተቀብለዋል።

    1. የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሠራተኞች በሙሉ

    የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ጸጥታውን የሚቆጣጠሩ የመከላከያ ሠራዊት እና የፌዴራል ፓሊስ አባላት፣ እንዲሁም የሕዳሴው ግድብ የመሠረት ድንጋይ ከተጣለበት ከመጋቢት 24 ቀን 2004 ዓ.ም ጀምሮ በጉባ በሥራ ላይ የሚገኙ የግድቡ ሠራተኞች የ2012 ዓ.ም የበጎ ሰው ሽልማት ልዩ ተሸላሚ ሆነዋል። በጉባ የሚገኙ ሠራተኞችን ወክለው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሥራ አስኪያጅ ኢ/ር ክፍሌ ሆሮ ሽልማቱን ተረክበዋል።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    8ኛው የበጎ ሰው ሽልማት

    Anonymous
    Inactive

    ስምንተኛው የበጎ ሰው ሽልማት በልዩ ሁኔታ እንደሚካሄድ ተገለጸ

    አዲስ አበባ (አዲስ ዘመን) – ስምንተኛው የበጎ ሰው ሽልማት ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ እና ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መከላከል ሥራ ጋር ለሕዝብ አርዓያነት ያለው ተግባር ላይ ያተኮረ ሆኖ በልዩ ሁኔታ እንደሚካሄድ ተገለጸ።

    ዘንድሮ ለስምንተኛ ጊዜ የሚካሄደውን የበጎ ሰው ሽልማት መርሃ ግብር አስመልክቶ ነሐሴ 12 ቀን 2012 ዓ.ም. ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡት የበጎ ሰው የሽልማት በጎ አድራጎት ድርጅት የቦርድ ሰብሳቢ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት፥ ወቅታዊ ሁኔታውን ታሳቢ ባደረገ መልኩ የዘንድሮው የበጎ ሰው ሽልማት በዘርፎች ላይ ሳይሆን በሁለት ወቅታዊ እና ሀገራዊ አንኳር ጉዳዮች ላይ ልዩ አስተዋፅኦ ላበረከቱ ኢትዮጵያውያን የሚሰጥ ይሆናል ብለዋል።

    እንደ እርሳቸው ማብራሪያ፥ በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ (ኮቪድ-19) ምክንያት በዓለም ላይም ሆነ በሀገሪቱ ባለው ወቅታዊ ሁኔታ የተነሳ ሽልማቱን በተለመደው መንገድ ለመስጠት አይቻልም፤ በመሆኑም የዘንድሮውን መርሃ ግብር በተለየ መንገድ ለማከናወን ተወስኗል፤ በበሽታው ምክንያት ከሰዎች ንክኪና ግንኙነት ነጻ በሆነ መንገድ ማካሄድ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ሽልማቱ ከዚህ ቀደም ከተለመደው በተለየ ሁኔታ ይካሄዳል።

    የበጎ ሰው ሽልማት በጎ አድራጎት ድርጅት የቦርድ ጸሐፊ አቶ ቀለመወርቅ ሚዴቅሳ በበኩላቸው፥ ድርጅቱ በየዓመቱ በአስር ዘርፎች በየሙያቸው ለሀገራቸው የላቀ ተግባር ላከናወኑ ኢትዮጵያውያን በሕዝብ ፊት ዕውቅና ሲሰጥ መቆየቱን አስታውሰው፥ “በጎ ሰዎችን በማክበርና ዕውቅና በመስጠት ሌሎች በጎ ሰዎችን እናፍራ” በሚል መሪ ሃሳብ ባለፉት ሰባት ዓመታት ሽልማቱ ሲከናወን መቆየቱን ጠቁመዋል።

    የዘንድሮውን ሽልማት ለማከናወንም ከየካቲት 1 እስከ መጋቢት 15 ቀን 2012 ዓ.ም. ከሁለት መቶ በላይ ዕጩዎችን በመቀበል ታሪካቸውንና አበርክቷቸውን የማጥናት ሥራ መሰራቱንም አመልክተው፤ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ በዓለም አቀፍ ደረጃ በመቀስቀሱና በሀገሪቱም ከጊዜ ወደ ጊዜ ስርጭቱ እየተባባሰ በመምጣቱ በዕቅዱ መሠረት እንደ ልብ ተንቀሳቅሶ መሥራት ባለመቻሉ የዘንድሮው ሽልማት በልዩ ተሸላሚ ሥነ ሥርዓት እንዲካሄድ በቦርዱ አባላት በተወሰነው መሠረት የሚከናወን መሆኑን አቶ ቀለመወርቅ አስታውቀዋል።

    አቶ ቀለመወርቅ ሁለት ወቅታዊና አንኳር ሀገራዊ ጉዳዮች መመረጣቸውንና ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ እና በኮሮና ወረርሽኝ መከላከል ሥራ ለሕዝብ አርዓያነት ያለውና የላቀ ተግባር ላከናወኑ ግለሰቦችና ተቋማት በልዩ ሁኔታ የዘንድሮው በጎ ሰው ሽልማት እንደሚበረከትላቸው ተናግረዋል።

    የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ እንዲሳካ፣ ለመጀመሪያው ዙር ውሃ ሙሌት እንዲበቃና በሕዝቡ ዘንድ ብሔራዊ ኩራት እንዲፈጠር ምክንያት የሆኑ በጎ ሰዎችና ድርጅቶች የዘንድሮው የበጎ ሰው ተሸላሚ ይሆናሉ ብለዋል።

    የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በሀገሪቱ ከተከሰተበት ጊዜ ጀምሮ በሕዝብ ላይ የሚደርሰውን የጤና ችግር ለመከላከል፣ በበሽታው መስፋፋት የተነሳም በሀገሪቱ ምጣኔ ሃብት ላይ ሊደርስ የሚችለውን ጉዳት ለመቀነስ እና በተለያዩ መንገዶች ለተጎጂ ወገኖች ድጋፍ በማድረግ የተጉና አርዓያነት ያለው ተግባር የፈጸሙ ኢትዮጵያውያን የሚመሰገኑበት እንደሚሆንም አክለዋል።

    በሁለቱ ጉዳዮች ዙሪያ ለሀገራቸው የላቀ አስተዋፅኦ ያበረከቱ ስምንት ኢትዮጵውያን ግለሰቦችና ድርጅቶች የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁንና የጤና ተቋማት ደንብን ባከበረ መንገድ በተመጠኑ ታዳሚያንና በቀጥታ የሚዲያ ስርጭት በመታገዝ ጳጉሜ 1 ቀን 2012 ዓ.ም. በአዲስ አበባ በሚካሄድ መርሃ ግብር የዘንድሮው የበጎ ሰው ሽልማት የሚከናወን ይሆናል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት

    ስምንተኛው የበጎ ሰው ሽልማት

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ዘንድሮ ለሰባተኛ የተለያዩ ኢትዮጵያውያንን የሸለመው የ2011 ዓ.ም. የበጎ ሰው ሽልማት ሥነ ሥርዓት በኢንተር ኮንቲኔንታል ሆቴል የመሰብሰቢያ አዳራሽ ውስጥ (ካዛንችስ፣ አዲስ አበባ) ተካሂዷል።

    በሽልማት ሥነ ሥርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ (ኢፌዴሪ) ፕሬዝደንት ሳህለወርቅ ዘውዴ እና የኢፌዴሪ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር አሚር አማንን ጨምሮ የተለያዩ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎችና ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።

    ለዘንድሮው የበጎ ሰው ሽልማት በዘጠኝ ዘርፎች 291 ሰዎች ከሕዝብ ዘንድ ተጠቁመው የነበረ ሲሆን፤ ከእነዚህም ውስጥ 27ቱ ተመርጠው ለመጨረሻ ዕጩነት (በዘጠኝ ዘርፎች፣ በእያንዳንዱ ዘርፍ ሦስት ሦስት ዕጩዎች) ቀርበው ኢትዮጵያውያን አሸናፊዎችን እንዲመርጡ ተደርጎ ነበር

    ነሐሴ 26 ቀን 2011 ዓ.ም. በእያንዳንዱ ዘርፍ ከቀረቡት ዕጩዎች ውስጥ የመጨረሻ ተሸላሚዎች ይፋ ተደርገዋል። በዚህም መሠረት አሸናፊዎቹ የሚከተሉት ናቸው።

    በመምህርነት ዘርፍ

    • ወ/ሮ ህይወት ወልደመስቀል

    በሳይንስ (ህክምና፣ ቴክኖሎጂ፣ ፊዚክስ፣ ምህንድስና፣ ኬሚስትሪ፣ አርክቴክቸር፣ ወዘተ)

    • ፕሮፌሰር ሰብስቤ ደምሴ (አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ በ አትክልት ምርምር ፕሮፌሰር፣ የጎለሌ ዕፅዋት ማዕከል የበላይ ኃላፊ፣ በሀገረ እንግሊዝ የተከበረው KEW International ሜዳል ተሸላሚ)

    በኪነ ጥበብ፣ ሥነ ጥበብ እና በፎቶ ግራፍ ዘርፍ

    • አቶ በዛብህ አብተው (ኢትዮጵያ ውስጥ የመጀመሪያው የስፖርት ፎቶግራፍ አንሺ)

    በበጎ አድራጎት (እርዳታ እና ሰብዓዊ አገልግሎቶች)

    • አቶ አብድላዚዝ አህመድ

    በንግድና ሥራ ፈጠራ ዘርፍ

    • አቶ ነጋ ቦንገር (የነጋ ቦንገር ሆቴል፣ እንዲሁም አዲስ አበባ ውስጥ የተለያዩ የንግድ ተቋማት ምሥራች እና ባለቤት)

    በመንግሥታዊ የሥራ ተቋማት ኃላፊነት

    • አቶ ግርማ ወንዳፍራሽ

    በቅርስና ባህል ዘርፍ

    • አቶ አብዱልፈታህ አብደላ (የበርካታ ብሔር ብሔረሰቦችን የባህላዊ ዳኝነትና የፍትህ ሥርዓቶችን በመጻፍ የሚታወቁ)

    በሚዲያና ጋዜጠኝነት

    • አቶ አማረ አረጋዊ (ሚዲያና ኮምዩኒኬሽንስ ሴንተር በስሩ የሚታተመው ሪፖርተር ኢትዮጵያ (የአማርኛ እና የእንግሊዝኛ) ጋዜጣ መሥራች)

    በኢትዮጵያ እድገት አስተዋፅኦ ያበረከቱ ዲያስፖራዎች

    • አቶ ኦባንግ ሜቶ (ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) መሥራች እና ሊቀ-መንበር)

    የሰባተኛው የበጎ ሰው ሽልማት ልዩ የክብር ተሸላሚዎች

    • የጋሞ ሽማግሌዎች (በቡራዩ የተከሰተውን ግድያ በመቃወም በአርባ ምንጫ የተቃውሞ ሠልፍ ላይ፣ በቁጣ ንብረት ለማውደም የቃጡ ወጣቶች እንደነበሩ የሚታወስ ሲሆን፣ አንደ አካባቢው ባሕል ሣር ይዘው በአካላቸው ቆመው ንብረቱን ከጥፋት የተከላከሉት የጋሞ ሀገር ሽማግሌዎች ነበሩ።)

    በሽልማት ሥነ ሥርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት ፕሬዝደንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የ2011 ዓ.ም. የበጎ ሰው ሽልማት ተሸላሚዎችን እንኳን ደስ አላቸሁ ብለዋል። ሀገር በትውልድ ቅብብሎሽ የምትገነባ መሆኑን የገለጹት ፕሬዝደንቷ፥ የበጎ ሰው ሽልማት ተሸላሚዎች ለነገው ትውልድ ተረካቢዎች አርዓያ የሚሆን ሥራ በመሥራታቸው ሊደነቁ ይገባል በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

    በ2005 ዓ.ም. በዲያቆን ዳንኤል ክብረት የተቋቋመው የበጎ ሰው ሽልማት ዋና ዓላማ ለኢትዮጵያ እና ለኢትዮጵይውያን በጎ ሥራን የሠሩ እና ለሌሎች አርዓያ ሊሆኑ የሚችሉ ግለሰቦችን ማበረታታት እና ዕውቅና መስጠት ነው።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    The 7th edition of Bego Sew Award የበጎ ሰው ሽልማት


    Anonymous
    Inactive

    ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን በኪነ ህንፃ ሲያስመርቅ ዘንድሮ ለሦስተኛ ጊዜ ሲሆን፥ ዘንድሮ የተመረቁት 18 ወንዶችና 16 ሴቶች በአጠቃላይ 34 የኪነ ህንፃ ሙያተኞች መሆናቸውን በምረቃ ሥነ ስርዓቱ ላይ ተገልጿል።

    ጎንደር (ሰሞነኛ)–የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ለአምስት ዓመት ተኩል በኪነ ህንፃ ትምህርት መስክ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ቅዳሜ፥ የካቲት 9 ቀን 2011 ዓ.ም. በባችለር ዲግሪ (BSc in Architecture) አስመረቀ።

    በምረቃ ሥነ ስርአቱ የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት ያስተላለፉት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ደሳለኝ መንገሻ፥ ዩኒቨርሲቲው በኪነ ህንፃ የትምህርት ዘርፍ ዘንድሮ ተማሪዎችን ሲያስመርቅ ለሦስተኛ ጊዜ መሆኑን ገልፀዋል።

    ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በአሁኑ ወቅት በቴክኖሎጂ የትምህርት መስኮች ከ5 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ተቀብሎ እያሰለጠነ እንደሚገኝ የተናገሩት ፕሬዚዳንቱ፥ ቅዳሜ ዕለት የተመረቁት 18 ወንዶችና 16 ሴቶች በአጠቃላይ 34 የኪነ ህንፃ ሙያተኞችም በሀገራችን የሚታየውን የህንፃ ጥበብ ችግር ለማስተካከልም ሆነ በሙያው የሚታየውን የሰለጠነ የሰው ኃይል ለመቅረፍ እንዲተጉ አሳስበዋል።

    የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለፓን አፍሪካ ዩኒቨርሲቲ ማሰገንቢያ የሚውል አስር ሚሊዮን ብር ለገሰ

    የጎንደር ከተማ ም/ከንቲባ ዶ/ር ሙሉቀን አዳነ በምርቃቱ ሥነ ስርዓት ላይ በክብር እንግድነት ተገኝተው የተመራቂዎቹ የምርቃት ዕለት የልጅነት ዘመን አብቅቶ ለሀገር ብቁ የሆነ የኪነ ህንፃ ባለሙያ የሚሆኑበት ዕለት እንደሆነ አስገንዝበዋል። ከዚህ በኋላም ተመራቂዎቹ ሀገሪቱ ለረዥም ዓመታት የምትጠራበትና የምትታወስበትን የኪነ ህንፃ ጥበብ እንደሚያበረክቱ እምነታቸውን ገልፀዋል።

    ተመራቂዎቹም በሙያቸው ሀገራቸውን ለማገልገል የገቡትን ቃል ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

    ከዩኒቨርሲቲው ዜና ጋር በተያያዘ የዩኒቨርሲቲው ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የማኔጅመንትና የህዝብ አስተዳደር ት/ቤት “በወቅታዊ የፖለቲካ ለውጥ ዘላቂነት ላይ የምሁራን ሚና” (‘The Role of Academicians in Sustaining the Current Political Reforms’) በሚል ርዕስ ዙሪያ ከካቲት 6 እስከ 7 ቀን 2011 ዓ.ም. ኮንፈረንስ አካሂዷል።

    በዕለቱ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ደሳለኝ መንገሻ፣ በጠቅላይ ሚኒስቴር ፅ/ቤት የመሰረተ ልማትና የከተማ ልማት አማካሪ ዶ/ር አምባቸው መኮንን፣ የጎንደር ከተማ ም/ከንቲባ ዶ/ር ሙሉቀን አዳነ፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ፖለቲከኛ ፕ/ር መረራ ጉዲና፣ ከአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ አቶ ክርስቲያን ታደለ፣ ደራሲና የታሪክ ተመራማሪው ዲያቆን ዳንኤል ክብረት፣ የጎንደር ከተማ የልማትና የሰላም ሸንጎ አባላት የዩኒቨርሲቲው ም/ፕሬዚዳንቶች፣ ዲኖች፣ መምህራን፣ ተማሪዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– በ2006 ዓ.ም. በሰባት የየመገናኛ ብዙሃን (ሚዲያ) እና ኪነ ጥበብ ባለሙያዎች የተቋቋመው ጉዞ ዓድዋ፥ አንድ ሺሕ አስር ኪሎሜትሮችን የሚሸፍን፣ ከኢትዮጵያ ዋና ከተማ አዲስ አበባ ተነስቶ መዳረሻውን የዓድዋ ድል አምባ ተራሮች ጫፍ ላይ የሚያደርግ ረዥም የእግር ጉዞ ነው። ላለፉት ስድስት ዓመታት ከጥር ወር ጀምሮ የዓድዋ ድል በዓል እስከ ሚከበርበት የካቲት 23 ቀን ድረስ ከስድስት ሳምንታት ላላነሰ በየዓመቱ ሳይቋረጥ የቆየው ጉዞ ዓድዋ፥ ዘንድሮ የኢትዮጵያዊነቱ ስሜት እጅግ ጎልቶ በጉዞው ላይ የሚሳተፉት ቁጥርም ጨምሯል። በዘንድሮው ጊዞ ዓድዋ 44 ተጋዦች ከአዲስ አበባ እና 4 ተጓዦች ከሐረር በአጠቃላይ 48 ተጓዦች ጥር 7 ቀን 2011 ዓ.ም. ቀን ከአዲስ አበባ ተነስተዋል።

    የመላው አፍሪቃውያን ድል እስከመባል የደረሰው ታላቁ የዓድዋ ድል፥ የግዝፈቱን ያህል ክብር እና መታወሻ ሥነሥርዐት ሳይኖረው እየተከታተለ ከመጣው ትውልድ ጋር የበዓሉ አከባበር ዐውድ እየወረደ ጭራሽ እየተዘነጋ እና እየደበዘዘ መሔድ ያሳሰባቸው የጉዞ ዓድዋ መሥራቾች ትውልዱ ትኩረት ሰጥቶ የድሉን መንፈስ እንዲጋራ ለማድረግ ይህንን የጉዞ ሐሳብ አመንጭተዋል።

    ◌ የጉዞ ዓድዋ ተጓዦችና የኢትዮጵያዊያን አስተያየት

    በዚህም የተነሣ ጉዞ ዓድዋ ባለፉት ስድስት ዓመታት ብቻ ከታለመው ዓላማ አንጻር ከፍተኛ የሆነ አመርቂ ውጤት በማስመዝገብ የዓድዋ ድል በዓል ቀድሞ ከነበረበት አከባበር የላቀ ተሳትፎ ያለው የድል በዓል እንዲሆን አስተዋጽዖ ለማድረግ ተችሏል።

    ጉዞውን ከማካሔድ በተጓዳኝ በየመንገዱ ተንቀሳቃሽ የመጻሕፍት ንባብ መሰናዶ በማካሔድ በየዓመቱ የሚጓዙ አባላትን በዓድዋ ጦርነት እና ድል ዙሪያ በቂ የሆነ ግንዛቤ እና ዕውቀት የማጋራት ዝግጅቶችን ሲያካሂድ ቆይቷል። ከአንድ ወር በላይ በተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን ሰፊ ሽፋን የሚሰጠው የጉዞው የዕለት ተእለት ውሎ፣ በዓሉ ከመድረሱ አስቀድሞ በበርካታው ሕዝባችን ላይ የካቲት 23 ዕለትን በጉጉት የመጠበቅ ስሜት እንዲፈጠር አድርጓል።

    ◌ የዓድዋ ድል በዓል በጎሰኞች ዓይን የዲያቆን ዳንኤል ክብረት መጣጥፍ

    ከዚህ ቀደም የድል በዓሉ በብቸኝነት ከሚከበርባቸው የአዲስ አበባ እና የዓድዋ ከተሞች በተጨማሪ ከ28 በላይየሚሆኑ የክልል ከተሞች እና በርካታ ሕዝብ የሚኖርባቸው የገጠር ወረዳዎች ተጓዥ ቡድኑ በየደረሰበት በሚኖሩ ደማቅ አቀባበሎች ላይ በሚሰጡ የግንዛቤ መስጫ መልዕክቶች ስለ ዓድዋ ድል ታሪክ ግንዛቤ በመሰጠቱ የበዓሉአከባበር ከፍተኛ ለውጥ በማምጣት ላይ ይገኛል። የጉዞ ዓድዋ ትሩፋቶች፦

    • በዓድዋ ከተማ ውስጥ በአምስት ዓመት አንድ ጊዜ ብቻ የነበረው የዓድዋ ድል በዓል አከባበር ሥነ ሥርዐትበየዓመቱ እንዲካሔድ አስችሏል።
    • የበዓሉ አከባበር በፌደራል መንግሥት ደረጃ እንዲከበር ልዩ ትኩረት እንዲሰጠው ከፍተኛ አስተዋጽዖ አድርጓል።
    • ከ120 ዓመታት በፊት መቀሌ ከተማ በሚገኘው የእንዳየሱስን ምሽግ ለማስለቀቅ ከጣሊያን ጦር ጋር ሲዋጉ ሕይወታቸው ያለፉ ጀግና ኢትዮጵያውያን አጽም የትም ተበታትኖ በመቅረቱ፥ ጉዞ ዓድዋ በአሁኑ ሰዓት የቦታው አስተዳዳሪ የሆነውን የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ በማንቃት፤ የካቲት 26 ቀን 2008 ዓ. ም አጽማቸውን አሰባስቦ በክብር እንዲያርፍ ተደርጓል። ከዚህም ባሻገር በዓመቱ የካቲት 26 ቀን 2009 ዓ.ም በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ወጪ “የጀግኖች ኢትዮጵያዊያን መታሰቢያ ሙዚየም” የተሰኘ ጣራ አልባ ቤተ መዘክር በእንዳየሱስ ታሪካዊ ምሽግ ላይ ተገንብቶ ለመመረቅ በቅቷል።
    • የዓድዋ ጦርነት መንስዔ የሆነው የዉጫሌ ውል የተፈረመበት “ይስማ ንጉሥ” የተባለው ታሪካዊ ቦታ ተከልሎ ጥበቃ እንዲደረግለት በማድረግ ጉዞ ዓድዋ ቁልፍ ሚና ተጫውቷል። ከዚህም በተጨማሪ ውሉ በተፈረመበት ዕለት ሚያዝያ 25 ቀን በየዓመቱ፤ ምሁራዊ ተዋስዖ የሚደረግባቸው መድረኮች በመፍጠር፣ ላለፉት ስድስት ዓመታት ባበረከተው የላቀ አስተጽዖ የአምባሰል ወረዳ የዓድዋ ድልን ለመዘከርና ቦታውን የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ ያለመቋሚ ቤተ መዘክር በቦታው ላይ እንዲገነባ የሚያስችል የ19 ሚልዮን ብር የበጀት ድጋፍ ከአማራ ክልል መንግሥት እንዲያገኝ ጉዞ ዓድዋ ቁልፍ ሚና ተጫውቷል።
    • ለበርካታ ዓመታት አገልግሎቱ ተዘግቶ የቆየው በዳግማዊ ዐፄ ምኒልክ የትውልድ መንደር “አንጎለላ” የሚገኘው የዳግማዊ ዐፄ ምኒልክ መታሰቢያ ክሊኒክ እንዲከፈት ከፍተኛ ቅስቀሳ በማድረግ፤ በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ድጋፍ ክሊኒኩ ታዳጊ የጤና ጣቢያ ሆኖ በድጋሚ አገልግሎት እንዲሰጥ ጉዞ ዓድዋ አስተዋጽዖ ካደረጉ መካከል ግንባር ቀደሙን ሚና ተጫውቷል።
    • የዓድዋ ጀግና የሆኑት ራስ አሉላ አባ ነጋ የቀብር ቦታ በሆነው የአባ ገሪማ ገዳም ውስጥ ለሁለቱም ጾታዎች ጉብኝት ምቹ በሆነ ቦታ ላይ ሐውልት እንዲቆምላቸው ጉዞ ዓድዋ ባመቻቸው ዕድል በአንድ ባለ ሀብት ሐውልታቸው ተሠርቶ ለምረቃ በቅቷል።
    • በየዓመቱ በሚካሔዱ ጉዞዎች ከዓድዋ ድል ጋር ግንኙነት ያላቸው ቦታዋችን እና ልዩ ታሪካዊ መረጃዎችን በምስል እና በጽሑፍ በመሰብሰብ ለጥናትና ምርምር አስተዋጽዖ ማበርከት የሚችሉ የታሪክ ግብዓቶችን በማደራጀት በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች በተለይም የማኅበራዊ ድረ ገጽን በመጠቀም ቅርሶችን የማስተዋወቅና የመጠበቅ ሥራዎችንበ መሥራት ላይ ይገኛል።

    የጉዞ ዓድዋ ማኅበር የዓድዋ ድል በዓል በኢትዮጵያውያን እንዲሁም በጥቁር አፍሪካውያን ዘንድ የሚገባውን ክብር እንዲያገኝ ላደረገው ጥረት፣ ከላይ ለተጠቀሱት እና በየዓመቱ በሚያደርጋቸው እጅግ አመርቂ ክንዋኔዎች ምክንያት በ2009 ዓም በቅርስና ባሕል ዘርፍ የዓመቱ በጎ ሰው ተሸላሚ ሆኗል።

    ላይ የሚሳተፉ ተጓዦች በጉዞአቸው ላይ የሚያደርጓቸውን የተለያዩ ክንዋኔዎችና የሚዘግቧቸውን ታሪክ ተኮር ዘገባዎች ለመከታተል የማኅበሩን የፌስቦክ ገጽ ይጎብኙ።

    ◌ ዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ እና ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ በደብረ ብርሃን ከተማ ሃውልት ሊቆምላቸው ነው

    ምንጭ፦ በጎ ሰው ሽልማት / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ጉዞ ዓድዋ


Viewing 5 results - 1 through 5 (of 5 total)