ቅኔ ነው ሀገር ― የኦርኬስትራ ቅንብር ልዩ ኅብረ ዝማሬ

Home Forums Semonegna Stories ቅኔ ነው ሀገር ― የኦርኬስትራ ቅንብር ልዩ ኅብረ ዝማሬ

  • This topic has 0 replies, 1 voice, and was last updated 4 years ago by Anonymous.
Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #14494
    Anonymous
    Inactive

    ቅኔ ነው ሀገር ― የሦስት ሙዚቃዊ ዘመናት አንጋፋ እና ወጣት ድምፃውያንን እንዲሁም ታላላቅ የሙዚቃ ሊቃውንትን ያገናኘ ልዩ ኦርኬስትራዊ ኅብረ ዝማሬ!!!

    • ከ1950ዎቹ እና 60ዎቹ አንጋፋ ድምጻውያን መካከል አንዱ የሆነው ጥዑመ ልሳኑ ድምጻዊ ታደለ በቀለ (ከሥራዎቹ በጥቂቱ፦ “አላስቀየምኳትም”፣ “ዉብ ዓይናማ” /ከሒሩት በቀለ ጋር/፣ “ሸንኮርዬ” /ከወይንሸት ሙሉነህ ጋር/)፣
    • ከ1970ዎቹ እና 80ዎቹ የወጣትነት ዘመናቸው እስከ ዛሬ ዝናቸው እንደተጠበቀ እዚህ የደረሱት ድምጻውያኑ ንዋይ ደበበ (ከብዙ ሥራዎቹ በጥቂቱ፦ “የፍቅር ገዳም”፣ “አልዋሽም”፣ “ብትከዳኝ ታዘብኳት”፣ “ማዕበል ነው”፣ “ሸጊት ከሐረር፣ ሸጋው ከሐረር” /ከሀመልማል አባተ ጋር/) እና ጸጋዬ እሸቱ (ከብዙ ሥራዎቹ በጥቂቱ፦ “ሰንደቅ ዓላማ”፣ “ያይኔ አበባ”፣ “አላስገድድሽም”፣ “አንቺ ቅናተኛ”፣ “እናት ወደር የላት”፣ “ለሰርጓ ተጠራሁ”)፣
    • ከ1990ዎቹ አይረሴ አልበሞቹ ጀምሮ እስከ ዛሬ ተወዳጅ የኾነው ድምጻዊ ኃይልዬ ታደሰ (ከብዙ ሥራዎቹ በጥቂቱ፦ “ሁሌ ሁሌ”፣ “እንደአፍሽ ያድርገው”፣ “እሷን ብቻ”፣ “በዘመኔ”፣ “ልትሄድ ነው”፣ “ይሞታል ወይ”)፣
    • የሙዚቃ ልኬት በልዩ አጨዋወት እና ድንቅ ብቃት የታየበት እንዲሁም ብዙዎች ለመስማት የጓጉለት ሠርፀ ፍሬስብሐት (በኢትዮጵያን አይድል [Ethiopian Idol] ውድድር ላይ እጅግ ላቀ ባለ የዳኝነት ሙያው አንቱታን ያተረፈ)፣
    • ከወጣቶቹ፣ ከዘመነኞቹ ከወደፊት የሙዚቃ ተስፋዎቹ ከሚካኤል ለማ ደምሰው፣ ከየማርያም ቸርነት (የሚ)፣ ከማኅሌት ነጋሽ ፣ ከማስተዋል ዕያዩ እና ከይድነቃቸው ገለታ ጋር በአንድነት “ቅኔ ነው ሀገር” የተሰኘ ድንቅ ኅብረ ዝማሬ አቅርበዋል።

    ድርሰት፣ ቀረፃ፣ ቅንብር፣ ፕሮዳክሽን እና ዳይሬክቲንግ በያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት መምህሩ በወጣቱ ድንቅ ሙዚቀኛ በኢዩኤል መንግሥቱ ውብ ሆኖ ተሰናድቷል።

    የሙዚቃው የድምጽ ውኅደት በታላቁ ሙዚቀኛ በአበጋሱ ክብረወርቅ ሺዎታ ተከውኗል።

    በሙዚቃ መሣሪያ ተጫዋችነት፥ ዶ/ር ዕዝራ አባተ፣ ረ/ፕ ኃይሉ ዓለማየሁ፣ የያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት ዳይሬክተር ሰላማዊት አራጋው፣ ታዋቂው ሳክስፎኒስት አክሊሉ ወልደ ዮሐንስ (ጆኒ)፣ ኤፍሬም ውብሸት፣ ዳዊት ፍሬው ኃይሉ፣ ኢዩኤል መንግሥቱ፣ ለታሪክ ጥላሁን ፣ ሚሊዮን አብርሀም፣ ቴዎድሮስ አበራ፣ ዳዊት ቦስኮ እና ሌሎች በርካታ የሙዚቃ መሣሪያ ተጫዋቾች በሥራው ላይ ግሩም አጨዋወት ተሳትፈዋል።

    ሀገር ሰምና ወርቅ ያላት ቅኔ ናት። የቅኔዋን “ወርቅ” የምናገኘው፣ “ሰው በሌለበት ሰው ሆነን ስንገኝ ነው፤” ሰውነት፣ ሀገር መውደድ፣ ሰው ሆኖ መገኘት… የዘመናችን እና የወቅቱ ትልቅ “የመሆን አለመሆን” (to be or not to be) ‘ሐምሌታዊ’ (ሼክስፒሪያን) ጥያቄ ስለመሆኑ ኅብረ ዝማሬው ይነግረናል።

    ይህን ምርጥ የትብብር ውጤት የሆነውን ሙዚቃ ለማድመጥ/ ለመመልከት (ምነው ሸዋ ቲዩብ) እዚህ ጋር ይጫኑ

    ሠርፀ ፍሬስብሐት እንደጻፈው

    ቅኔ ነው ሀገር

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.