በቀድሞ የሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንትና በሌሎች ግለሰቦች ተወስዷል የተባለ 130 ሚሊዮን ብር ታገደ

Home Forums Semonegna Stories በቀድሞ የሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንትና በሌሎች ግለሰቦች ተወስዷል የተባለ 130 ሚሊዮን ብር ታገደ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #7813
    Semonegna
    Keymaster

    ለሶማሌ ክልል በድጎማ ከተመደበ በጀት ላይ ከ130 ሚሊዮን ብር በላይ በቀድሞ የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ አብዲ መሐመድና በሌሎች ግለሰቦች መወሰዱን ጠቅሶ፣ ገንዘቡ እንዳይንቀሳቀስ ፖሊስ አሳገደ፡፡

    የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቡድን በተለያዩ የምርመራ መዝገቦች ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ችሎት ባቀረበው ማመልከቻ፣ የክልሉ ፕሬዚዳንት የነበሩት አቶ አብዲ መሐመድ (አብዲ ኢሌ) እና የክልሉ ልዩ ኃይል ፖሊስ አዛዥ የነበሩት አቶ አብዱራህማን አብዱላሂን ጨምሮ፣ በ11 ሰዎች ለግል ጥቅም ተወስዷል ያለውን በአጠቃላይ 132.2 ሚሊዮን ብር እንዲታገድ ጠይቋል፡፡

    የተሻሻለውን የፀረ ሙስና ልዩ የሥነ ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ አዋጅ ቁጥር 882/2007 አንቀጽ (8) በመተላለፍ የተፈጸመና የተጠቀሰውን ያህል የብር መጠን ያለው ጉዳት፣ በመንግሥት ላይ የደረሰ መሆኑን በማስረዳት ገንዘቡ እንዲታገድ ጠይቋል፡፡ ፍርድ ቤቱም የተጠቀሰው ገንዘብ ተለዋጭ ትዕዛዝ እስከሚሰጥ ድረስ እንዳይንቀሳቀስና ተጠብቆ እንዲቆይ፣ ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክና ሌሎች ባንኮችም ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡

    ማንበብዎን ይቀጥሉ፦ በቀድሞ የሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንትና በሌሎች ግለሰቦች ተወስዷል የተባለ 130 ሚሊዮን ብር ታገደ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.