በተባበረ ሀገራዊ አቅም የእንቦጭ አረምን ከጣና ሐይቅ ላይ ለማስወገድ የሚስችል ዘመቻ ሊጀመር ነው

Home Forums Semonegna Stories በተባበረ ሀገራዊ አቅም የእንቦጭ አረምን ከጣና ሐይቅ ላይ ለማስወገድ የሚስችል ዘመቻ ሊጀመር ነው

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #16280
    Anonymous
    Inactive

    በተባበረ ሀገራዊ አቅም የእንቦጭ አረምን ከጣና ሐይቅ ላይ ለማስወገድ የሚስችል ዘመቻ ሊጀመር ነው
    የውሃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – በተባበረ ሀገራዊ አቅም የእንቦጭ አረምን ከጣና ሐይቅ ላይ ለማስወገድ የሚስችል ዘመቻ ሊጀመር ነው፤ ዘመቻውን አስመልክቶ የኢፌዲሪ የውሃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር መስከረም 29 ቀን 2013 ዓ.ም ውይይት አካሂዷል። በውይይት መድረኩም ላይ የአማራ ክልላዊ መንግሥት አመራሮችን ጨምሮ የዩንቨርሲቲ ምሁራንና ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል።

    በዘመቻው እንቦጭን ከጣና ሐይቅ ላይ ለማስወገድ ሁሉንም ክልሎች፣ የከተማ አስተዳደሮች እና የፌደራል እና የክልል ተቋማት እንዲሁም መንግሥታዊ ያልሆኑ አካላት ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ለማስቻል የተዘጋጀ ዕቅድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

    በውሃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር የተፋሰስ ልማት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር አዳነች ያሬድ የሚደረገውን ዘመቻ ዕቅድ ባቀረቡበት ወቅት፥ እንደገለጹት እንቦጭ በጣና ሐይቅና በአባይ ተፋሰስ የውሃ አካላት ላይ እጅግ በሰፊው ተንሠራፍቶ እንደሚገኝ አሳውቀው፤ እንቦጭ የተንሠራፋበትን ይህንን የውሃ አካል ለማጽዳት ሁሉም ክልሎች፣ የከተማ አስተዳደሮች እና የፌደራል እና የክልል ተቋማት እንዲሁም መንግሥታዊ ያልሆኑ አካላት እንቦጭ የተንሠራፋበትን የሐይቁን አካል በመከፋፈል በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ የሚስወግዱት ይሆናል። አረሙን ከውሃው ላይ ማስወገድ፣ መንቀል፣ በአንድ ቦታ ማከማቸትና ማቃጠል ወይንም መቅበር በዘመቻው የሚሠራበት መፍትሄ ነው።

    የውሃ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ኢነጂነር ስለሺ በቀለ ለአንድ ወር በሚካሄደው በዚህ ዘመቻ ላይ ሁሉም ክልሎች፣ የከተማ አስተዳደሮች፣ ተቋማትና ሁሉም ኢትዮጵያውያን በዘመቻው በንቃት እነዲሳተፍበት ጥሪ አቅርበዋል።

    በተለይ ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸው ተቋማት ለዘመቻው ስኬታማነት ከተለመደው አሠራር ባሻገር ማቀድና ስራውን መፈጸም ይጠበቅብናል ብለዋል። ከክልል እስከ ቀበሌ ያለውን መዋቅርም በከፍተኛ ንቅናቄ መምራት ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።

    በዚሁ መድረክ ላይ የተገኙት የአማራ ክልላዊ መንግሥት ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ፋንታሁን ማንደፍሮ ይህ እቅድ በአግባቡ የምንተገብረው ከሆነ እንቦጭ የሚስከትለውን ጉዳት መቀነስ እንችላለን በማለት ሀሳባቸውን ገልጸዋል። በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ለሚካሄደው ለዚህ ዘመቻ 92 ሚሊዮን ብር የሚያስፈልግ እንደሆነም ተመላክቷል። ለዘመቻውም እስከ 10 ሺህ የሚጠጉ ሰዎችን ለማሳተፍ ታቅዷል።

    የእንቦጭ አረም በተፋሰሱ በሚገኙ 30 ቀበሌዎች በሚያዋስኑት የሐይቁ አካል ላይ ተንሠራፍቶ ይገኛል።

    ምንጭ፦ የውሃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የእንቦጭ አረምን ከጣና ሐይቅ ላይ ለማስወገድ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.