ኢትዮጵያ ውስጥ የኮቪድ-19 (ኮሮና ቫይረስ) ስርጭትን እና ለመከለከል የሚደረገውን ጥረት ወቅታዊ መረጃ

Home Forums Semonegna Stories ኢትዮጵያ ውስጥ የኮቪድ-19 (ኮሮና ቫይረስ) ስርጭትን እና ለመከለከል የሚደረገውን ጥረት ወቅታዊ መረጃ

Viewing 2 posts - 16 through 17 (of 17 total)
  • Author
    Posts
  • #15275
    Anonymous
    Inactive

    ኢትዮጵያ ውስጥ በሚቀጥሉት 3 ወራት በኮቪድ-19 ምክንያት ወደ 8,000 የሚጠጉ ሰዎች ሊሞቱ ይችላሉ፤ ቢሆንም የፊት ጭምብል (ማስክ) መጠቀም ሞትን በ65% ሊቀንስ ይችላል ― የ IHME ትምበያ

    ለኢትዮጵያ የሚደረጉት አዳዲስ የ IHME COVID-19 ትምበያዎች እንደሚያሳዩት፣ እስከ ጥቅምት 22 ባለው ጊዜ ድረስ ወደ 8,000 የሚጠጉ ሰዎች (በኮቪድ-19 ምክንያት) ይሞታሉ፣ ቢሆንም የፊት ጭምብል (ማስክ) መጠቀም ሞትን በ 65% ሊቀንስ ይችላል።

    ሲያትል፥ ዋሽንግተን ግዛት (IHME) – በዩኒቨርሲቲ ኦፍ ዋሺንግተ የሚገኘው Institute for Health Metrics and Evaluation (የጤና ሜትሪክስና ግምገማ ተቋም) (IHME)፥ ሀገሪቱ የማኅበራዊ መራራቅ ፖሊሲን ላላ የማድረጉን ፖሊሲ ማስተግበሩን ከቀጠለች፥ በኢትዮጵያ ውስጥ እስከ ጥቅምት 22 ባለው ጊዜ ውስጥ፣ 7,872 ሰዎች (ከ 1,115 እስከ 31,971 የሚሆኑ ) በኮቪድ-19 ምክንያት እንደሚሞቱ ይተነብያል።

    ቢሆንም ጭምብልን መጠቀም ስርጭትን መቆጣጠርን ሊረዳና የመከላከል አገልግሎት ይሰጣል ብለው የ IHME ዳይሬክተር፥ ዶ/ር ክርስቶፈር መሪ (Dr. Christopher Murray) ተናግረዋል። ተቋሙ እንደ ሞዴል የተጠቀመበት እጅግ ከፍተኛ የፊት ጭምብል ጥቅም ላይ መዋልን ሲሆን፥ 95% የሚሆነው ሕብረተሰብ ጭምብል እውጭ በሚንቀሳቀስበት ወቅት ቢጠቀም፥ ሞትን በ 65%፣ ማለትም በ 2,790 ሰዎች (ከ 675 እስከ 9,341 የሚሆኑ) ይቀንሳል ተብሎ ይገምታል።

    “ኢትዮጵያ ገና በመጀመሪያው የወረርሽኝ ደረጃ ላይ ነው ያለችው፤ እናም ሞትን አስመልክቶ ገና ጣርያውን አልነካነውም፣ ስለሆነም ሀገሪቱ እነዚህን አዋጆችን ላላ እያረገች በሄደችበት ወቅት፣ ይህ አስከፊ ቫይረስ በመላው ሀገሪቱ፣ በተለይም በአዲስ አበባ በፍጥነት ይሰራጫል የሚል ስጋት አለኝ” ብለው የ IHME ዳይሬክተር ዶ/ር ክሪስቶፈር መሪ ተናግረዋ። “ይህንን አዝማሚያ ለመቀልበስና ቫይረሱን በቁጥጥር ስር አውሎ ህይወትን ለማዳን የሚያስችሉ እርምጃዎች መወሰድ ይኖርባቸዋል።”

    የተደረገው ትንበያ ለእያንዳንዱ ሚሊዮን ሰው 8 ሰው በሚሞትበት ወቅት ላይ፣ ሀገሪቱ፣ የማኅበራዊ መራራቅን አዋጅ ለስድስት ሳምንታት አስተግብራለች ብሎ በመገመት ነው። ቢሆንም ሀገሪቱ ገና እዚያ ደረጃ ላይ ከጥቅምት 22 ቀን 2013 ዓ.ም. በፊት አትደርስም ተብሎ ነው የሚገመተው።

    ትንበያው ምን ያህል የሀኪም ቤት አልጋዎችና የ ICU አልጋዎች እንደሚይስፈልጉ ደግሞ ይገምታል። ወረርሽኙ አሁን ባለበት የአካሄድ ፍጥነት ከቀጠለ፥ ኢትዮጵያ ያሏት ለኮቪድ-19 በሽተኞች የተዘጋጁ የ ICU አልጋዎች በሐምሌ መጀመሪያዎች (2012 ዓ.ም.) ላይ ይሞላሉ ተብሎ ይጠበቃል።

    “ኢትዮጵያና ሌሎች የአፍሪቃ መንግሥታት ከባድ ሁኔታ ገጥሟቸዋል” ብለው ዶ/ር መሪ ይናገራሉ። “ጭንብልን መጠቀም፣ የምርመራ ቁጥርን መጨመርና ሌሎች እርምጃዎች፣ በተለይም በሽታን የመከላክል አቅማቸው የተዳከሙ ሰዎች፣ አረጋውያን፣ እና ሌሎች መሃል ቫይረሱ እንዳይሰራጭ ለመግዳት የሚረዱ ዋና መሣርያዎች ናቸው።”

    እነዚህ አዳዲስ ግምቶች በመላው ከሳሃራ በታች ያሉ የአፍሪቃ ሀገራት ውስጥ ያለውን የወረርሽኝ እድገትን ያሳያል። የማኅበራዊ መራራቅ አዋጅ ተግባራዊ ከሆነ እስከ ጥቅምት 22 ቀን 2013 ዓ.ም. ባለው ጊዜ ውስጥ፣ ደቡብ ኣፍሪቃ ውስጥ፣ 34,757 ሟች (ከ 13,263 እስከ 64,199 የሚሆን)፣ እንዲሁም ኬንያ 5,613 ሟች (1,613 እስከ 18,493) ይኖራል ተብሎ ይጠበቃል።

    እነዚህ አዳዲስ የሟች ቁጥር ግምታዊ ኣሃዞችና ሌሎች መረጃዎችን በ https://covid19.healthdata.org ላይ ሊገኙ ይችላሉ።

    IHME ይህንን የኮቪድ-19 ግምታዊ አሃዝን እውን ለማድረግ የረዱንን የእነዚህንና የሌሎችን ጥረቶችን ለመጥቀስ ይፈልጋል።

    ስለ Institute for Health Metrics and Evaluation (የጤና ሜትሪክስና ግምገማ ተቋም)

    የ Institute for Health Metrics and Evaluation (IHME)፣ በ University of Washington School of Medicine ውስጥ የሚገኝ፣ በአለም አቀፍ ደረጃ የሚገኙ የጤና ችግሮችን አስመልክቶ በጣም ትክክለኛና ተነጻጻሪ የመጠን ደረጃ የሚሰጥና፣ ለእነዚህ ችግሮች የመፍትሄዎችን ስትራተጂዎችን የሚገመግም፣ ገለልተኛ የሆነ አለማቀፋዊ የጤና ምርመር ድርጅት ነው። IHME ግልጽና፣ ፖሊሲ ነዳፊዎች፣ የሕዝብን ጤና ለማሻሻል የሚያስችሉ አቅርቦቶችን በአግባቡ ለማቅረብ የሚያስችሉ፣ እውቀትን የተሞረከዙ ውሳኔዎችን ለማስተላለፍ የሚያስችሏቸውን ማስረጃዎችን ለሆሉም ለማቅረብ በታታሪነት ይሠራል።

    ምንጭ፦ healthdata.org

    [caption id="attachment_15277" align="aligncenter" width="600"]IHME COVID-19 Ethiopia Update በኮቪድ-19 ምክንያት የሚሞቱ ሰዎች IHME COVID-19 Ethiopia Update[/caption]

    #15477
    Semonegna
    Keymaster

    የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን በመከላከልና በመቆጣጠር ረገድ ጉልህ ሚና ተጫውቷል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን በመከላከልና በመቆጣጠር፣ እንዲሁም ሊያስከትል ይችል የነበረዉን ጉዳት በመቀነስ ረገድ ከፍተኛ ሚና ተጫዉቷል።

    የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርሽኝ ወደ ሀገራችን መግባቱን ተከትሎ መጋቢት 30 ቀን 2012 ዓ.ም. የታወጀዉ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ወረርሽኙ/ቫይረሱ ሊያስከትል ከሚችለዉ የከፋ ጉዳትን በመቀነስ በኩል ያበረከተዉ አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑን በኢፌዲሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የሕግ ማርቀቅና ማስረፅ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ በላይሁን ይርጋ ገልጸዋል።

    የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርሽኝን ለመከላከልና ለመቆጣጠር እንዲሁም የሚያደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ በተለመደው የጤና አጠባበቅ ዘዴ እና አካሄድ ለመቆጣጠር አዳጋች በመሆኑ፥ ሀገራችንም የወረርሽኙን አደገኛነት በመገንዘብ ይህን ወረርሽኝ ለመከላከልና ለመቆጣጠር እንዲሁም የሚያደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ እንዲቻል መጋቢት 30 ቀን 2012 .ም. የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በማውጣት በሥራ ላይ እንዲውል አድርጋለች።

    የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ተከትሎ ሦስት ደንቦችና ስድስት መመሪያዎችን በማውጣት የተለያዩ ክልከላዎችንና ግዴታዎችን በመደንገግ ተግባራዊ እየተደረጉ የሚገኙ ሲሆን ሥራውን የሚመሩ ከብሔራዊ ኮሚቴ ጀምሮ ከፌዴራል እስከ ክልል ድረስ ባሉ አደረጃጀቶች የተለያዩ ኮሚቴዎችና ንዑሳን ኮሚቴዎች እንዲቋቋሙ በማድረግ ሥራውን በተናበበና በተቀናጀ መልኩ እየሠሩ ይገኛሉ።

    ከተቋቋሙት ንዑስ ኮሚቴዎች መካከል ከፌዴራል እስከ ክልል እና ወረዳ ባሉ አደረጃጀቶች የተቋቋመው የሕግ ጉዳዮች ንዑስ ኮሚቴ አንዱ ሲሆን፥ ይህ ንዑስ ኮሚቴ በፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የሚመራ ሆኖ የወጡ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሕጎች ለሚመለከተው አካል በወቅቱ እንዲደርሱ ሲያደርግ የቆየ ሲሆን ሕጎቹ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ የተለያዩ መንገዶችን በመጠቀም ሲያከናውን የቆየ መሆኑን ዳይሬክተሩ ገልፀዋል።

    ግንዛቤ ከተፈጠረ በኋላ ንቃተ ሕጉ በሕብረተሰቡ ላይ ያመጣዉን ለዉጥና አፈፃፀሙስ ምን ይመስላል የሚሉትን በመለየትና ወጣ ገባ የታየባቸዉን ጉዳዮች በመለየት ከሚመለከታቸዉ አካላት ጋር መድረኮችን በመፍጠርና በቪዲዮ ኮንፈረንስና በፊት ለፊት ስልጠና በመታገዝ የተስተዋሉ ክፍተቶች ላይ ዉይይቶች እየተደረጉ አቅጣጫ እንዲሰጥባቸዉ የማድረግ ሥራዎች ሲሠሩ መቆየታቸዉን አክለዉ ገልጸዋል።

    በአንዳንድ ክልሎች ወጣ ገባ አፈፃፀም መኖር እና ሕጉን አዉቆ መተግበር ላይ በማኅበረሱ ዘንድ የታዩት ቸልተኝነቶች የፈጠሩት አንዳንድ ክፍተቶች የተስተዋሉ መሆኑን የጠቆሙት አቶ በላይሁን፥ ሆኖም ግን አዋጁ መታወጁ የኮሮና ወረርሽኝ ሊያደርሰዉና ሊያስከትለዉ ይችል ከነበረዉ የከፋ አደጋ ታድጎናል ሲሉ ተናግረዋል።

    ምንጭ፦ የኢፌዲሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ

    የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን በመከላከልና በመቆጣጠር

Viewing 2 posts - 16 through 17 (of 17 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.