የኢትዮጵያ ቡና ከመቐለ 70 እንድርታ ጋር አዳማ ላይ አልጫወትም አለ፤ በዒድ አል ፈጥር ምክንያት ጨዋታው በድጋሚ ተራዝሟል

Home Forums Semonegna Stories የኢትዮጵያ ቡና ከመቐለ 70 እንድርታ ጋር አዳማ ላይ አልጫወትም አለ፤ በዒድ አል ፈጥር ምክንያት ጨዋታው በድጋሚ ተራዝሟል

  • This topic has 1 reply, 2 voices, and was last updated 6 years ago by Anonymous.
Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #11065
    Anonymous
    Inactive

    የኢትዮጵያ ወንዶች ፕሪሚየር ሊግ ውድድር ላልተወሰነ ጊዜ እንዲቋረጥ ተወሰነ
    —–

    የኢትዮጵያ ወንዶች ፕሪሚየር ሊግ ውድድር ለጊዜው እንዲቋረጥ ውሳኔ መተላለፉን ውድድሩ በበላይነት የሚቆጣጠረው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ግንቦት 28 ቀን 2011 ዓ.ም. አስታወቀ።

    የፌዴሬሽኑ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ግንቦት 28 ባደረጉት አስቸኳይ ስብሰባ በውድድሩ ከሚካፈሉ የእግር ኳስ ክለቡችና ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ሌሎች አካላት ጋር ውይይት ተደርጎ፥ ውድድሮች በተገቢው መንገድ የሚካሄዱበት ዘላቂ መፍትሄ እስኪሰጥ ድረስ የወንዶች ፕሪሚየር ሊግ ላልተወሰነ ጊዜ እንዲቋረጥ ወሳኔ ላይ ደርሰዋል።

    የተደረገውን የአስቸኳይ ስብሰባ ውሳኔ ተከትሎ ግንቦት 29 ቀን 2011 ዓ.ም. በአዳማ ሊካሄድ የነበረው የኢትዮጵያ ቡና እና የመቐለ 70 እንደርታ ጨዋታ ለጊዜው እንዲሰረዝም ተደርጓል። ከዚህም በተጨማሪ ለፌዴሬሽኑ የሚቀርቡ የተለያዩ ጥያቄዎች በፌዴሬሽኑ የዲሲፕሊን መመሪያ የውድድር ደንብ መሰረት እንዲታዩ ውሳኔ ተላልፏል።

    ምንጭ፡- የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.