የመንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምደባ ይፋ ሆነ

Home Forums Semonegna Stories የመንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምደባ ይፋ ሆነ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #7923
    Semonegna
    Keymaster

    የመንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምደባን ይፋ ከማድረጉ በፊት ኤጀንሲው የተለያዩ የማጣራት ሥራዎችን በማከናወን ሂደት ውስጥ በመቆየቱ ምክንያት ምደባው ዘገየ በማለት ቅሬታችሁን ስታሰሙ ለነበራችሁ ተማሪዎች እና የተማሪ ቤተሰቦች ከወዲሁ ይቅርታ የጠየቀ ሲሆን ተማሪዎች በተመደባችሁባቸው የትምህርት ተቋማት በምትሄዱበት ወቅት የነገዋ ኢትዮጵያ በእናንተ ትከሻ ላይ መሆኗን በመገንዘብ በትምህርታችሁ ላይ ብቻ ትኩረት በመስጠት ውጤታማ በመሆን ለሀገራችን እድገት እና ልማት የበኩላችሁን አስተዋጽዖ ታበረክቱ ዘንድ ኤጀንሲው ከአደራ ጋር መልዕክቱን አስተላልፏል።

    አዲስ አበባ (ኢዜአ/NEAEA)– የመንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምደባ ይፋ መሆኑን የሀገር አቀፍ የትምህርት ፈተናና ምዘናዎች ኤጀንሲ (NEAEA) አስታወቀ።

    የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ አርዓያ ገብረእግዝአብሔር ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንዳስታወቁት፤ የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምደባ ከዛሬ ከመስከረም 25 ቀን 2011 ዓም ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ ይፋ ሆኗል።

    ምደባው የተማሪዎችን ውጤት፣ የትምህርት ዓይነት፣ የዩንቨርስቲ ምርጫ፣ የዩንቨርስቲዎችን የቅበላ አቅም፣ የወንዶችና የሴቶችን ምጠና ማዕከል ባደረገ እንዲሁም የልዩ ድጋፍ ተጠቃሚዎችን ያገናዘበ መሆኑን ነው ያመላከቱት።

    ዓይነ ስውራንን፣ መስማት የተሳናቸውን፣ አካል ጉዳተኞችን/ በተጨማሪም የጤና እክል ያለባቸው እና ከታወቀ የመንግስት ሆስፒታል የሜዲካል ቦርድ ማረጋገጫ ያቀረቡት ላይ የማጣራት ሥራዎችን ካካሄደ በኋላ ምደባው እንደተዘጋጀም እንዲሁ አስታውቀዋል።።

    በዚሁ መሰረት በዘንድሮው የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና የማለፊያ ነጥቡን ያለፉ 138 ሺ 283 የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ሲሆኑ 75ሺ 338 የማህበራዊ ሳይንስ በድምሩ 213 ሺ 621 ናቸው።

    ከነዚህም መካከል 98 ሺ 576 የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎችና 51 ሺ 229 የማህበራዊ ሳይንስ በድምሩ 149 ሺ 805 ተማሪዎች ቅዱስ ጳውሎስ ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ፣ በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎችን ጨምሮ ባሉት የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ በአጠቃላይ የሚመደቡ ይሆናል።

    ◌ RELATED: 35 Best Universities and Colleges Ethiopia (public and private)

    ከነዚህም በኤጀንሲው በኩል በ43ቱ የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት 95 ሺ 681 የተፈጥሮ ሳይንስ (natural science) እንዲሁም 51ሺ 066 የማህበራዊ ሳይንስ (social science) በድምሩ 146 ሺ 747 ተማሪዎች መመደባቸውን አስታውቀዋል።

    ተማሪዎች ወደ ተመደቡበት የትምህርት ተቋማት በሚሄዱበት ወቅትም የነገዋ ኢትዮጵያ በትከሻቸው ላይ መሆኗን በመገንዘብ ለትምህርታችሁ ትኩረት እንዲሰጡም አቶ አርአያ አሳስበዋል።

    ከግንቦት 27-30 ቀን 2010 ዓ.ም በተሰጠው የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና (የ12ኛ ክፍል ፈተና) 154,010 ወንዶች እንዲሁም 127,964 ሴቶች በድምሩ 281,974 ተማሪዎች የወሰዱ ሲሆን በሐምሌ 24 ቀን 2010 ዓ.ም ውጤት ይፋ መደረጉ ይታወሳል።

    ተማሪዎች ምደባችሁን በኤጀንሲው ድረ-ገጽ app.neaea.gov.et በመግባት ማየት እንደሚችሉም ነው የገለፁት።

    ምንጮች፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) እና የሀገር አቀፍ የትምህርት ፈተናና ምዘናዎች ኤጀንሲ (NEAEA)

    የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.