“የኪነጥበብ (የአዝማሪ) ሚና ትናንት፣ ዛሬና ነገ” የሰላም እና የኪነጥበብ መድረክ በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ

Home Forums Semonegna Stories “የኪነጥበብ (የአዝማሪ) ሚና ትናንት፣ ዛሬና ነገ” የሰላም እና የኪነጥበብ መድረክ በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #13172
    Semonegna
    Keymaster

    ደብረ ታቦር (ሰሞነኛ) – “የኪነጥበብ (የአዝማሪ) ሚና ትናንት፣ ዛሬና ነገ” በሚል ርዕስ የሰላም እና የኪነጥበብ መድረክ በርከት ያሉ ታዳሚዎች በተገኙበት በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ።

    በአዝማሪ ላይ የተሠሩ ጥናቶች እንደሚሉት የአዝማሪዎች አገልግሎት በማኅበራዊ ሕይወት ላይ ብቻ የተወሰነ አልነበረም፡፡ አዝማሪዎች ዘፈንን ከሚከውኑበት ሰውን የማዝናናት ተለምዷዊ ተግባር ባሻገር በኢትዮጵያ ባህላዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ታሪክ ውስጥ ጉልህ ስፍራ ነበራቸው፡፡ ለዚህም ምክንያቱ Kimberlin (1983) እንደሚገልፁት፥ ዘፈን ከኢትዮጵያ ሕዝብ አኗኗር፣ ይትብሃልና ሕይወት ጋር ከፍተኛ ቁርኝት ያለው በመሆኑ ነው፡፡ እንደ Ashenafi (1971) እና Teclehaimanot (1986) ትንታኔ አዝማሪዎች ዋና ሥራቸው ማዝናናት ቢሆንም በተጨማሪ ግን ዜናና ታሪክ ነጋሪዎች፣ ሃያሲዎች፣ የፖለቲካ ተንታኞች፣ መዝጋቢዎች፣ አዝማቾች፣ ሆነው አገልግለዋል፡፡ ይህንን ታሳቢ ያደረገው የደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ከሰላም ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር “የኪነጥበብ (አዝማሪ) ሚና ትናንት፣ ዛሬና ነገ” በሚል ርዕስ ታህሳስ 20 ቀን 2012 ዓ.ም. የግማሽ ቀን መርሐ-ግብር አካሂዷል።

    ሰላም ኢትዮጵያ፣ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ እና ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ በመተባበር ባዘጋጁት መድረክ የደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር አነጋግረኝ ጋሻው የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን፥ በንግግራቸውም እንደገለፁት ኪነጥበብ ለዕድገት ወሳኝ መሆኑንና፣ ኪነጥበብንና ባህልን ያላካተተ ዕድገት ሙሉ ሊሆን እንደማይችል እና ይህ ሰላምና ባህልን አጣምሮ የያዘ መድረክ የደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚከታተለው ገልጸዋል።

    በመርሐ-ግብሩ “የኪነጥበብ (አዝማሪ) ሚና ትናንት፣ ዛሬና ነገ” በሚል ርዕስ የተካሄደ ሲሆን ከውይይቱ በተጨማሪ በመድረኩ የቀረቡት ልዩ ልዩ የኪነጥበብ ሥራዎች ድምቀት ሰጥተውታል።

    በመርሐ-ግብሩ መጨረሻ የመዝጊያ ንግግር ያደረጉት የደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የም/ማ/አ/ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ/ር መንበሩ ተሾመ ባህሉንና ትውፊቱን የማያውቅና እነዚህን ሀብቶቹን የማያለማ ማኅበረሰብ ሁልግዜም አያድግም፤ በመጤ ባህሎች የራሱን ወርቃማ የሆኑ ሀብቶቻችንን እያጣንሁልግዜ የውጭ ናፋቂ እየሆንን፤ ስልጣኔ የሚመስለን የሌሎቹ ነው። ግን እኛ ወርቃማ የሆነ ጥበብ አለን፤ እናም ይኸ ለማኅበራዊ፣ ለኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ፋይዳው ከፍተኛ ለሆነው ባህል ሁላችንም የበኩላችንን ድጋፍ ማድረግ፣ መስመር ማሳየት፣ ስልጠናዎችን ማዘጋጀት ባለሙያዎችን አይዟቹህ ማለት አለብን ሲሉ ገልጸዋል። ባለሙያዎችን ለወደፊቱ እንዴት እንደግፋቸው? እንዴት እናበረታታቸው? የውጭና የውስጥ ሀይሎችን እንዴት እናስተሳስራቸው የሚለውን ለቀጣይ የሁላችንም የቤት ሥራ መሆን አለበት ያሉ ሲሆን በመጨረሻም ለመርሐግብሩ መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከቱትን አካላት በሙሉ አመስግነዋል – ዶ/ር መንበሩ ።

    ማጣቀሻዎች፦

    • Ashenafi Kebede: The music of Ethiopia: its development and cultural setting. Dissertation, Wesleyan University. (1971)
    • Cynthia Tse Kimberlin: “The Music of Ethiopia“, in Music of Many Cultures, E. May, ed., Berkeley, Los Angeles: University of California Press. (1983).
    • Teclehaimanot G. Selassie: A brief survey study of the Azmaris in Addis Ababa. Proc. of the International Symposium on the Centenary of Addis Ababa. (1986).

    ምንጭ፦ ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የኪነጥበብ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.