በአገሪቱ እድገት የራሳቸውን አሻራ ለማሳረፍ ዝግጁ መሆናቸውን ኢትዮጵያዊያን የዲያስፖራ አባላት ገለፁ

Home Forums Semonegna Stories በአገሪቱ እድገት የራሳቸውን አሻራ ለማሳረፍ ዝግጁ መሆናቸውን ኢትዮጵያዊያን የዲያስፖራ አባላት ገለፁ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #7955
    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ኢዜአ)፦ መንግሥት በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን በአገራቸው ልማት ቀጥተኛ ተሳታፊ እንዲሆኑ እያደረገ ያለውን ሁሉን አቀፍ ጥሪ ከግምት ያስገባ አዲስ አቅጣጫ እየቀየሰ መሆኑን የኢትዮጵያ የዲያስፖራ ማኅበር አስታወቀ።

    አገሪቱ የጀመረችውን የለውጥ ሥራ ለማገዝ፣ እንደዚሁም በውጭ የሚኖረው ዜጋ በሌሎችም አገራዊ ጉዳዮች ላይ ተሳታፊ እንዲሆን ለማስቻል ማህበሩ አደረጃጀቱን መልሶ በማዋቀር ላይ ነው ተብሏል።

    በሽርክና ወይንም በሌላ መንገድ በመደራጀት በአገሪቱ የልማት እድገት ውስጥ የራሳቸውን አሻራ ለማሳረፍ ዝግጁ መሆናቸውን ኢትዮጵያዊያን የዲያስፖራ አባላት ገልፀዋል።

    በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን መዋዕለ ንዋያቸውን በማቀናጀት አገር ውስጥ መሥራት የሚሹ ከሆነ መንግሥት የተለየ ድጋፍ እንደሚያደርግ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) አረጋግጠዋል።

    ጠቅላይ ሚኒስትሩ መስከረም 27 ቀን 2011 ዓ.ም. በአዳማ ኢንዱስትሪያል ፓርክ የምርቃት ስነ-ስርዓት ላይ ባስተለላፉት መልዕክት፤ በውጭ የመኖሩ ኢትዮጵያዊያን በአገሪቱ ልማት ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ በድጋሚ ጥሪ አቅርበዋል።

    በተለይም በስቶክ ማርኬት ወይንም በአክሲዮን ንግድ ዘርፍ የተሰማሩ ኢትዮጵያዊያን ዲያስፖራ አባላት በተናጠልም ሆነ በመደራጀት ወደ አገራቸው ተመልሰው በልማት እንዲሰመሩ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠይቀዋል።

    ያላቸውን እውቀትና ገንዘብ በማደራጀት መቅረብ ለሚችሉ የዲያስፖራ አባላት መንግሥት የተለየ ድጋፍ እንደሚያቀርብ ነው ዶ/ር አብይ ያረጋገጡት።

    ቪድዮ፦ ኢትዮጵያውያን ዲያስፖራዎች ሀገር ውስጥ ለመሥራት ያላቸው ፍላጎት እና የሚያጋጥማቸው የቢሮክራሲ ችግር

    ኢትዮጵያዊያኑ ዲያስፖራዎች በበኩላቸው መንግሥት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በውጭ ለሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን እያደረገ ያለውን ጥሪ በአዎንታዊ መልኩ እንደሚመለከቱት ገልጸዋል።

    በዚህም በተለይም በሽርክና ወይንም በሌላ መንገድ በመደራጀት በአገሪቱ የልማት እድገት ውስጥ የራሳቸውን አሻራ ለማሳረፍ ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

    በተደራጀ አግባብ ከጓደኞቻቸው ጋር ተነጋግረው ትልቅ ካምፓኒ ይዘው ለመምጣት ሃሳብ እንዳላቸው የተናገሩት በውጭ የሚኖሩት ወይዘሮ አማኒ መሃመድ ናቸው።

    “የሥራ ሁኔታ እየተመቻቸ ነው፤ ሁሉም ሰው እውቀቱንና ገንዘቡን ኢንቨስት በማድረግ የአገሪቱን እድገት ለማረጋገጥ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ መልካም ነው። እኔም እንደ አንድ ውጭ አገር እንደሚኖር ዜጋ ወደ ሃገሬ መጥቼ ለመሥራት ትልቅ እቅድ ይዤ እንደምመጣ ተስፋ አደርጋለሁ” ያሉት ደግሞ አቶ አማን አህመድ ናቸው።

    የኢትዮጵያ የዲያስፖራ ማኅበር ዳይሬክተር አቶ አብርሃም ስዩም በበኩላቸው ማኅበራቸው ከሚመለከታቸው የመንግሥት ተቋማት ጋር በመሆን የዲያስፖራውን የልማት ተሳትፎ ለማሳደግ እየሠራ ነው።

    በተለይ ደግሞ በኢንደዱትሪ ፓርኮች ላይ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ሊኖራቸው የሚችለውን ተሳትፎ ለማጎልበት ፓርኮቹን የሚጎበኙበት ሁኔታ እየተመቻቸ መሆኑን ተናግረዋል።

    ይህም ዲያስፖራው ስለ ፓርኮቹ በቂ መረጃ እንዲኖረው ትልቅ እድል እንደሚከፍት ገልጸው ማኅበሩ መረጃ ከመስጠቱ ሥራ ጎን ለጎን ሌሎች የውጭ ዜጎችም በዘርፉ እንዲሰማሩ የበኩሉን ጥረት ያደርጋል ብለዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)

    የኢትዮጵያ የዲያስፖራ ማኅበር

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.