ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በጥቅምት ወር ወደ ጀርመን ያቀናሉ

Home Forums Semonegna Stories ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በጥቅምት ወር ወደ ጀርመን ያቀናሉ

Viewing 1 post (of 1 total)
  • Author
    Posts
  • #7825
    Semonegna
    Keymaster

    የጀርመኗ መራሂተ መንግስት አንጌላ መርክል ባደረጉላቸው ግብዣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክትር አብይ አህመድ በጥቅምት ወር ለይፋዊ ጉብኝት ወደ ጀርመን የሚያቀኑ ሲሆን፥ በአውሮፓ የሚገኙ ኢትዮጵያዊንን አግኝተው ያነጋግራሉ ተብሏል።

    አዲስ አበባ (የኢፌዴሪ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክትር አብይ አህመድ በጥቅምት ወር ለይፋዊ ጉብኝት ወደ ጀርማን የሚያቀኑ ሲሆን፥ በዚሁ ጉብኝታቸውም ከጀርመኗ መራሂተ መንግስት አንጌላ መርክል (Angela Merkel) እና ሌሎች የሀገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር በጀርመን ዋና ከተማ በርሊን እንደሚገናኙም ነው የተገለጸው።

    የጀርመኗ መራሂተ መንግስት አንጌላ መርክል በፈረንጆቹ ነሃሴ ወር በኢትዮጵያ እየመጣ ያለውን ለውጥ በመደገፍ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ጎን መሆናቸውን በስልክ በገለጹበት ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጀርመን ይፋዊ ጉብኝት እንዲያደረጉ መጋበዛቸውም ታውቋል።

    በዚህም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክትር አብይ አህመድ በጥቅምት ወር መጨረሻ ለይፋዊ ጉብኝት ወደ ጀርመን የሚያቀኑ ሲሆን፥ በአውሮፓ የሚገኙ ኢትዮጵያዊንን አግኝተው ያነጋግራሉ ተብሏል።

    በፈረንሳይ ፓሪስ፣ ጀርመን ፍራንክፈርት ከተሞችም በሚዘገጁ መድረኮችም ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክትር አብይ ከኢትዮጵያዊያኑ ጋር እንደሚገናኙ የተገለጸው።

    ሀገራዊ ዜና፦ አብይ አህመድ (ዶ/ር) እና ደመቀ መኮንን በድጋሚ የኢህአዴግ ሊቀመንበር እና ምክትል ሊቀመንበር ሆነው ተመረጡ

    በፈረንጆቹ ጥቅምት 31 ቀን 2011 (ጥቅምት 21 ቀን 2011 ዓም) ዓም በጀርመን ሁለተኘዋ ከተማ ፍራንክፈርት ላይ መድርክ እንደሚዘጋጅ እና ጠቅላይ ሚኒትሩ በአውሮፓ የሚገኙ ኢትዮጵያዊንን አግኝተው እንደሚያነጋግሩም ታውቋል።

    ለዚሁ ፕሮግራምና የጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አቀባበልን እስመልክቶ ከ80 ማህበራት የተውጣጡ አበላት ያሉት ኮሚቴ አየሰራ መሆኑንም ነው የተገለጸው።

    በጀርመን የኢትዮጵያ ቆንሰላ ጄኔራል ምህረት አብ ሙሉጌታ እንደገለጹት አሁን ላይ በኢትዮጵያ እየታየ ያለውን ለውጥ በመደገፍ 25 ሺህ ያህል ኢትዮጵያን ፍርንክፈረት ኮመርዝባክ አረና ስታዲየም (Commerzbank-Arena) በሚዘጃጀው ፕሮግራም ላይ ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።

    ምንጭ፦ የኢፌዴሪ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት

    ጀርመን

Viewing 1 post (of 1 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.