ከኢሳት (ESAT TV) የሥራ አስፈጻሚ ቦርድ የተሰጠ መግለጫ

Home Forums Semonegna Stories ከኢሳት (ESAT TV) የሥራ አስፈጻሚ ቦርድ የተሰጠ መግለጫ

  • This topic has 2 replies, 3 voices, and was last updated 6 years ago by Anonymous.
Viewing 2 posts - 1 through 2 (of 2 total)
  • Author
    Posts
  • #10999
    sami
    Participant

    It makes sense….great

    #11000
    Anonymous
    Inactive

    አቶ ነአምን ዘለቀ የኢሳት የሥራ አስፈጻሚ ቦርድ አባል በግላቸው የሰጡት መግለጫ

    ሶሻል ሚዲያ ላይ ለምትገኙ ኢትዮጵያውያን ሁሉ፦

    ኢሳትን በሚመለከት የውስጥ “መረጃ” በሚል በማኅበራዊ ሚዲያ የተሰራጩ ነገር ግን ከሃቁ፣ ከእወነታው ከሂደቱ የራቁ፣ ሕዝብን ለማወናበድ፣ ኢሳትንም ለማፍረስ ሆነ ተብሎ የተደረገ መሆኑ እንዲታወቅ እንወዳለን። የወጣው ስም ዝርዝር ከሀቁ የራቀ፣ መሰረተ ቢስ መሆኑን ለማሳወቅ እወዳለሁ።

    ማንኛውም ተቋም ገቢውን የሚያገኝበት ሁኔታ ሲለወጥ የማስተካከያ እርምጃዎች ይወስዳል። በእኔ በኩል ለአለፉት 4 ዓመታት አራት ሌሎች አባላት የሚገኙበት የኢሳት የሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሆነን ስንሠራ እንዳደረግነው ሁሉ ኢሳትን የሕዝብ ዓይንና ጆሮ ሆኖ እንዲቀጥል ለማድረግ የማዋቀርና የማስተካከል በርካታ እርምጃዎች ስንወስድ የቆየን ሲሆን አሁንም ተጨማሪና ተከታታይ እርምጃዎችን እንደሚወስድ በአፕሪል 18 ቀን 2019 (ሚያዝያ 10 ቀን 2011 ዓ.ም.) ለሕዝብና ለኢሳት ቤተስቦች ይፋ ማድረጉ ይታወሳል።

    በተጨማሪም ኢሳት ከለውጡ በፊት በነበረው አቅምና ሁኔታ ማስቀጠል እንደማይቻል ለኢሳት ባልደረቦች ስናሳስብና ለወራት ያህል ብዙ ዝርዝሮች የሚገኙበት ውይይቶች ስናደርግ ቆይተናል፤ መፍትሄዎችም ለማፈላለግ ብዙ ጊዜ በርካታ ስብሰባዎች ተደርገዋል። ካስፈለገ ሁሉንም ጉዳይ ከጅምሩ እስካሁን የነበረውን በተለያዩ ደረጃዎች የተደረጉትን ሁሉ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ይፋ ለማድረግ እንደሚቻል መታወቅ አለበት።

    ይህ “መረጃ” ተብዬ የወጣው ኢሳትን ለማፍረስ በዚህም ተጠቃሚ ለመሆን በታቀደ መልኩ ሆን ተብሎ የተሠራና ከዶ/ር ብርሃኑም ሆነ ዶ/ር አብይ አህመድ ጋር በመሆን የተወሰነ የፓለቲካ አስተሳሰብ ያላቸውን ለማጥቃት የታለመ እንደሆነም የተሰራጨው “መረጃ” መሰረተ-ቢስ መሆኑን ለኢትዮጵያ ሕዝብ ለማረጋገጥ እወዳለሁ።

    “ቅጥረኛ” በሚልም እኛን ለመወንጀል የደፈሩ ግለሰቦችም ሆነ “መረጃው”ን የሰጧቸው ሰዎች በዚህ ሸፍጥ የሚያሸንፉና ሕዝብን የሚያወናብዱ ከመሰላቸው ይህ እንደማይሳካላቸው፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ማን ምን እንደነበር፣ ከየትስ እንደመጣ፣ መቼ ወደ ኢሳት እንደመጣ፣ ማንስ እንዳመጣው፣ እኛም ምን እንዳደረግን፣ ከየት ወዴት እንደተጓዝን፣ ሁሉንም እስካሁን ድረስ የተደረገውን ጉዞ ከማስረጃና ከሰነዶች ጋር ለማቅረብ ስለሚቻል ሕሊናቸውን እንዲመረምሩና ከዚህ የአደባባይ ነውር ቢታቀቡ የተሻለው መንገድ ነው በማለት በግሌ ሁሉንም ለማሳሰብ እወዳለሁ።

    እዩኝ፣ እዩን ስለተባለ ብቻ “እኛ ብቻ ጋር ሀቅም፣ እውነትም፣ የትግል ባለቤትነትም፣ ዕውቀትም፣ አልፎሞ አሁን ደግሞ ኢሳትም ‘የእኔ’ ብቻ ነው” ባዩ የበዛበት ዘመን ላይ ስለሆንን፣ ነውር ውስጥ እየገቡ እኛን ምላሽ እንድንሰጥ፣ ህዝብም እንዲያዝን የሚያስገድዱን ማናቸውም ወገኖች ሁሉ በድጋሚ፣ ባለፈው እንደሆነው ስም ወደማንሳትና ጭቃ መወራወር እንደተገባው እንዳይሆን በጥብቅ ለማሳሰብ በግሌ እወዳለሁ።

    እውነት ያወጣሀል እንደሚባለው ሃቁን፣ ሂደቱን፣ እውነቱን በዝርዝር ለማውጣት ምንም የምንቸገርበት፣ የምናፍረበትም፣ ለማንም ለምንም ኣንደማንመለስ፣ እንደ አንዳንዶች “ቅጥረኛ’ ሳንሆን 26 ዓመታት ለኢትዮጵያ ህዝብ ፍትህን፣ ነጻነት፣ ለማምጣት ሁለንተናዊ ትግል ያደረግን፣ ሁሉንም ነጋራችንን የሰጠን፣ ከማንም ምንም የማንፈልግ ግለሰቦች እንደምንገኝበት ለህሊናችን ያደርንና ይህንኑ ይዘን እስከ ዕለተ ሞታችን እንደምንቀጥልም ሆዳቸው የሚያውቁ፣ ነገር ግን ይህን ርካሽ ተግባር የትም የማያደርሳቸው ግለሰቦች እንዲያስቡበት፣ ወደ ህሊናቸው እንዲመለሱ በግሌ በጥብቅ ለማሳሰብ እወዳለሁ። ለሁሉም ጎራ ስናሳስብ፣ በግልም፣ በቡድንም፣ በአደባባይ ስም ሳይጠቀስም ለሁለት ሳምንታት እንደተጻፈውና ፣ ለበርካታ ወራት ኢሳት ውስጥ የተፈጠሩ ችግሮችን ለመፍታት ጥረት ስናደርግ እንደከረምነው።

    አቶ ነአምን ዘለቀ የኢሳት የሥራ አስፈጻሚ ቦርድ አባል (በግል)

Viewing 2 posts - 1 through 2 (of 2 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.