ከኢሳት (ESAT TV) የሥራ አስፈጻሚ ቦርድ የተሰጠ መግለጫ

Home Forums Semonegna Stories ከኢሳት (ESAT TV) የሥራ አስፈጻሚ ቦርድ የተሰጠ መግለጫ

Viewing 3 posts - 1 through 3 (of 3 total)
  • Author
    Posts
  • #10995
    Semonegna
    Keymaster

    ከኢሳት (ESAT TV) የሥራ አስፈጻሚ ቦርድ የተሰጠ መግለጫ

    ጉዳዩ፦የኢሳትን (ESAT TV) መዋቅርና አሠራር ማስተካከልን ይመለከታል

    ጊዜው ኢሳትን የመሰሉ የኢትዮጵያዊነትና የዲሞክራሲ ድምጾችን አገራችን ኢትዮጵያ ከመቼውም ጊዜ በላይ የምትፈልግበት ነው። ኢሳትም (ESAT TV) ለዚህ አገራዊ ጥሪ መልስ ለመስጠት በአገር ውስጥም ሆነ ከአገር ውጭ ተጠናክሮ ለመሥራት ቃል መግባቱን በድጋሚ ለማስታወስ እንፈልጋለን።

    የኢሳት ቦርድ (ESAT TV Executive Board) ባለፈው ኤፕሪል ወር (April 2019) ውስጥ ይህንን ጥሪ በወጉ ለመመለስ በስድስት አስፈላጊ የሆኑ ኢሳትን የማጠናከሪያና የማሻሻያ አቅጣጫዎች ከተቋሙ ሠራተኛና የድጋፍ ኮሚቴ ተወካዮች ጋር በመመካር መወሰን እንደሚጀመር አስታውቆ ነበር። በዚህ መሰረት ሜይ 28፣ 2019 (ግንቦት 20 ቀን 2011 ዓ.ም.) ቦርዱ ከመላው ዓለም አቀፍ የኢሳት ባልደረቦች ጋር በመሰብሰብ የመጀመሪያውን ውሳኔ ይፋ አድርጓል።

    ይህ ውሳኔ ያተኮረው ኢሳት ኢንተርናሽናልን በባጀት፣ በሰው ኃይል፣ በፕሮግራሞች ይዘትና አቅጣጫዎች እንዲሁም በአስተዳደር አቅም ከዘላቂነት ጋር እንዲጣጣም ማድረግን ይመለከታል። ውሳኔው እንደማንኛውም ተቋማዊ የመዋቅር የማስተካከያ እርምጃ ጊዜያዊ ችግሮችን ሊፈጥር ቢችልም በዘላቂነት ግን ኢሳትን (ESAT TV) በሁሉም ዘርፍ አቅሙንና ሕዝባዊነቱን በማጠናከር የተመሰረበትን መሰረታዊ ዓላማ እውን ማድረግ ነው።

    ይህንን መሰረተ ሃሳብ በደንብ ተገነዘቦ በሚሠራ የኢሳት አስተዳደርና ባለሙያዎች የተወሰነን ውሳኔ የፖለቲካ ፉክክር ጨዋታ ውስጥ እያስገቡ መተርጎም ትክክል አይሆንም። ይህ ውሳኔ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ሰሞኑን እንደሚወራው በኢሳት ውስጥ ያሉ የጋዜጠኞች የሃሳብ ልዩነቶች ጋር የተያያዘ አይደለም። ኢሳት የፖለቲካ ፓርቲ አይደለም። በባለሙያዎቹ ውስጥ እንደማንኛችንም የህብረተሰብ አባላት የተለያየ የግል እምነትና የፓለቲካ አመለካከቶች እንደሚንጸባረቁ ግልጽ ነው። ሆኖም እንደ ሚዲያ ተቋም የኢሳት ሚና የመንግሥትን ወይም የማንንም አንድ ወገን ፍላጎትን መቃወም ወይም መደገፍ ሳይሆን ሙያዊ ብቃት ያለው አስተማማኝና የተጣራ መረጃ የሚያቀርብ የህዝብ ሚዲያ ሆና ማገልገል ነው።

    የኢሳት ግብ በነጻነት፣ በሙያዊ የጋዜጠኝነት ሥነ-ምግባር፣ እንዲሁም በሕዝባዊ ዓላማ ላይ ተመስርቶ የሚዲያ ምርቶችን በማምረት፡ በፓለቲካዊ፣ በኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና፣ ባህላዊ ርዕሰ ጉዳዮች እንዲሁም የተጣሩ መረጃዎች በማቅረብ ሕዝብን ማገለገል ነው። በተለይ አሁን ሀገራችን ባለችበት ሁኔታ ደግሞ የኢትዮጵያን ሕዝብ አንድነት ማበረታታት፣ የሀገሪቱም ችግሮችና ተግዳሮቶች በዲሞክራሲያዊ መንገድና በውይይት የመፍታትን ባህል እንዲስፋፋ መርዳት ነው።

    ይህንን መሰረተ ሃሳብ በደንብ ተገነዘቦ በሚሠራ የኢሳት አስተዳደርና ባለሙያዎች የተወሰነን ውሳኔ የፖለቲካ ፉክክር ጨዋታ ውስጥ እያስገቡ መተርጎም ትክክል አይሆንም። ዛሬ የተጀመረው የኢሳት ማጠናከሪያ በቅርቡም በቦርድ፣ በአስተዳደር፣ በኤዲቶሪያልና በአጠቃላይ የኢሳት አሠራር ላይ ይቀጥላል። ኢሳት በመጀመሪያ የሥራ ምዕራፉ ማለትም በሀገራችን ከ 27 ዓመታት በላይ የተሰራፋውን አፋኝና ዘረኛ ስርዓት በማስወገድ ሂደት ያበረከተውን አስተዋጽኦ በሚቀጥለውም የሀገርና የሕዝብ አንድነትና የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ሥራ ምዕራፍ ውስጥም እንደሚቀጥል ጥርጥር የለንም። ለዚህም የኢሳት ቤተስቦችና የድጋፍ ኮሚቴዎች እንደወትሮው ኢሳት የህዝን ዓይንና ጆሮ ሆና እንዲቀጥል የበኩላችሁን እንድታደረጉ ትብብራችሁን በአክብሮት እንጠይቃለን።

    ጁን 1 ቀን፣ 2019 (ግንቦት 24 ቀን 2011 ዓ.ም.)፣ ዋሺንግተን ዲሲ
    የኢሳት (ESAT TV) ቦርድ ሥራ አስፈጻሚ
    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ኢሳት (ESAT TV)


    #10999
    sami
    Participant

    It makes sense….great

    #11000
    Anonymous
    Inactive

    አቶ ነአምን ዘለቀ የኢሳት የሥራ አስፈጻሚ ቦርድ አባል በግላቸው የሰጡት መግለጫ

    ሶሻል ሚዲያ ላይ ለምትገኙ ኢትዮጵያውያን ሁሉ፦

    ኢሳትን በሚመለከት የውስጥ “መረጃ” በሚል በማኅበራዊ ሚዲያ የተሰራጩ ነገር ግን ከሃቁ፣ ከእወነታው ከሂደቱ የራቁ፣ ሕዝብን ለማወናበድ፣ ኢሳትንም ለማፍረስ ሆነ ተብሎ የተደረገ መሆኑ እንዲታወቅ እንወዳለን። የወጣው ስም ዝርዝር ከሀቁ የራቀ፣ መሰረተ ቢስ መሆኑን ለማሳወቅ እወዳለሁ።

    ማንኛውም ተቋም ገቢውን የሚያገኝበት ሁኔታ ሲለወጥ የማስተካከያ እርምጃዎች ይወስዳል። በእኔ በኩል ለአለፉት 4 ዓመታት አራት ሌሎች አባላት የሚገኙበት የኢሳት የሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሆነን ስንሠራ እንዳደረግነው ሁሉ ኢሳትን የሕዝብ ዓይንና ጆሮ ሆኖ እንዲቀጥል ለማድረግ የማዋቀርና የማስተካከል በርካታ እርምጃዎች ስንወስድ የቆየን ሲሆን አሁንም ተጨማሪና ተከታታይ እርምጃዎችን እንደሚወስድ በአፕሪል 18 ቀን 2019 (ሚያዝያ 10 ቀን 2011 ዓ.ም.) ለሕዝብና ለኢሳት ቤተስቦች ይፋ ማድረጉ ይታወሳል።

    በተጨማሪም ኢሳት ከለውጡ በፊት በነበረው አቅምና ሁኔታ ማስቀጠል እንደማይቻል ለኢሳት ባልደረቦች ስናሳስብና ለወራት ያህል ብዙ ዝርዝሮች የሚገኙበት ውይይቶች ስናደርግ ቆይተናል፤ መፍትሄዎችም ለማፈላለግ ብዙ ጊዜ በርካታ ስብሰባዎች ተደርገዋል። ካስፈለገ ሁሉንም ጉዳይ ከጅምሩ እስካሁን የነበረውን በተለያዩ ደረጃዎች የተደረጉትን ሁሉ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ይፋ ለማድረግ እንደሚቻል መታወቅ አለበት።

    ይህ “መረጃ” ተብዬ የወጣው ኢሳትን ለማፍረስ በዚህም ተጠቃሚ ለመሆን በታቀደ መልኩ ሆን ተብሎ የተሠራና ከዶ/ር ብርሃኑም ሆነ ዶ/ር አብይ አህመድ ጋር በመሆን የተወሰነ የፓለቲካ አስተሳሰብ ያላቸውን ለማጥቃት የታለመ እንደሆነም የተሰራጨው “መረጃ” መሰረተ-ቢስ መሆኑን ለኢትዮጵያ ሕዝብ ለማረጋገጥ እወዳለሁ።

    “ቅጥረኛ” በሚልም እኛን ለመወንጀል የደፈሩ ግለሰቦችም ሆነ “መረጃው”ን የሰጧቸው ሰዎች በዚህ ሸፍጥ የሚያሸንፉና ሕዝብን የሚያወናብዱ ከመሰላቸው ይህ እንደማይሳካላቸው፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ማን ምን እንደነበር፣ ከየትስ እንደመጣ፣ መቼ ወደ ኢሳት እንደመጣ፣ ማንስ እንዳመጣው፣ እኛም ምን እንዳደረግን፣ ከየት ወዴት እንደተጓዝን፣ ሁሉንም እስካሁን ድረስ የተደረገውን ጉዞ ከማስረጃና ከሰነዶች ጋር ለማቅረብ ስለሚቻል ሕሊናቸውን እንዲመረምሩና ከዚህ የአደባባይ ነውር ቢታቀቡ የተሻለው መንገድ ነው በማለት በግሌ ሁሉንም ለማሳሰብ እወዳለሁ።

    እዩኝ፣ እዩን ስለተባለ ብቻ “እኛ ብቻ ጋር ሀቅም፣ እውነትም፣ የትግል ባለቤትነትም፣ ዕውቀትም፣ አልፎሞ አሁን ደግሞ ኢሳትም ‘የእኔ’ ብቻ ነው” ባዩ የበዛበት ዘመን ላይ ስለሆንን፣ ነውር ውስጥ እየገቡ እኛን ምላሽ እንድንሰጥ፣ ህዝብም እንዲያዝን የሚያስገድዱን ማናቸውም ወገኖች ሁሉ በድጋሚ፣ ባለፈው እንደሆነው ስም ወደማንሳትና ጭቃ መወራወር እንደተገባው እንዳይሆን በጥብቅ ለማሳሰብ በግሌ እወዳለሁ።

    እውነት ያወጣሀል እንደሚባለው ሃቁን፣ ሂደቱን፣ እውነቱን በዝርዝር ለማውጣት ምንም የምንቸገርበት፣ የምናፍረበትም፣ ለማንም ለምንም ኣንደማንመለስ፣ እንደ አንዳንዶች “ቅጥረኛ’ ሳንሆን 26 ዓመታት ለኢትዮጵያ ህዝብ ፍትህን፣ ነጻነት፣ ለማምጣት ሁለንተናዊ ትግል ያደረግን፣ ሁሉንም ነጋራችንን የሰጠን፣ ከማንም ምንም የማንፈልግ ግለሰቦች እንደምንገኝበት ለህሊናችን ያደርንና ይህንኑ ይዘን እስከ ዕለተ ሞታችን እንደምንቀጥልም ሆዳቸው የሚያውቁ፣ ነገር ግን ይህን ርካሽ ተግባር የትም የማያደርሳቸው ግለሰቦች እንዲያስቡበት፣ ወደ ህሊናቸው እንዲመለሱ በግሌ በጥብቅ ለማሳሰብ እወዳለሁ። ለሁሉም ጎራ ስናሳስብ፣ በግልም፣ በቡድንም፣ በአደባባይ ስም ሳይጠቀስም ለሁለት ሳምንታት እንደተጻፈውና ፣ ለበርካታ ወራት ኢሳት ውስጥ የተፈጠሩ ችግሮችን ለመፍታት ጥረት ስናደርግ እንደከረምነው።

    አቶ ነአምን ዘለቀ የኢሳት የሥራ አስፈጻሚ ቦርድ አባል (በግል)

Viewing 3 posts - 1 through 3 (of 3 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.