Search Results for 'ገዱ አንዳርጋቸው'

Home Forums Search Search Results for 'ገዱ አንዳርጋቸው'

Viewing 12 results - 1 through 12 (of 12 total)
  • Author
    Search Results
  • Semonegna
    Keymaster

    ፀደይ ባንክ ጠቅላላ ተቀማጭ ገንዘቡ 24.5 ቢሊዮን ብር መድረሱን ገለጸ፤ 1.5 ቢሊዮን ብር ማትረፍ ችሏል

    ባሕር ዳር (ሰሞነኛ ኢትዮጵያ) – ፀደይ ባንክ የባለ አክሲዮኖች 1ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔውን በባሕር ዳር ከተማ ተካሂዷል። የፀደይ ባንክ በ2014 የሒሳብ ዓመት ጠቅላላ ተቀማጭ ገንዘቡ 24.5 ቢሊዮን መድረሱን የባንኩ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ገልጸዋል።

    በ2014 ዓ.ም ባንኩ ከተለያዩ መለኪያዎች አንፃር አበረታች ውጤት እንዳስመዘገበም አቶ ገዱ የተናገሩት። አያይዘውም የባንኩ ተቀማጭ ገንዘብ በ12 በመቶ አድጎ 24.5 ቢሊዮን ጠቅላላ ተቀማጭ ገንዘብ መድረሱንም ገልጸዋል።

    ሰኔ 2020/21 በተደረገ ሪፖርት ባንኩ 38.9 ቢሊዮን ብር ካፒታል እንዳስመዘገበና 9.5 ቢሊዮን ብር ጠቅላላ የተጣራ ካፒታል ማካበቱንም አንስተዋል።

    ባንኩ የቁጠባ መጠኑን 28.1 ቢሊዮን ብር ያደረሰ ሲሆን፤ በ2014 የሒሳብ ዓመት 1.5 ቢሊዮን ብር ጠቅላላ ትርፍም አግኝቷል ብለዋል። ካለፈው የሒሳብ ዓመት ጋር ሲነፃፀር በ29 በመቶ እድገት አሳይቷል የተባለ ሲሆን ለበርካታ ዜጎችም የብድር አገልግሎት መስጠት መቻሉም ተነስቷል።

    አቶ ገዱ በሪፖርታቸው ካቀረባቸው ነጥቦች ዋና ዋናዎቹ፦

    • የፀደይ ባንክ እስከ ፈረንጆቹ ሰኔ 2022 አጠቃላይ ሀብቱ 44 ቢሊዮን ብር ደርሷል።
    • ጠቅላላ ካፒታሉ 11 ቢሊዮን ብር ነው።
    • ጠቅላላ የተከፈለ ካፒታል7 ቢሊዮን ብር ነው።
    • የባንኩ ጠቅላላ ተቀማጭ ገንዘብ5 ቢሊዮን ብር ደርሷል። ይህም ከባለፈው ዓመት ከነበረበት በ12 በመቶ እድገት አሳይቷል።
    • ባንኩ የእቅዱን 94 በመቶ ማሳካት ችሏል።
    • የባንኩ ጠቅላላ የብድር ክምችት6 ቢሊዮን ብር ደርሷል።
    • የብድር መጠኑንም በ29 በመቶ አሳድጓል።
    • ባንኩ በበጀት ዓመቱ ለተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች1 ቢሊዮን ብር አበድሯል።
    • ፀደይ ባንክ 5 ቢሊዮን ብር ወጭ ማድረጉም በሪፖርቱ ተመላክቷል።
    • በ2014 የሒሳብ ዓመት 5 ቢሊዮን ብር ትርፍም አስመዝግቧል፤ የ2015 የሒሳብ ዓመት ትርፉን ወደ 1.66 ቢሊዮን ብር ለማሳደግ አቅዷል።
    • ትርፉ ካለፈው የሒሳብ ዓመት ጋር ሲነጻጸር 3 በመቶ ማደጉን የቦርዱ ሰብሳቢ አቶ ገዱ ገልጸዋል።

    ባንኩ በቀጣይ ከ100 በላይ ቅርንጫፎችን በመክፈት የአገልግሎት አድማሱን እንደሚያሰፋ ነው የተገለጸው። ፀደይ ባንክ ሀገር ችግር ውስጥ በገባችበት ወቅት 100 ሚሊየን ብር ወጭ በማድረግ ለወገን ደራሽነቱን አስመስክሯል። እንደሀገር የተከሰተውን የዋጋ ንረት ለመቋቋምም አጥብቆ ይሠራል ነው የተባለው።

    በአጠቃላይ 471 ቅርንጫፎችን በማቀፍ በብድርና ቁጠባ ተቋምነት (የአማራ ብድርና ቁጠባ ተቋም) ሲንቀሳቀስ ቆይቶ በቅርቡ ወደ ባንክ ተቋምነት የተሸጋገረው ፀደይ ባንክ፥ በአሁኑ ሰዓት ከ150 በላይ ቅርንጫፎቹ ውስጥ ከ12,200 በላይ ሠራተኞችን ቀጥሮ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል። ከዚህ በተጨማሪም አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ 36 ወለሎች ያሉት ዋና ቅርንጫፍ እያስገነባና፥ ግንባታውም በ2015 የሒሳብ ዓመት ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተዘግቧል።

    ንግድና ኢንዱስትሪ ነክ ዜናዎች ― ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ፀደይ ባንክ

    Anonymous
    Inactive

    የአቶ ሽመልስ አብዲሳ የሚስጥር ንግግር
    (ሙሉሸዋ አንዳርጋቸው)

    ኢትዮ 360 አቶ ሽመልስ አብዲሳ የዛሬ 7 ወር ገደማ በከፍተኛ ሚስጥር ይጠበቅ ብሎ በኦሮምኛ በስብሰባ ላይ የተናገረውን የኦሮሙማ ፕሮጄክት ለሕዝቡ ሰሞኑን ለቆታል

    መረጃውን ለኢትዮ 360 ማን ለምን እንዴት ሰጠ የሚለውን ለጊዜው ወደጎን ትተን፥ ኢትዮ 360 ከተወሰኑ ሰዎች ጋር ተማክረው የኢትዮጵያን ህልውና ግምት ውስጥ በመክተት ነገሮች እስኪረጋጉ መረጃውን ከመልቀቅ በመቆጠባቸው ሊመሰገኑ ይገባል። ይሄ ነው በተግባር ኢትዮጵያን ከሁሉም በላይ ማስቀደም። እንደ ጋዜጠኞች መረጃውን ማግኘት መቻላቸውም በራሱ በተጨማሪ ሊያስመሰግናቸው ይገባል።

    ወደ ሽመልስ ንግግር ፍሬ ነገር ስንገባ፥ አነ ሽመልስ አብዲሳ እና በጥቅሉ የኦሮሙማ አራማጆች ምን እንደሚያስቡ ማወቅ ተገቢውን የትግል ስልት ለመቀየስ በእጅጉ ይረዳል። ከዚህ በፊት ኦቦ ለማ መገርሳ ስለ ዲሞግራፊ ሃሳባቸው፣ አያቶላ ጃዋር ስለ 2ኛው የቄሮ ስውር መንግሥት፣ አሁን ደግሞ ሽመልስን በዚህ ረገድ እናመሰግናቸዋለን።

    ከዚህ ቀጥዬ የሽመልስን ንግግር ልፈትሸው እሞክራለሁ። እነ ሽመልስ አብዲሳ እና ኦሮሙማ አራማጆች ምን እንዳሰቡና ምን እንደሚፈልጉ ለሁላችንም ግልጽ ነው፤ ነገር ግን እግረ መንገዴን ሩቅ አሳቢ ቅርብ አዳሪ መሆናቸውን ለማሳየት እሞክራለሁ። መደስኮርና በተግባር ማሳካት ትልቅ ልዩነት አላቸው።

    1. በመጀመርያ ይሄ ዲስኩር የተደረገው የዛሬ 7 ወር ገደማ መሆኑን ልብ እንበል። Fast forward ዛሬ ላይ ባጭሩ ኦሮሙማ አራማጆች ላይ የነበረው እንዳልነበረ ሆኗል። የ2ኛው መንግሥት መሪያቸው ጃዋር ታስሯል፤ ኦ ኤም ኤን (OMN) የሀገር ቤት መርዛማ ስርጭቱ ተዘግቷል፤ ቀላል የማይባሉ የኦሮሙማ አራማጆች ታስረዋል፤ የዲሞግራፊ ቅየሳ መሃንዲሱ ኦቦ ለማና የለገጣፎ/ሱሉልታ/ሰበታ አፈናቃይዋ ጠቢባ ሀሰን ሳይቀሩ ከፓርቲው ታግደዋል። ከዚህ በፊት ብዙ ጊዜ አባ ገዳዎች ከብት እያረዱ ሊያስማሟቸው ቢሞክሩም፥ ዛሬ ላይ የኦሮሙማ አራማጆች እርስ በእርስ ከመጨራረስ ምንም ምድራዊ ኃይል የሚያስቆማቸው ያለ አይመስልም። ዛሬ ላይ ለዐቢይ ከጃዋር በላይ፣ ለጃዋር ከዐቢይ በላይ ጠላት ከየትም አይመጣም። መሬት ላይ ያለው ሃቅ ይሄ ነው።
    2. ሽመልስ አብዲሳ እኛ ነን ትህነግን (የትግራይ ሕዝብ ነፃ አውጪ ግንባር) በቁማር ጨዋታ ያባረርነው የሚለውን እስቲ እንፈትሸው።

    በረከት ስምዖን በቶሎ ካልተቀየርን አደጋው የከፋ ነው ብዬ ስለፈልፍ አልሰማ ብለውኝ፤ የጎንደር አመጽ ሲጀመር የኢህአደግ አመራሮች የምር መሆኑ ዘግይቶም ቢሆን ገባቸው አለ። በሕወሃት የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል የተጻፈው የኢህአዴግ የቁልቁለት ጉዞ መጽሐፍ ላይ የገዱ አንዳርጋቸው ቡድን ከትህነግ ጋር ለረጅም ጊዜ ፊት ለፊት ሲጋፈጥ እንደነበር ቀን፣ ቦታና አጀንዳ ጠቅሶ ያስረዳል። ዐቢይ ከመመረጡ በፊት የአማራ ሚዲያ ከትህነግ ቁጥጥር ውጪ ወጥቶ ተደማጭ ሚዲያ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው። ቴዲ አፍሮ በአዲስ አበባ በትህነግ የተከለከለውን ኮንሰርት ባህር ዳር በነጻነት ያውም በኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ አሸብርቆ ማድረጉን እናውቃለን። ባህር ዳር እነ ለማ መገርሳን የጋበዛቸው፣ በሰላምም ቆይተው በሰላም እንዲመለሱ ያደረገው የገዱ አንዳርጋቸው ቡድን ነው። በትህነግ እነ ለማን ለማሰር ታስቦ ደመቀ እምቢ ብሎ ማስቀረቱን ሰምተናል።

    ጥሬ ሃቁ ይሄ ከሆነ እነ ሽመልስ ቁማር ከተጫወቱ፥ ባለቀ ሰዓት መላው የኢትዮጵያ ሕዝብና ከውስጥ ደግሞ የገዱ ቡድን በዋናነት ገዝግዞ የጣሉትን ትህነግ፣ በቁማር ጨዋታ የገዱን ቡድን በልጠው ወደ አራት ኪሎ ቤተ መንግሥት መግባታቸው ነው። የገዱ ቡድን ትልቁ ድክመቱ ባህር ዳር ከአዲስ አበባ ርቆ ተወሽቆ፣ ከመሃል ሀገር ስነ ልቦና መራቁና ስልጣን ይገባኛል የሚል ስነ ልቦና ስላልነበረው ነው።

    1. አቶ ሽመልስ አብዲሳ ስለ ኦሮሙማ ፕሮጀክት የመጀመሪያው ተናጋሪ አይደሉም። በእርግጠኝነት የመጨረሻም ተናጋሪ አይሆኑም። ኦዴፓን (ኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ) ጨምሮ የኦሮሞ ፓርቲዎች በኦሮሙማ አራማጆች የተሞሉ ናቸው።

    አቶ ሽመልስ ከዚህ ቀደም የማናውቀውን ነገር ብዙም አልነገሩንም። ክብርና ምስጋና በዋናነት ለእስክንድር ነጋ ይግባውና፥ የኦሮሙማ ፕሮጀክትን ከስር ከስር እየተከታተለ አዲስ አበባ ውስጥ ስር እንዳይሰድ አጋልጧቸዋል። እስክንድር ተወልዶ ባያነሳ ብዕር፣ አዲስ አበባ ይሄኔ የኦሮሙማ መቀለጃ ትሆን ነበር። እስክንድርን ለምን እንዳሰሩት ይገባናል።

    1. የአቶ ሽመልስ አብዲሳ ንግግርና የኦሮሙማ አራማጆች ፍላጎት ላይ ምንም ብዥታ የለንም። ቢችሉ አማርኛን ሙሉ ለሙሉ ቢያጠፉና ኦሮምኛ ብቻ ቢነገር ደስተኞች ናቸው፤ ቅዠታቸው እዚህ ድረስ ነው። ሽመልስ አማርኛ ቋንቋ እንዲሞት፣ ኦሮምኛ ደግሞ እያደገ እንዲመጣ እንዳደረጉ፥ ኦሮምኛ ቋንቋ በ22% እንዳሳደጉ፣ በቤንሻንጉል፣ በጋምቤላ፣ በሀረሪ፣ በሶማሌ የኦሮሞኛ ቋንቋ እንዳሳደጉ ይናገራል። ለሽመልስ ጥያቄዬ ይሄን ሁሉ ያደረጉት በዚህ 2 ዓመት ውስጥ ነው? የመረጃው ምንጩ ምንድን ነው? ማስረጃ እስኪጠቀስ ድረስ እንደ ኦሮሙማ ምኞት ቢወሰድ የሚመረጥ ይመስለኛል።

    አቶ ሽመልስ አብዲሳ ብልጽግና ውስጥ የኦዴፓ ውክልና በምንወክለው ሕዝብ ብዛት መጠን እንዲሆን አድርገናል ይላል። በዚህ የተነሳ ኦሮሞ ያልሆነ ወይም ኦሮሞ ያልፈለገው ሊቀ-መንበርም ሆነ ምክትል ሊቀ-መንበር እንዳይወጣ አድርገን ብልጽግናን ሠርተናል ይላል። ሲጀምር ፓርቲዎቹ በሚወክሉት ሕዝብ ብዛት መጠን ድምጽ መኖሩን ከትህነግ በቀር ሁሉም ፓርቲዎች ይፈልጉትታል። ሲቀጥል ሽመልስ 40% ድምጽ አለን የሚለውን እውነት አድርገን እንውሰደውና፥ በየትኛው ቀመር ይሆን የተቀሩት 60% ድምፅ ካላቸው ፍላጎት ውጪ ኦዴፓዎች የፈለጉትን እንዲያደርጉ የሚያስችላቸው? ወይስ የብልጽግና ደንብ ኦዴፓ ያልፈቀደው ሊቀ-መንበር ወይም ምክትል ሊቀ-መንበር መሆን እንደማይችል “veto power” ለኦዴፓ ይሰጣል? እንዴት አርገው ነው 30% የሕዝብ ብዛት ኢትዮጵያን በኦሮሙማ ቅድ መስፋት የሚቻልው? ሌላው ጉራጌው፣ አማራው፣ ሱማሌው፣ ደቡቡ፣ ትግሬው እሺ ብሎ ይገዛል ወይ?

    አቶ ሽመልስ አብዲሳ በአዲስ አበባ በሕጋዊ መንገድ ይሁን ከሕግ ውጪም የኦሮሞን ቁጥር እንጨምራለን ይላል። መጀመርያ የለማ በአዲስ አበባ ዙርያ ሰፋሪዎች፣ ቀጥሎ ታከለ ኡማ በዚህ ጉዳይ ላይ ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ መሬት ላይ ምን እያደረገ እንደሆነ እናውቃለን። አቶ ሽመልስ ምንም አዲስ ነገር እዚህ ላይ አልነገረንም።

    አዲስ አበባን ሌሎች ሁለት ወይም ሦስት ተጨማሪ የፌዴራል መቀመጫ ከተሞች በመጨመር እናዳክማታለን አለ። አቶ ሽመልስ አብዲሳ አዲስ አበባን ለማዳከም መወሰን ማለት “ፊንፊኔ ኬኛ” ቀረ እያለን እንደሆነ ገብቶታል? አዲስ አበባን ማዳከም እንደ ማውራት ቀላል ይሆን? ከተጨማሪ የፌዴራል ከተሞች ውስጥ ለምሳሌ አንዱ ናዝሬት የሁሉም ኢትዮጵያኖች ከተማ ቢሆን፣ “ናዝሬት ኬኛ” በኋላ ማለት ሊጀምሩ ይሆን?

    አቶ ሽመልስ አብዲሳ በአሁኑ ወቅት በልበ-ሙሉነት እንደ ኦሮሚያ እየለማ ያለ ቦታ የለም ይላል። Really? የቄሮ እብደት ከጀመረ በኋላ ፋብሪካዎች በኦሮሞ አካባቢ ሲቃጠሉና ሲዘጉ አይደል እንዴ እያየን የለነው? አሁን እንኳን ሻሸመኔ፣ ዝዋይ፣… እንዳልነበሩ ሆነው አልወደሙም? ስንት ዓመት ይፈጅ ይሆን የተቃጠሉትን ከተሞች ያሉበት ቦታ ለመመለስ? በተጨማሪ “ፊንፊኔ ኬኛ” ብለው የኦሮሞ ባህል ማዕከል፣ የኦሮሞ መሥሪያ ቤቶች፣ቢሮዋች፣…. ሸገር ላይ ነው የሚሠሩት። ታዲያ እንዴት አድርገው ነው አዱ ገነትን መግደል የፈለጉት? በኦሮሞ አካባቢ አለመረጋጋትና በኦሮሙማ አራማጆች ድንቁርና እየተመነደጉ ያሉት ከተሞች ሌሎች ናቸው። በስታትስቲክስ የተደገፈ መረጃ እዚህ ላይ ለሽመልስ ማቅረብ ይቻላል።

    1. ማጠቃለያ
      የሽመልስና የቢጤዎቹ ኦሮሙማ አራማጆች ሴራ በንቃት ሁላችንም መከታተልና ማጋለጥ አለብን። ለሴራቸውም ማክሸፊያ በሕብረት መፈለግ አለበት። በተለይ ሌሎቹ የብልጽግና አባሎች ይሄንን የእነ ሽመልስን የኦሮሙማ ቅዠት በዋዛ ፈዛዛ ሊያልፉት አይገባም። ከስር ከስር እነ ሽመልስን እየተከታተሉ ማጋለጥና ማርከሻ መፈለግ አለባቸው። የእነ ሽመልስን እጅና እግር ለማሰር የብልጽግናን ደንብ መለወጥ ካለባቸው አይናቸውን ማሽት የለባቸውም። እንዲህ በማድረግ ነው የኦሮሙማ ቅዠታሞችን እሩቅ አሳቢ፣ ቅርብ አዳሪ አድርገን የምናስቀረው።

    ሙሉሸዋ አንዳርጋቸው

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ፦ በሰሞነኛ ድረገጽ የአማርኛ ፎረም (semonegna.com/forums) ላይ የሚገኝ ማንኛውም ጽሑፍ የጸሐፊውን አመለካከት ብቻ የሚያንጸባርቅ ሲሆን፥ ጽሑፉ የሰሞነኛ ኢትዮጵያንንም ሆነ የተሳታፊዎችን አመለካከትና ምልከታ ላይወክል ይችላል።

    አቶ ሽመልስ አብዲሳ

    Semonegna
    Keymaster

    የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የውሃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአሜሪካ የግምጃ ቤት ዲፓርትመንት ሴክሬታሪ በየካቲት 21 ቀን 2012 ዓ.ም. (እ.ኤ.አ. በ28 February 2020) የታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በተመለከተ ኢትዮጵያ ያልተሳተፈችበትን ስብሰባ ተከትሎ የወጣውን ጋዜጣዊ መግለጫ በከፍተኛ ቅሬታ ተመልክተውታል።

    ስብሰባው የተካሄደው ኢትዮጵያ አስቀድማ ለግብጽ፣ ለሱዳን እና ለአሜሪካ ስብሰባው ለሌላ ጊዜ እንዲተላለፍ አሳውቃ እያለ ነው።

    የግድቡ ባለቤት የሆነችው ኢትዮጵያ በመርሆዎች መግለጫ ስምምነቱ መሰረት የግድቡን ሙሌት ከግንባታው ትይዩ በፍትሐዊ እና ምክንያታዊ አጠቃቀም እና ጉልህ ጉዳት ያለማድረስ መርሆዎች መሠረት የምታከናውን ይሆናል።

    ኢትዮጵያ የግድቡን የመጀመሪያ ሙሌት እና የውሃ አለቃቅ መመሪያ እና ደንብ ለማዘጋጀት የሚደረገው ድርድር ተጠናቋል በሚል የተሰጠውን መግለጫ አትቀበልም።

    በዋሽንግተን ዲሲ የግብጽ ዐረባዊት ሪፐብሊክ ፈርሞበታል የተባለው “ረቂቅ” የሦስቱ ሀገራት የድርድርም ሆነ የሕግ እና ቴክኒክ ቡድኖች ውይይት ውጤት አይደለም። የቴክኒክ ጉዳዮች ድርድሩም ሆነ የሕግ ማዕቀፍ ዝግጅቱ ላይ የሚደረገው ድርድር አልተጠናቀቀም።

    ኢትዮጵያ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ሙሌት እና የውሃ አለቃቅ መመሪያ እና ደንብ የሚዘጋጀው በሶስቱ ሀገራት ብቻ እንደሆነ አቋሟን ቀድማ አሳውቃለች።

    ኢትዮጵያ ግብጽ እና ሱዳን በሚያውቁት እና በተስማሙበት እንዲሁም በመርሆዎች መግለጫ ስምምነት መርህ አንቀጽ ስምንት አድናቆታቸውን በሰጡት ሂደት መሠረት ሁሉንም የግድብ ደህንነት የሚመለከቱ ጉዳዮች በዓለምአቀፍ የባለሙያዎች ቡድን ምክረ ሃሳብ መሰረት የተሰጡትን ምክረ-ሃሳቦች መፈጸሟን ትቀጥላለች።

    የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ሙሌት እና የውሃ አለቃቅ መመሪያ እና ደንብን ለማዘጋጀት ቀሪ መሰረታዊ ልዩነቶችን ለመፍታት ኢትዮጵያ ከግብጽ ዐረባዊት ሪፐብሊክ እና ከሱዳን ሪፐብሊክ ጋር የጀመረችውን ሂደት ለመቀጠል ቁርጠኛ ናት።

    ከዚሁ ጉዳይ ጋር በተያያዘ፥ የኢትዮጵያ መንግስት ሕዳሴ ግድብን በተመለከተ ብሔራዊ ጥቅምን የሚነካ ድርድር እንደማያደርግ የሚስትሮች ም/ቤት አስታወቀ።

    ታላቁ የሕዳሴ ግድብን የሚመለከት ማንኛውም ነገር የኢትዮጵያን ፍላጎትና ጥቅም በሚጠብቅ መልኩ ብቻ እንደሚከናወን የሚስትሮች ምክር ቤት ገልጿል።

    ምክር ቤቱ በዛሬው ዕለት ባካሄደው ስብሰባ ሕዳሴ ግድብን በተመለከተ ብሔራዊ ጥቅምን የሚነካ ድርድር የኢትዮጵያ መንግስት እንደማያደርግ አስታውቋል።

    በዛሬው ዕለት ባካሄደው 80ኛ መደበኛ ስብሰባው ምክር ቤቱ የኮሮና ቫይረስ መከላከል ስራዎችን የሚከታተል ስድስት አባላት ያሉት ብሔራዊ የሚኒስትሮች ኮሚቴ ማቋቋምን ጨምሮ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል።

    የብሔራዊ የሚኒስትሮች ኮሚቴው ስድስቱ አባላትም የሰላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል፣ የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ፣ የገቢዎች ሚኒስትር ወይዘሮ አዳነች አቤቤ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገዱ አንዳርጋቸው፣ የትራንስፖርት ሚኒስትር ወይዘሮ ዳግማዊ ሞገስ እና የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሊያ ታደሰ ናቸው።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    Ethiopian government's statement regarding the negotiations on GERD የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ

    Semonegna
    Keymaster

    “ሀገራችንን ኢትዮጵያን አጣብቆ የያዘውን መንግሥታዊ ኃይል ቢዳከም፣ እነዚህ የታሪክም የፓለቲካ መሠረት ያላቸው ልዩ ልዩ ቅራኔዎች በየቦታው ቢፈነዱ፣ በሕዝብ መካከል የእርስ በእርስ ግጭቶች ቢበራከቱ በብዙ አቅጣጫና ውስብስብ የብሄር ቅራኔዎች፣ ሌሎች ፓለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና፣ ማኅበራዊ ችግሮች የተጠመደች ሀገራችንና የኢትዮጵያ ሕዝብ ወዴት ሊወስዱ እንደሚችሉ ከግምት ማስገባት አስፈላጊና ወሳኝ ይሆናል።”

    ሳይቃጠል በቅጠል
    በጋራ ሀገራችን ላይ ያጠላውን የመበታተንና የሕዝብ ለሕዝብ እልቂት ለመቀልበስ የመፍትሄዎች አካል እንሁን!
    (ነአምን ዘለቀ)

    በሀገር ውስጥ ለምትገኙ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ በሙሉ፣ የአማራ፣ የኦሮሞ፣ የልዩ ልዩ የቋንቋና ባህል ማኅበረሰቦችን ለምትወክሉ ልሂቃንና ምሁራን፣ የሃይማኖትና የፓለቲካ ድርጅቶች መሪዎች፣ በሀገር ውስጥና በዲያስፓራ ለምትገኙ ኢትዮጵያውያን ወገኖች፣ አክቲቪስቶች፣ የሚዲያ ባለሙያዎችና የማኅበራዊ ሚዲያ ተሳታፊዎች በሙሉ፦

    ሰሞኑን በአገራችን በኢትዮጵያ ልዩ ልዩ አካባቢዎች በደረሱ ጥቃቶች ሳቢያ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰላማዊና ንጹሃን ወንድሞች፣ እህቶች፣ አባቶች፣ እናቶች፣ አዛውንት፣ ሕጻናት ሳይቀሩ፣ የሃይማኖት አገልጋዮች ጭምር በግፍ ተገድለዋል፣ ቆስለዋል፣ ተፈናቅለዋል። አብያተ ክርስቲያናትና መስጊዶችም ተቃጥለዋል። ብዙ ግፍ ተፈጽሟል። ሕይወታቸውን ላጡ ንጹሃን ዜጎች ወገኖቼና ለቤተሰቦቻቸው፣ ለዘመዶቻቸው በአጠቃላይ ለኢትዮጵያ ሕዝብ የተሰማኝን ጥልቅ ሃዘን እገልጻለሁ።

    የሰው ልጆችን ከእንስሳት የሚለየን ረቂቅ ሕሊናን፣ ርሕራሄን፣ ሰብዓዊነት ነው። ከአራት አስር ዓመታት በላይ በተሰበኩ፣ ላለፉት በርካታ ወራት ደግሞ በተካረሩና ጥላቻን መሠረት ባደረጉ የተዛቡና ቁንጽል የታሪክና የፓለቲካ ትርክቶች ሳቢያ ለደረሰው እጅግ አሳዛኝ ጥቃትና የኢትዮጵያውያን ሕይወት መቀጠፍ የራሳቸው ሚና እንደነበራቸው የሚያጠያይቅ አይደለም።

    እነዚህን አሰቃቂና ዘግናኝ ድርጊቶች የፈጸሙ ሁሉ ተጠያቂ መሆን አለባቸው፣ መንግሥት እነዚህን ኢ-ሰብዓዊ ወንጀል የፈጸሙ ግለሰቦች በሕግ ፊት ማቅረብ አለበት።

    ከጥቂት ወራት በፊት በልዩ ልዩ ሚዲያዎች በተደጋጋሚ ሃሳቤን ለመግለጽ እንደሞከርኩት ከአንዳንድ የኦሮሞና የአማራ፣ የሕብረ ብሔር ኢትዮጵያውያን ልሂቃን፣ እንዲሁም በልዩ ልዩ ሚዲያዎችና ሶሻል ሚዲያዎች፣ አክቲቪስቶች፣ የብሔርም የሕብረ ብሔርም የፓለቲካ ድርጅት መሪዎች ሲሰነዘሩ የቆዩ ትንኮሳዎች፣ ጠብ አጫሪ ተግባራት፣ እንቅስቃሴዎች በልዩ ልዩ ማኅበረስቦች መካከል ለዘመናት የነበረውን ተጋምዶ፣ ትስስር፣ ትብብር፣ ፍቅር፣ ወልዶ ተዋልዶ አብሮ መኖር የነበረውን እንዳልነበር እያራከሰ እያኮሰሰ የደረሰበትን አሳዣኝ ዝቅጠት ከንፈር እየመጠጥን ስንታዘብ ሰንብተናል። በእኔ እበልጥ እኔ እበልጥ፣ እልህ ተጋብተውም እንዱ እንዱን ለመብለጥ የቃላት ጦርነቶችና፣ ከሁሉም ጎራ የሚሰራጩ የተዛቡ ትርክቶች፣ በሶሻል ሚዲያ የቃላት ሰይፍ መማዘዝ፣ ጥላቻን በሕዝብ መካከል መርጨት በስፋት ሲደረጉ የቆዩበት ሁኔታ፣ በስፋት በተሰራጩ የታሪክም የፓለቲካም የተዛቡ ትርክቶች፣ እጅግ ሲጋነኑ የነበሩ ቁንጽል መረጃዎች፣ ፊው የተዛመቱ የፈጠራ ወሬዎችን ጨምሮ በማኅበረሰቡ መካከል፣ በተለይም ለዘመናት ኢትዮጵያን እንደ ሀገር በመገንባት ትልቅ ድርሻ ያላቸውን በኦሮሞና የአማራ ሕዝቦች መካከል ትልቅ ክፍተት እንዲፈጠር፣ የተወሰኑ የሕዝብ ክፍሎች ውስጥም ጥላቻ አየሰፋ፣ እየተጠናከረ እንዲመጣ አፍራሽ አሰተዋጽኦ በማድረግ ከሰሞኑ ለተቀሰቀስው ከጥላቻ የመጣ ጥቃት፣ እጅግ አሳዛኝና እሰቃቂ ድርጊቶች ሚና እንደነበራቸው መታወቅ ያለበት ይመስለኛል።

    በተለይ በሕዝብ ቁጥር ትልቅ በሆኑት ብሔሮች በአማራና በኦሮሞ መካከል ቅራኔን፣ ጥላቻን፣ ጥርጣሬን የሚያጠናክሩ ትንኮሳዎች፣ በየመድረኩ፣ በጀርመን በእሥራኤል፣ በሌሎችም የዲያስፓራ የተቃውሞ ሰልፎች የተሰነዘሩ የጥላቻ፣ እንዱ ሌላውን በንቀት የሚያንኳስሱ ቃላቶችና ድርጊቶች፣ የተሳሳቱና የተዛቡ ትርክቶች በስፋት ሲካሄዱ እንደነበር የሚካዱ ሊሆኑ አይችሉም። ከዚህ አፍራሽና እጅግ ስስና ተሰባሪ የሆነውን የሀገሪቱን ሁኔታ፣ ተዋናዮቹ ግለሰቦች ብቻ ሳይሆኑ፣ ከግለሰቦች ጀርባ የሚገኙ የዶ/ር መረራ ጉዲናን አጠቃቀም ለመዋስ “የሚጋጩ ህልሞች” እንዲሁም ቅዠቶች፣ ሃሳቦችና ትርክቶች፣ በእነዚህ ትርክቶች ዙሪያም የተሰለፉ ሚሊዮኖች መኖራቸውን እነዚህ ሚዲያዎች፣ ሶሻል ሚዲያዎችና፣ አክቲቪስቶችና የፓለቲካ ልሂቃን ከግምት ውስጥ ሊያስገቡት አልቻሉም፤ ለማስገባትም አልተፈለገምም ነበር።የሴራ መልዕክቶች፣ ባልተጣሩና ለማጣራትም ምንም ጥረት ባልተደረገባቸው በዜና መልክ የሚቀርቡ የፈጠራም የተጋነኑም ወሬዎች በተለይ ሀገር ውስጥ በመሬት ላይ ለሚገኘው የገፈቱ ቀማሽ ሰላማዊ ሕዝብ የማይበጀው መሆኑ መረዳት ያስፈልግ ነበር።

    ያደራጁት ኃይል በእጃቸው በሌለበት፣ አማራጭ ራዕይና ፕሮግራም ባላዘጋጁበት፣ አገርን ሊያረጋጋ፣ ሕዝብን ከጥቃት ሊከላከል የሚችል ወታደራዊና የጸጥታ ኃይሎችን ባላሰለጠኑበት፣ በማይመሩበት፣ ለዚህ ደግሞ መንግሥታዊ አቅሙም፣ ችሎታም፣ ስትራቴጂካዊ ጥናቶች ሆነ ቅደመ ዝግጅቶች ማንም ምንም በወጉ ባላሰቡበት፣ ባልተዘጋጁበት ሁኔታ በስልጣን ላይ የሚገኘውን ብዙ ተግዳሮቶች የገጠመው ነገር ግን ለውጥን ለማምጣት ደፋ ቀና ሲል የቆየውን የለውጡን አመራር በከፍተኛ ርብርብ ለማዋከብና ለመሸርሸር የተሄደበት ርቀት ትልቅ ታሪካዊ ስህተት ይመስለኛል።

    ሀገራችንን ኢትዮጵያን አጣብቆ የያዘውን መንግሥታዊ ኃይል ቢዳከም፣ እነዚህ የታሪክም የፓለቲካ መሠረት ያላቸው ልዩ ልዩ ቅራኔዎች በየቦታው ቢፈነዱ፣ በሕዝብ መካከል የእርስ በእርስ ግጭቶች ቢበራከቱ በብዙ አቅጣጫና ውስብስብ የብሄር ቅራኔዎች፣ ሌሎች ፓለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና፣ ማኅበራዊ ችግሮች የተጠመደች ሀገራችንና የኢትዮጵያ ሕዝብ ወዴት ሊወስዱ እንደሚችሉ ከግምት ማስገባት አስፈላጊና ወሳኝ ይሆናል። እንደ ሀገር መኖር አለመኖር፣ እንደ ሀገር መቀጠል ወይንም አለመቀጠል የምንችልበት ወይንም የማንችልበት የታሪክ መጋጠሚያ ላይ ደርሰናል። በአንድ አካባቢ የሚጀመር እሳት፣ ወደ ሌላ አካባቢ ሊዛመት እንደሚችል ወደ ሰደድ እሳት ሊያድግ፣ ሊሸጋገር ወደሚችል ደረጃ እንደሚደርስ ብዙ እውቀትና ማሰብ የሚፈልግ አይመስለኝም። በሌላም በኩል ደግሞ የእርስ በእርስ ግጭቶች እየተቀጣጠሉ፣ አድማሳቸው እየሰፋ ሊሄድ እንደሚችል፣ በአንድ አካባቢ የተነሳ ግጭትና የግጭቱ ጥቃት ስለባ የሆኑ ወገኖች በሌላ አካባቢ በሚገኙ የአጥቂዎች ወገኖች ላይ የብቀላ ጥቃት፣ የብቀላ ብቀላ አድማሱ አየሰፋ፣ እየተዛመተ፣ ማንም ምድራዊ ኃይል ሊቆጣጠረው ወደማይችል ምድራዊ ሲኦል ሊለወጥ የማይችልበት ምክንያት አይኖርም።

    ውድ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ፦

    ዛሬ ትላንት አይደለም። ትላንት የሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢዎች፣ የአብዛኛው የዲያስፓራ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ትኩረትና የትግሉ ግብ፣ የትግሉም ዒላማ በሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ሲዘወር በነበረ ግፈኛና ጨካኝ አገዛዝ ላይ ያነጣጠረ እንደነበር የሚካድ አይደለም። ከጎንደር እስከ ሐረር፣ ከባሌ ዶሎ እስከ ወሎ፣ ከሐረር እስከ ባሕር ዳር የኢትዮጵያ ሕዝብ ከኦሮሞ እሰክ አማራው፣ ከጋምቤላ እሰከ ሶማሌ፣ ከአዲስ አባባ እስከ አምቦ ትግሉ ከመንግሥት ኃይሎች፣ ከጨቋኝና ግፈኛ ገዥዎችና የመጨቆኛ መሥራሪያዎቻቸው፣ ተቋማቶቻቸው ጋር ሲያፋፍም የነበረ፣ አለፍ ካለም የእነሱ ጥቂት ደጋፊዎች ላይ ያነጣጠረ እንደነበር የማይረሳ ነው።

    ዛሬ ግን ቅራኔው፣ ግጭቱ፣ ጥላቻው የጎንዮሽ በሕዝብ መካከል ሆኗል፤ በማኅበረሰቦች መካከል ሆኗል። ትልቁ አደጋ ይህ ከሰሞኑ የተከሰተውና ነጥሮ የወጣው እውነታ ከዚህ ጋር የተያያዘ መሆኑ የሚያጠራር፣ የሚያሻማ ሊሆን አይችልም። ዛሬ ቅራኔው ለዘመናት አብረው በኖሩ ማኅበረሰቦችና በሕዝብ መካከል መሆኑ ነው። ይህ እውነታ በስፋትና በጥልቀት በበርካታ የአገሪቱ አካባቢዎች የሚታይ እጅግ አደገኛ ሂደት መሆኑ ግልጽ አየሆነ ነው።

    ይህን ልዩና እጅግ አስጊ ሁኔታ ለመለወጥ ከፍተኛ ጥንቃቄ፣ ዘዴዎች፣ ብልሃቶች ይጠይቃል። መንግሥታዊ የማድረግ አቅም የመኖር አለመኖር ብቻ ሳይሆን የመንግሥት እርምጃዎች፣ የመንግሥት ድርጊቶች ሊፈጥሩ የሚችሉትን አሉታዊ የሆነ የአንድ ወይንም የሌላ ወገን የአጸፋ ምላሽ ለመቋቋም የሚያስችል፣ ያልተጠበቁ ትላልቅ አደጋዎች በሕዝብ ላይ እንዳይደርሱም እስቀድሞ ችግሮቹ በቀጥታ የሚመለከታቸውና ከችግሩ ጋር ተፋጠው የሚገኙ የመንግሥት መሪዎችና ልዩ ልዩ የመንግሥታዊ ተቋማት ሃላፊዎች ሊደረግ ብቻ የሚችል የቢሆንስ ትንታኔም የሚያስፈልገው ነው። የመንግሥት መሪዎች ወደ ስልጣን ያመጣቸው ፓርቲና ሕዝብ ውስጥ ያላቸው ቅቡልነት፣ ስትራቴጂካዊ አስተሳሰብ ዝግጁነት፣ በየጊዜው የሚፈተሽ ዕቅድና ይህንኑ የማስፈጸሚያ/የ ማድረግ አቅም የሚሰጡ ልዩ ልዩ የመሣሪያዎች ሳጥን በአግባቡና በብቃት ማዘጋጀትን የሚጠይቁ ናቸው። ድርብርብና በየደረጃው የሚከናወኑ ተግባራት ያሉበት ውስብስብ ሁኔታ ነው። በመንግሥት ብቻ ሳይሆን፣ በአገር ሽማግሌዎች፣ በሃይማኖት አባቶች፣ በልሂቃን፣ በልዩ ልዩ ኃይሎችና ባለድርሻዎች በጋራም፣ በተናጠልም ሥራዎችን ይጠይቃሉ።

    የኢትዮጵያን ሰላምና፣ ደህንነት፣ መረጋጋት የሚፈልጉ ዜጎች ሁሉ ይህን አስጊና አደገኛ በሕዝባችን ደህንነት፣ በሕዝባችን አብሮነት፣ በኢትዮጵያ ሃገራዊ ህልውና ላይ የተደነቀረ ከባድ አደጋ ለመሻገር ከተፈለገ ይህን አደጋ ከሚያባብሱ፣ ከሚቀጣጥሉ ቃላት፣ ቅስቀሳዎች፣ ቁንጽልና በቅጡ ያልታሰቡባቸው፣ ያልተጠኑም በርካታ የሀሰትም ወሬዎች፣ የተዛቡና በምንም መልኩ መቼም ሙሉና ሁለንተናዊ እይታን ሊሰጡ የማይችሉ ትርክቶች በሚዲያና በማኅበራዊ ሚዲያዎች ከማሰራጨት መቆጠብ የግድ ይሆናል። በምትኩ የሚዲያዎች ሚና ለኢትዮጵያ ሕዝብ ተስፋ መስጠት፣ ማኅበረሰቦች እንዲቀራረቡ የበኩላቸውን ሚና መጫወት ያለባቸው ይመስለኛል። ግጭት ሳይሆን ውይይት፣ ቅራኔን ሳይሆን መግባባት እንዲመጣ ገንቢ ጥረቶች ማድረግ የሁሉም የፓለቲካ ልሂቃንና የሚዲያዎች፣ በሀገር ቤትም በውጭ ሀገርም የሚገኙ የብሄርም የሕብረ ብሄርም ዓላማ ያነገቡ አክቲቪስቶች ታሪካዊ ሃላፊነት ነው ብዬ አምናለሁ። በተለይም እሳቱ የማይደርስባቸው፣ በእነሱም በቤተሰቦቻቸው፣ በዘመዶቻቸው ላይ ጭምር ሊደርስ የሚችል የማይመስላቸው በውጭም በሀገር ውስጥም የሚገኙ የየብሔሩ ልሂቃን፣ የየብሔሩና በሕብረ ብሔርም ኢትዮጵያዊነትና ዜግነት ፓለቲካ የተደራጁ አክቲቪስቶች ሁሉ ቆም ብለው ማሰብ የሚገባቸው ወቅት አሁን መሆኑን በጥብቅ ለማሳሰብ እፈልጋለሁ።

    የሚቀጥለው እሳት ወደ ሰደድ እሳት እንዳያመራ ሳይቃጠል በቅጠል እንዲሉ ለትላልቆቹ የፓለቲካ ልዩነቶች መፍትሄ ማፈላለግ ያስፈልጋል። የተጀመረው አዝጋሚና ብዙ ተግዳሮቶች የገጠመው የለውጥ ሂደት ከእናካቴው እንዳይቀለበስ ሁሉም የድርሻውን ማበርከት አለበት ብዬ አምናለሁ። ይህን አጋጣሚ ለመጠቀም ያቆበቆቡ፣ ይህን ሁኔታ ለመጠቀም ሰሞኑን በሀዘን የተመለከትነውን ጥቃት በማጦዝ፣ በማራገብ ጮቤ የረገጡ፣ ልዩ ልዩ ዘዴዎችንም በመጠቀም ከተለያዩ የፓለቲካም፣ የሚዲያም ተዋናዮች ጀርባም በመሆን ቅራኔዎችና ችግሮች እንዲሰፉ፣ እንዲባባሱ የእነማን ዘርፈ ብዙ ጥረት እንደሆነ የሚጠቁሙ በርካታ መረጃዎች በየጊዜው እንደሚያሳዩ ለአብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ ግልጽ ይመስለኛል። ከመሸጉበት ለማንሰራራት፣ ብሎም የኢትዮጵያን ሃገረ መንግሥት ማዕከል ዳግም ለመቆጣጠር ያላቸውን ቀቢጸ-ተስፋ ዕውን ለማድረግ፣ የለመዱትንም ግፈኛ መንግሥታዊ ሽብርና መንግሥታዊ ዘረፋ በመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ኪሳራ ለማስቀጠል ሙከራቸውን ከማድረግ ወደ ኋላ የማይሉ እኩይና ከታሪክ የማይማሩ ያረጁ ያፈጁ ከ21ኛው ክፍለ ዘመን የፓለቲካ አስተሳሰብ ጋር እራሳቸውን ማለማመድ፣ ካለፈው ወንጀሎቻቸውና ውድቀታቸው መማር የማይችሉ ድኩማን የፓለቲካ ድርጅች እንዳሉ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ፍንትው ብሎ የሚታይ ሃቅ ነው ብዬ እገምታለሁ።

    እነዚ ህይሎች የራሳቸውን ጥቅምና ያጡትን የበላይነትና ፈላጭ ቆራጭነት ከማየት በስቲያ፣ በሕዝብ ላይ ጭነው ከነበሩት የበላይነት ባሻገር ለሕዝብ መከራ፣ ለሰው ልጆች ጉስቁልና ቁብ የማይሰጣቸው ናቸው። የሚሊዮኖች ኢትዮጵያውያን ደምና እንባ ለ27 ዓመታት አንደ ጎርፍ እንዲፈስ ያደረጉት እነዚህ የፓለቲካ ዓመታት ይህን እኩይ ዓላማቸውን ለማሳካት የጋራ አገራችን ኢትዮጵያ አገራዊ ትርምስ ውስጥ ብትገባ ፈጽሞ የማይጨነቁበት መሆኑን ሲጀምሩም የተነሱበት የፓለቲካ ዓላማ፣ ታሪካቸው፣ እስካሁንም የቀጠሉበት አንደበታቸው፣ የተካኑበት መሰሪነትና ተንኮል ያረጋግጣል። “እኛ የኢትዮጵያ አዳኞች ነን” በሚል ሽፋንና ነገር ግን የማዕከላዊ መንግሥትን ሙሉ በሙሉ የመቆጣጠር ቀቢጸ-ተስፋቸው እሁንም በትዕቢትና በትምክህት ተወጥረው በሚያደርጉት እንቅስቃሴ አገራችንን ወደ ሁለንተናዊ ትርምስ ጎዳና ሊያስገባ የሚችል ዕድል እንዳንሰጣቸው የኢትዮጵያ ሕዝብ ሁሉ ነቅቶ መጠበቅ እንዳለበት በጽኑ አምናለሁ።

    የኢትዮጵያ ምድር ከጥንት ከሺህ ዓመታት በፊት ዛሬ የሚገኙ ሕዝቦች ያልነበሩበት፣ አንዱ በአንድ ዘመን ከደቡብ ተነስቶ ሌሎችን ማኅበረሰቦች አስገብሮ መሬት ሲይዝ፣ በሌላ ዘመን ሌላው ይህኑ አጸፋ ሲያደርግ፣ ሲስፋፋ፣ በአመዛኙ ደግሞ የየብሔሩ ገዢዎች፣ በዓለም ላይ እንደነበሩ ገዥዎች ሁሉ የተደረጉ ሂደቶች ናቸው። ሌሎች የዓለም ሃገሮች ከተመሠረቱበት የሀገራት ምሥረታ ሂደት ምንም የሚለየው የለም። ባርያ ፈንጋዩና አስገባሪው ደግሞ የአንድ ብሔር አንድ ቋንቋ የሚናገሩ ብቻም አልነበሩም። በልዩ ልዩ የታሪክ ምዕራፎች የየማኅበረሰቡ/ብሄሩ ንጉሶችና ገዢዎች፣ አስገባሪዎች፣ ተስፋፊዎች በመሆን ተፈራርቀዋል። የልዩ ልዩ ብሔሮች/ማኅበረሰቦች ገዢዎች ከመሃል ወደ ደቡብ፣ ከደቡባዊ ከምሥራቃዊ ኢትዮጵያ ተነስቶ እስከ መሃላዊ የዛሬዋ ኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን እስከ ሲሜናዊና ሰሜን ምሥራቃዊ የሀገሪቱ ክፍሎች በመዝመት በመስፋፋት ሲፈራረቁበት የቆዩበት የረጅም ዘመናት ሂደት ነው። የረጅም ዘመናት ታሪካችን እያንዳንዱ ማኅበረሰብና በየዘመኑ፣ በሰፊው የታሪካችን ምዕራፎች የነበሩ የብሔርም የሕብረ-ብሔርም ገዥዎች በቀደሙት ዘመናት አጣኋቸው ያላቸውን መሬቶች ለማስመለስ ዳግም በኃይል ሲስፋፋ የነበረበት ውጥንቅጥና አባይን በጭልፋ እንደሚባለው ረጅምና ተጽፎ ያላለቀ፣ ተጽፎም ሊያልቅ የማይችል፣ የብዙ ዘመናት የመጥበብ፣ የመስፋት ሂደቶችና ተደጋጋሚ ኡደቶች ብቻም አልነበሩም። የንግድ ልውውጥ፣ የማኅበራዊ ግንኙነቶች፣ የቋንቋና ባህል መወራርስና መዳቀል የነበሩበትም ሂደት ነበር። ለዳር ድንበርና ለሕዝብ ክብር ለኢትዮጵያ አገራዊ ግንባታ በኦሮሞም፣ በአማራም፣ በአፋር፣ በትግሬ፣ በወላይታ፣ ጉራጌ በሌሎችም የቋንቋና የባህል ማኅበረሰቦች ባፈሯቻቸው በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሀገራዊ እርበኞች፣ አንጸራቂ ጀብድ በፈጸሙ፣ ታላላቅ ጀግኖችና የጦር መሪዎች መስዋዕትነት የተገነባ ሕብረ-ብሔራዊ ኢትዮጵያ ማንነትና ሃገራዊነት የታሪክ ሂደትም ነው። ይህ ውስብስብ የታሪክ ሂደት በ150 ዓመት ታሪክ ትንሽ አጭር መነጽር ሊታጠር፣ ሊገደብ የማይችል ሰፊ የዘመናት የታሪክ ባህርን በጭልፋ በሰፈረ፣ እጅግ ቁንጽል የሆነ የነፍጠኛ የሰባሪ የገባር/የአስገባሪ ትርክትና እንድምታ የማያይወክለው፣ የማይገልጸው ሰፊና ጥልቅ የሆኑ የታሪኮቻችን ገመዶችና ክሮች የልዩ ልዩ ማኅበረስቦች መስተጋብሮች፣ ግንኙነቶችና፣ የሂደቶች ውጤት ነው።

    ዋናው፣ ትልቁ ሃቅ ግን ከዚህም ከዚያም ወገን ማንም የታሪካችን ሙሉ እውቀት፣ ሙሉ መረጃ እንኳን በዚህኛው በወዲያኛውም ሕይወቱ ሊኖረው አይችልም። ታላላቆቹና በዓለም ደረጃ የሚታወቁት የታሪክ ጸሐፍት እነ አርኖልድ ቶዬንቢ (Arnold J. Toynbee)፣ ኤድዋርድ ጊበን (Edward Gibbon)፣ ዘመናዊና ትላልቅ ስም ያላቸው ኒያል ፊርግሰን (Niall Ferguson)፣ ፈርናንድ ብራውዴል (Fernand Braudel)፣ ሌሎችም ታዋቂ የታሪክ አጥኚዎች የሀገራቸውንም ሆነ የዓለምን ታሪክ በሚመለክት የጻፏቸው ሁሉንም የታሪክ ምዕራፎች፣ ሁሉንም ታሪካዊ ክንውኖች፣ ሁሉንም ታሪካዊ መረጃዎች፣ ሁሉንም ታሪካዊ ሂደቶች አጣርተው በሙሉ፣ ፍጹም በሆነ እውቀት/ዩኒቨርሳል የታሪክ ዘይቤም የታሪክ ሙሉ እይታ ሊኖራቸው እንደማይችል የታወቀ ሃቅ ነው። የብዙ አገሮች ታላላቅ የታሪክ ጸሐፊዎች በእያንዳንዱ የታሪክ ምዕራፍ አስከ ዛሬ የሚወዛገቡባቸው በርካታ የታሪክ ኩነቶች፣ የታሪክ ትርጓሜዎች፣ የታሪክ ዘይቤዎች እንዳሉ ራሱ የኢትዮጵያን ታሪክ በራሳቸው ልክ ለሚፈልጉት የፓለቲካ አጀንዳ ቀንጭበውና ቆንጽለው የሚያቀርቡ የየብሔሩ ልሂቃን የሚያጡት ሃቅም አይደለም።

    እነዚህ አጨቃጫቂ፣ አወዛጋቢ የሆኑት በሁሉም ወገን ቁንጽል የሆኑና ማንም በምንም መልኩ ሙሉ በሙሉ በሚያስብል ደረጃ እንደበርክታ የታሪክም የማኅበራዊ ሳይንስ የመነጩ ጥናትችና ትርክቶች ሙሉ እይታ፣ ሙሉ እውቀት፣ ሙሉ ግንዛቤ፣ እንደሌላቸው ይታወቃል። የተፈጥሮ ሳይንስ በተለይም ከአንስታይን የሬላቲቪትይ የፊዚክስ ቲዎሪ (Albert Einstein’s Relativity Theory) ግኝት በኋላ ሁሉን አዋቂና ሁሉን ተንባይ ነኝ የሚለው ማንነቱ ላይ በደረሰብት ቀውስ ሳቢያ የሳይንሱ ማኅበረሰብ የሚቀበለው በአመዛኙ ፍጹም የሆነ፣ ሙሉ የሆነ እውቀት፣ ዩኒቨርሳል የሆነ እርግጠኝነት፣ የትንበያ አቅምም እንደሌለ ነው። ሌሎች ታላላቅ የሳይንስ ፈላስፎች ኢ-እርግጠኝነት (Uncertainty principle) የሚል ስያሜ የሰጡት የተፈጥሮ ሳይንስ ንጉስ የሆነው ፊዚክስ ተፈጥሮን ሙሉ በሙሉ፣ ሁሉን ለማወቅና የሚሆነውንም ለመተንበይ የማይችል፣ በእጅጉ ያለውን ውሱንነት ያጠናከሩ፣ ልዩ ልዩ የእውቀት ዘርፎችም ከኢኮኖሚክስ እስከ የፓለቲካ ሳይንስ የእውቀት ዘርፎች ጠቅላይ ሊሆኑ፣ ሙሉና የወድፊቱንም በፍጹም እርግጠኝነት ሊተነብዩ እንደማይችሉ፣ ልዩ ልዩ የእውቀት ዘርፎች በተወሰነ አውድ፣ በተወሰነ ካባቢ ውሱን ለሆነ ግንዛቤና እውቀት፣ ለውሱን ችግሮች መፍቻ ዘይቤዎች/መሣሪያዎች ብቻ እንደሆኑ፣ የወደፊቱም የመተንብይም ሆነ ያልፈውን የታሪክም የማኅበረሰብን ውጥንቅጦች በሁለንተዊና ጠቅላይ/ዩኒቨርሳል በሆነ መልኩ ለማወቅ እንደማይቻል እንዱ ሌላውን ሲገለብጡ፣ የኖሩ ንደፈ ሃሳቦች፣ ጽንሰ ሃሳቦች (theories)፣ የዓለም እይታዎች (paradigms)፣ ልዩ ልዩ የማኅበረሰባዊና የተፈጥሮ ሳይንስ ፍልስፍናዎች፣ እንዲሁም የዘይቤዎች (methods/models) የትየለሌ መሆናቸው የሚያረጋግጡት ይህንንኑ ነው። በብዙዎች ዘንድ በዚህ ጉዳይ ላይ ሰፊ ግንዛቤና መግባባት የተደረሰ ይመስለኛል።

    ስለዚህ የኢትዮጵያ ልሂቃን በተለይ በፓለቲካው ትልቅ ሚና ያላችሁ የታሪክና የህብረተሰቡን ችግሮች ሁሉ በሚመለከት አለን የምትሉት ግንዛቤ ውሱንነት መቀበል። ትህትና ብትህውትነት (humbleness and humility) እኛ ሁሉን እናውቅለታለን ብለው ለሚገምቱት ሕዝብና ማኅበረሰብም የተሻለው ምልከታ ይመስለኛል። ምክንያቱም ፍጹም እወቀት፣ ፍጹማዊ እውነት አለኝ ለማለት በማይቻልበት እጅግ ሰፊና ጥልቅ የተፈጥሮ፣ የታሪክ፣ የማህብረሰብም ሂደቶች፣ ጉራማይሌዎች፣ ጓዳ ጎድጓዳዎች፣ ጉራንጉሮች፣ ዥጉርጉር ሁኔታዎችና ሂደቶች የነበርን ሕዝቦች በመሆናችን። የሰው ልጆች ሕይወትም ሆነ የዓለም ሕዝቦች ታሪክ አካል የሆነ የኢትዮጵያ ታሪክ (ታሪኮች) ግራጫ ቀለም ያላቸው እንጂ ነጭና ጥቁር ባለመሆናቸው የኋላ ታሪኮቻችን፣ የሚጋጩ ትርክቶች ያን ወይንም ይህን ቁንጽል የታሪክ ጠብታ ይዞ ሙሉ እውቀት ባለቤት ነኝ፤ በሞኖፖል እውቀት እኔ ጋር ብቻ የሚል ስሜት ያላቸው የየብሄሩ ልሂቃን ቁንጽ የታሪክ ትርጉሞች/ትርክትን መሠረት አድርገው የሚሰነዘሩ ሽኩቻዎች የሕዝብ፣ የማኅበረሰብ ቅራኔዎች፣ ጥላቻና፣ ግጭቶች፣ ጥቃቶች መንስዔም እየሆነ የመጣበት ይህ እጅግ አሳዛኝ ሁኔታ እሁን ላይ መቆም ይገባዋል። ለአገርና ለሕዝብ የተሻለው፣ የሚበጀው መንገድም ይህ ይመስለኛል። ሁለተኛው አማራጭ ሕዝብን ማጫረስ፣ ሀገርን ማፍረስ፣ ሁሉም በእሳት የሚጫወት ተዋናይ በሰደድ እሳቱ ወላፈን እራሱም ሆነ በምድር ላይ የሚገኙ የሚወዳቸውም ሳይቀሩ የመለብለብ፣ የሚጠበስ ምድራዊ ገሃነም ብቻ ናቸው።

    የኦሮሞም የአማራም ከዚያም የደቡባዊና የምሥራቃዊ ኢትዮጵያን፣ እንድሁም የኦሮሞን ታሪክ በአግባቡ አላካተተም ወይንም አይወክልም የሚባለው የግዕዝ ስልጣኔ ታሪክ፣ ሌላም ካለ ሁሉም ወገን የኔ የሚላቸው ትርክቶች፣ ልዩ ልዩ ታሪኮች ወይንም የሚጣጣሙበት ወይንም የሚቀራረቡበት መንገዶችና ዘዴዎች መፈለግ፤ ወይንም ደግሞ ተመሳሳይ የታሪክ አረዳድ ያልነበራቸው አገሮች፣ የሚጋጩ ትርክቶች አገራዊ ትርምስ የፈጠሩባቸው የሌሎች ሀገሮችን ሕዝቦች ልምድ ቀስሞ ከሁሉም የተውጣጣ፣ ይህንኑ የሚያጠና ባለሙያዎች የሚገኙበት ኮሚሽን የሚቋቋምበት ሁኔታ ቢመከር ምናልባት አንዱ የመፍትሄ አካል ሊሆን ይችላል። ምክንያቱም ቀደም ሲል እንደተነሳው የአገራችን ትላልቅ የፓለቲካ ቅራኔዎች አንዱ ከአለፉ ታሪኮቻችን የታሪክ አረዳድና አተረጓጎም ልዩነቶች፣ የሚጋጩ ትርክቶች ላይ የሚመነጩ በመሆናቸው ከፍተኛ ትኩረትና ቅድሚያ ሊሰጠው ይገባል እላለሁ።

    ሁሉም አሸናፊ የሚሆንበት፣ ማንም ተሸናፊ የማይሆንበት በሀገሪቱ ዋና ዋና ችግሮች ዙሪያ መፍትሔ ተኮር ውይይቶች በየደረጃው የሚደረጉበት ሁኔታዎች መፈለግ አስፈላጊ ይሆናል። ሁሉም ባለድርሻዎች አገሪቷን እሁን ላይ ከገጠማት የህልውና አደጋ ለመታደግ ከለውጡ መሪዎች ጋር በመነጋገር፣ በለውጡ መሪዎችም በኩል ጉልህ ድምጽ ያላቸውን ባለድርሻዎች፣ የየብሄሩን ልሂቃንና የፓለቲካ ኃይሎች ሁሉ ፍላጎታቸውን በግልጽ ወደ ጠረጴዛው እንዲያቀርቡ፣ ውይይቶች እንዲደረጉ፣ ሰጥቶ የመቀበል፣ ብሎም ሀገራዊና ብሄራዊ መግባባት ላይ መድረስ እንዲቻል መድረኮችን የማመቻቸት ጊዜው አሁን ነው የሚል የሚል ሃሳብ አቀርባለሁ።

    የሁሉም ዜጎችና የቋንቋና የባህል ማኅበሰቦች ጥቅምና መብቶች ያልተከበሩባት ኢትዮጵያ የማንም የየትኛውም ብቸኛ ማኅበረሰብ/ወይንም ብሔር መብት፣ ፍትህና ጥቅም ለዘለቄታው ሊከበርባት እይችልም። የአማራ፣ የኦሮሞ፣ የሌሎችም ማኅበሰቦች ልሂቃንና የፓለቲካ ኃይሎች ቆም ብለው የማንም የማትሆን አገር ሁላችንም ወደ ምድራዊ ሲኦል የሚወስድ መንገድ ከመግፋት እጅግ የተሻለው አመራጭ ለሁሉም ጥቅም፣ ለሁሉም እኩልነት፣ መብቶች፣ ለሁሉም ድምጽና ክብር፣ ለሁሉም የምትመች ኢትዮጵያን እንድትሆን ተነጋግሮ፣ ተግባብቶ፣ ፍኖተ ካርታውን፣ የጨዋታውን ሕግ፣ ሂደቱን፣ የሥነ ምግባር ደንቡን… ወዘተ የሚመለከቱ እንዲሁም ዋና ዋና ፓለቲካዊ ልዪነቶች ላይ ዉይይቶች በማድረግ፣ ወደ መግባባት ላይ ለመድረስ ማሰብ ያለባቸው ጊዜ አሁን ይመስለኛል። ይህ ጥሪ ለኦሮሞ፣ ለአማራ፣ ለሶማሌ፣ ለአፋር፣ ለትግራይ ለሌሎችም ማኅበረሰቦች ልሂቃን፣ የፓለቲካ ኃይሎች፣ እንዲሁም የሕብረ ብሔር የኢትዮጵያዊነት የዜግነት የፓለቲካ ኃይሎች በሙሉ ለህሊናም፣ ለታሪካችሁም እጅግ የተሻለው አማራጭ መሆኑን በአንክሮ ማሰብ ወቅቱ አሁን ይመስለኛል።

    በሁሉም አካባቢዎች የሚገኙ ሕብረ ብሔር ኢትዮጵያውያን የዜግነት መብቶችና ጥቅሞች ፍትሃዊ በሆነ መልኩ እንዲስተናገድ፣ እንዲከበሩ፣ እንዲረጋገጡ የሚያስችል ሂደት መጀመርም አለበት። የየትኛውም ብሔር የበላይነት (hegemony)፣ በየትኛውም አካባቢ ይህ የኔ ለእኔ ብሔር ብቻ ነው ሌላው ዜጋ መጤ ነው፣ ሰፋሪ ነው… ወዘተ የሚሉ የተዛቡና ብዙ ሚሊዮን ዜጎችን በገዛ አገራቸው ባይተዋር ያደረጉ፣ ስጋትን፣ የነገን ተስፋ አለማየት፣ ከሰሞኑ ደግሞ በንጹሃን ዜጎች ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶች ሕይወት ያስቀጠፉ አስተሳሰቦችና ሥነ ልቦናዎች የሚለወጡበት ሁኔታ በቅጡ መታሰብ፣ መፍትሔም ማግኘት አለባቸው። በተጨማሪም ይሄ “የኔ ብሔር፣ ይሄ የኔ አካባቢ ብቻ ነው”፣ የሚሉ ኢ-ፍትሃዊ የሆኑ ጸረ-ዴሞክራሲያዊ አመለካከቶች “የኔ” ለተባለውም ብሔር ሕዝብ ጥቅምንም መብቶችንም ለዘላቂው ሊያስከብርና ሊያስቀጥል አይችልም። ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በሌለበት፣ የሕግ የበላይነት ባልተረጋገጠበት፣ ተጠያቂነትና ግልጽነት የሌሉዋቸው የፓለቲካ ስርዓቶች በስመ ብሄር፣ ወይንም በሀገራዊ ብሄርተኝነት ስም ወደ ስልጣን የመጡ ፈላጭ ቆራጭ አምባገነኖች ብሄሬ በሚሉት ሕዝብ ላይ ያደረሱትን መከራ፣ ስቃይና፣ እልቂት በታሪክም አሁን ላይ በዘመናችንም ከበቂ በላይ ሁላችንም የታዘብን፣ ያየን ይመስለኛል።

    በአንድ ሀገር ውስጥ ግማሹ የበኩር ልጅና አንደኛ ዜጋ፣ ገሚሱ የሀገሪቱ ሕዝብ ደግሞ የእንጀራ ልጅና ሁለተኛ ዜጋ፣ ከዚያም ወረድ ብሎ በስጋት በፍርሃት፣ ያለዋስትና እየኖረ የሚቀጥልባት ኢትዮጵያ እንደ እንድ የጋራ አገር፣ በጋራ አብሮ ለመኖር ሊያዘልቁ የሚያስችሉ አይሆኑም። ይህን እስከፊና ለ26 ዓመታት የተንሰራፋ፣ ዛሬም ሊደገም፣ ተጠናክሮ ሊቀጠልበት የሚሞከርበት፣ ብዙ ሚሊዮኖች አማርኛ ተናጋሪ ይሁኑ እንጂ ከኦሮሞ፣ ከጉራጌ፣ ከወላይታ፣ ከትግሬ፣ ከከንባታ፣ ጋሞ፣ ከሶማሌ አፋር፣ ከሌሎችም ማኅበረሰቦች ቅይጥና ቅልቅል የሆኑ፣ ወይንም በሥነ ልቦናም፣ በአመለካከትም፣ የትኛውም ብሔር ሳጥን ውስጥ ሊገፉና ሊከተቱ የማይችሉ፣ ነገር ግን ሁሉንም ብሔሮች/ማኅበረሰቦች የሚወዱ፣ አብሮ የኖሩ፣ አፍቅሮ፣ ተጋብቶና ተዋልዶ፣ በልዩ ልዩ ማኅበራዊና ሰዋዊ ገመዶች የተሳሰረ፣ በደም በአጥንት የተለሰነ የልዩ ልዩ ማኅበረሰቦች የተገኙ “ከአስገባሪነት”፣ “ከነፍጠኝነት”፣“ከሰባሪነት” ጋር ምንም ግኙነት የሌላቸው፣ ከኢትዮጵያዊነት ሌላ ቤት የሌላቸው፣ ብዙ ሚሊዮን ዜጎቻችን በአዲስ አበባ አካባቢዎች፣ በሐረር፣ በድሬ ዳዋ፣ በባሌ፣ በአዳማ፣ በአሰላ፣ በአዋሳ፣ በልዩ ልዩ ሌሎች የሀገሪቱ የከተማ፣ ከተማ ቀመስና የገጠር አካባቢዎች ሁሉ ሙሉ መብቶቻቸው፣ ደኅነታቸው፣ በሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢዎች በተለይም በኦሮሞ፣ በደቡብ በሌሎችም አካባቢዎች መከበር፣ መረጋገጥ የሚቻልበት ሁኔታዎች፣ ውይይቶች፣ ድርድሮች፣ መግባባቶች መደረስ ይኖርበታል።

    በሀገርም ውስጥ በውጭም የምትገኙ የምታውቁኝም የማታውቁኝም ወድ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ፦

    ታላቁ የአሜሪካን ፕሬዝደንት አብረሃም ሊንከን (Abraham Lincoln) የአሜሪካ ጥቁ ር ሕዝቦችን ከባርነት ለማላቀቅ በተደረገው የደቡብ ባሪያ አሳዳሪ ኮንፌደሬት ሠራዊትና የሰሜኑ የአንድነት ሠራዊቶች ከዛሬ 160 ዓመታት በፊት ባደረጉት የእርስ በእርስ ጦርነት ወቅት እንደተናገረው እርስ በእርሱ ተከፋፈለ ቤት ሊቆም/ሊዘልቅ አይችልም (“A house divided against itself cannot stand”)። አሁን እየታየ ባለው በሕዝብ ውስጥ የሚገኝ ቅሬኔና ትላልቅ ህመሞችና ስንጥቆች ሳቢያ የሁላችንም የጋራ ቤት የሆነችው ሀገረ ኢትዮጵያ በዚህ ሁኔታ ህልውናዋ መቀጠል አይችልም። ፍትሃዊነትና ልከኝነትን (just and fair) ማዕከል አድርገን አገራዊ የፓለቲካ ችግሮቻችንን ካልፈታን፣ ይህ ብዙ ሚሊዮን ዜጎቻችንን መብት አልባና አንገት አስደፊ ያደረገ፣ እስከፊና አሳፋሪ ሁኔታ እንደ አገር አብሮ ለመኖር አያስችለንም። ይህን አስከፊና ከሀገሪቱ ችግሮች አንዱ የሆነ አስተሳሰብና ሕጎች ለመለወጥ ሂደቶች መጀመር አለባቸው። ተጠያቂነት፣ ግልጽነት፣ ስልጣን የተገደበበት፣ ሕዝብ በርካታ አማራጮች ቀርበውለት በነጻ ርዕቱአዊ ምርጫ ሊወስን የሚችልበት የሕግ የበላይነትና ለአገራችን ውስብስብ ችግሮች መድኅን ሊሆን የሚችል ፌደራላዊም ዴሞክራሲያዊም የሆነ የፓለቲካ ሥርዓት ለዘላቂው ለሁሉም የቋንቋና የባህል ማኅበሰቦች፣ ለሁሉም ኢትዮጵያውያን ዜጎች ሊበጅና ሊጠቅም የሚችለው። በአንድ ጎን በየአካባቢው የሚገኙ የማኅበረሰቦች የስልጣን ምንጭነት፣ የባህል ቋንቋቸው እኩልነት የሚረጋገጥበት፣ በሌላ በኩል ደግሞ ሁሉም የኢትዮጵያ ዜጎች በሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች ሙሉ መብቶች የሚከበሩበት፣ የሚረጋገጡበት መንትዮሽ ግብ ሊያጣጥም፣ ሊያስታርቅ የሚችሉ የመፍትሔ ሃሳቦች፣ ሌሎች መሰል አመራጮችንም ማፈላለግ የአገሪቱ የፓለቲካ ልሂቃንና የተደራጁ ኃይሎች በጥልቀት ሊያስቡበት የሚገባ አንገብጋቢና ከቀዳሚዎቹ የፓለቲካ ችግሮቻችን አንዱ ይመስለኛል።

    የ20ኛ ክፍለ ዘመን ታላቁ የሳይንስ ሊቅ አልበርት አንስታይን (Albert Einstein) ከእምሮዋዊ አቅምና እውቀት፣ የወደፊቱን የማለም ምናባዊ ኃይል የበለጠ ነው (“Imagination is more important than knowledge”) እንዳለው ወቅቱ እውቀት አለን የምትሉ ልሂቃን ምናባዊ አቅማችሁን በመጠቀም የሀገራችንን የፓለቲካ ችግሮችና ተግዳሮቶች በውይይት፣ በድርድር፣ ለመፍታት ማሰብን በረጅሙ ማለምን ይጠይቃችሁሃል። ፓለቲካ የዕድሎች ጥበብ (“politics is the art of the possible”) ጭምር ነው ይባላል። ይህ አሻግሮ ማየትን፣ ተግዳሮቶችን ወደ መልካም ዕድሎች፣ አደጋዎችን ወደ ጥሩ አጋጣሚዎች ለመለወጥ ምናባዊ እቅምን መጠቀምንም የሚጠይቅም ጭምር ስለሆነ ይመስለኛል። ዊኒስተን ቸርችል (Winston Churchill) ታላቅ ከመሆን ጋር ታላቅ ኃላፊነትነትም አብሮ ይመጣል፣ ትልቅ ዋጋም ያስከፍላል (“The price of greatness is responsibility”) እንዳለው የብሄርና የሕብረ ብሄር የፓለቲካ ልሂቃን የሀገራችን የፓለቲካ ኃይሎች ለሀገራዊ ሰላም፣ ለሕዝብ መረጋጋት፣ ለፍትሃዊ የፓለቲካ ሥርዓት ምሥረታ፣ እናንተም ትልቅ ለመሆን ለምትችሉበት፣ በርዕቱአዊ ነጻ ምርጫ አማራጭ የፓለቲካ ፕሮግራሞቻችሁን አቅርባችሁ ካሸነፋችሁ 105 ሚልዮን ሕዝብ ለመምራት ለምትችሉበት ዴሞክራሲያዊ የፓለቲካ ሥርዓት በጋራ መሥርቱ። ቆምንለት ለምትሉት ብሄር/ብሄረሰብም ደኅነትና ሰላም፣ ጥቅምና መብቶች፣ እንዲሁ ለመላው ሕዝብ፣ ለሁሉም ኢትዮጵያውን ዜጎች፣ ለሁላችንም የጋራ ሀገር በታላቅ ኃላፊነት መንገድ ለመንቀሳቀስ መወሰን ብልህነትና አስተውሎት ነው። በታሪክ ፊት፣ በሕግም ፊት፣ በህሊናችሁም ተጠያቂ አያደርጋችሁም። በሰማይም እንዲሁ። ሀገር ከሌለ፣ ሀገር ውስጥ ሰላም መረጋጋት ከጠፉ ስልጣንም፣ ጥቅምም፣ ታላቅነትም፣ ማንም ምንም የሚያገኝበት ሁኔታ ሊኖር እንደማይችል፣ ሁሉም ሊጠፋፋ የሚችልበት ሀገራዊ ትርምስ ውስጥ እንደ ዋዛ ፈዛዛ ሊገባ እንደሚቻል በዛሬ ዘመን የተወለዱ የሊቢያን፣ የሶርያን፣ የመንን ሕዝቦች መከራና ስቆቃ እያዩ ያደጉ ታዳጊ ወጣቶች እንኳን የሚገነዘቡት እውነታ ነው።

    ሀገራችን ኢትዮጵያ የምትገኝበት አጠቃላይ ሁኔታ እጅግ እንደሚያሳስበው እንድ ኢትዮጵያዊ ዜጋ፣ ሰሞኑን በተከሰተው የንጹሃን ዜጎቻችን ሕይወት መቀጠፍ፣ መቁሰልና መፈናቀል እንደሚያሳዝነው አንድ ሰብዓዊ ፍጡር፣ ለአማራ ወይንም ለኦሮሞ ብቻ ሳይሆን ለሁሉም የቋንቋና የባሕል ማኅበረሰቦች፣ ዜጎች በፍትህ፣ በሕግ የበላይነት፣ በማኅበራዊ ፍትህ፣ በዴሞክራሲ ፌደራላዊ የፓለቲካ ሥርዓት የሚኖሩባት ኢትዮጵያ እውን እንድትሆን የበኩሉን አስተዋጽኦና ትግል እንዳደረገ አንድ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ዶ/ር አብይ አህመድ፣ ለምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንንለአቶ ለማ መገርሳለአቶ ገዱ አንዳርጋቸው፣ ሌሎችም ለውጡን የመሩና በመምራት ላይ የሚገኙ የኢህአዴግ አመራሮች ይህን ጉዳይ በጥብቅ እንዲያስቡበት ከሀገሪቱ ልዩ ልዩ ባለድርሻ አካላት፣ የብሔርም/ዘውግም፣ የሕብረ ብሔራዊ የፓለቲካ አመለካከትና ፕሮግራም ያላቸው ልሂቃንና ተጽዕኖ ፈጣሪ ባለድርሻዎች ሁሉ በአግባቡ የሚሳተፉበት ብሔራዊ የውይይት፣ የምክክር መድረኮች ማመቻቸት ሰዓቱ የደረሰ ይመስለኛል። መግባባትና እርቅ የሚደረስበት፣ እንዲሁም ወደ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ሊያራምዱ የሚችል ፍኖተ ካርታ በሁሉም ባለድርሻዎች ተሳትፎ ወደ ስምምነት የሚያደርሱ መድረኮች የማመቻቸት ሂደት እንዲጀመር የግሌን ሃሳብ እንደ እንድ ኢትዮጵያዊ ለማቅረብ እወዳለሁ።

    የሀገራችንን ችግሮችና ወቅታዊ ሁኔታ በሚመለከት በማዘጋጀት ላይ ያለሁትን የግሌን ሰፋ ያለ ምልከታ በቀጣይ አቀርባለሁ። ፍትህ፣ ሰላም፣ የሕግ የበላይነት፣ የሕዝብና የሀገርን ጥቅም ማስቀደም በሀገራችን እንዲሰፍን፣ መቻቻልና አብሮ መኖር እንዲለመልም ቸሩ አምላክ ይርዳን!!

    ነአምን ዘለቀ
    ቨርጂኒያ፡ አሜሪካ

    ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለችበት የፓለቲካ ቀውስ የሚያሳስበው ሁሉ ሊያነበው የሚገባ

    Anonymous
    Inactive

    አብረው ማልቀስ እንጅ አብረው መቆም የማይችሉ ማሽንኮች ተፈልፍለው ሀገሬን ዕረፍት ነሷት። ለቅሶ ቤት ለመድረስ አዛኝ ቅቤ አንጓች ሁላ ከአለባበሱ እስከ አነጋገሩ አሳምሮ ይግተለተል እንደሆነ እንጅ፣ መቃብር ላይ ለመላቀስ ቀብር ለማስፈጸም ይደምቃል እንጅ ቁም ነገር ላይ ነጥፎ በጠመንጃ መፈላለጉን ትውልዱ ጀብድ አድርጎታል። እየሳቁ መግደል ሕገ-መንግሥቱ ሆኗል። የመግለጫ ቃል በማዥጎድጎድ የሸፍጥ ኑሮውን ተክኖታል።

    ሀገሬን ምን ነካት?
    አባይነህ ካሴ (ዲ/ን)

    ከሰቀቀናሟ ዕለተ ቀዳሚት ሰኔ 15 እስከ ዛሬዋ ዕለተ ሰኑይ ሰኔ 17 ቀን 2011 ዓ.ም. ሕይወታቸውን በጥይት ላጡት ሁሉ እግዚአብሔር ነፍሳቸውን በቅዱሳን እቅፍ በገነት ያኑርልን፤ ለሐዘንተኞች በሙሉ ሁሉም ሟቾች የኢትዮጵያ ቤተሰቦች ናቸውና ለኢትዮጵያውያን ሁሉ አረጋጊው መንፈስ ቅዱስ አጽናኝ መልአክን ይዘዝላችሁ። ሞት ማንም ይሞታል፤ ብርቆች ሲሞቱ ግን ራሱ ሞት ያነጋግራል።

    ከሩቅ ከአድማሱ ሥር የብርሃን ብልጭታ ሲታየን ‘ሊነጋ ነው’ ስንል፣ የሳቀልንን ወገግታ ተከትለን በተስፋ ዓለም ስንፏልል፣ ደረስንብህ ስንለው ብርሃናችን ወዴት ሔደብን? በጥሩር ፀሐይ ሰማይ ሥር የውኃ ሽታ ያዘለ ነጭ ባዘቶ ደመና ሊያዘንብልን ነው ስንለው እንዳንጋጠጥን መና ቀረ። በርኅቀት ሳይሆን በርቀት ተሰወረ። እኛን ቀርቶ ሊቃውንቱን አደናገረ። መጣ ያልነው እጃችን ገባ ያልነው ሁላ እየጣለን በረረ። ማር ያልነው ከምን ጊዜው መረረ፣ ወተት ስንለው የነበረው ከመቼው ጠቆረ፣ ሰላም ምነው ኢትዮጵያችንን አፈረ?

    ‘እኔ፣ እኔ፣ እኔ’ ከሚለው ባሕር ‘እኛ፣ እኛ፣ እኛ’ የሚል የቡድን ውሽንፍር ውስጥ ገባንና ኢትዮጵያን፣ ሀገሬን ረሳናት። እርሷም እነዚህ ከንቱዎች እንኳን ለእኔ ለራሳቸው የማይሆኑ ገልቱዎች ብላ መታዘቡን ቀጥላለች። የደሟን እንባ ወደ ውስጧ ሕቅ ብላ ታነባለች። ከላይ ከላይ ደማቅ ፈገግታ እያሳየች። የጣቷ አንጓዎች እኔ እበልጥ እኔ እበልጥ ሲሉ ሲገዳደሉ ዝም ብላ ታለቅሳለች። የጠጒሮቿ ዘለላዎች በራሷ ላይ ሲሻኮቱ በሐዘኗ በግናለች፤ በክፉ ጦር ልቧን ተወግታለች። ሀገሬን ምን ነካት? ምንስ ነው የሚበጃት?

    አብረው ማልቀስ እንጅ አብረው መቆም የማይችሉ ማሽንኮች ተፈልፍለው ሀገሬን ዕረፍት ነሷት። ለቅሶ ቤት ለመድረስ አዛኝ ቅቤ አንጓች ሁላ ከአለባበሱ እስከ አነጋገሩ አሳምሮ ይግተለተል እንደሆነ እንጅ፣ መቃብር ላይ ለመላቀስ ቀብር ለማስፈጸም ይደምቃል እንጅ ቁም ነገር ላይ ነጥፎ በጠመንጃ መፈላለጉን ትውልዱ ጀብድ አድርጎታል። እየሳቁ መግደል ሕገ-መንግሥቱ ሆኗል። የመግለጫ ቃል በማዥጎድጎድ የሸፍጥ ኑሮውን ተክኖታል።

    በተመቸ ግርድፍ ቃል ወንድምን በመዝለፍ ድንበር በመዝለል ከልክ በላይ በማለፍ አጥንት የሚወጋ የቃል ጦር በማላጋት እና በመወራወር ሀገር መቁሰሏን ማን የወደዳት ተረዳላት? ንክንኩ ድንጋይ ይፈልጣል፤ የመከራ መዓት በአፍላጋቱ ይጓፍጣል፤ አላውቅም የሚል ጠፍቶ ሁሉም ሁሉን ያውቃል። አዎ ሁሉ ዐዋቂ ሲሆን ሁሉም ይታመማል ያን ዕለት ያን ሠዓት መድኃኒት ይጠፋል።

    ለሞቱት አሟሟት የሰማነው ትርክት ልብ አያሳርፍም፤ ገና አበቅ አለበት። እርሱ ሲጠራ የሚታይ ለጊዜው ግን የተሸፈነ እውነት እንዳይኖር ያሰጋል። ከአንድ ወገን ብቻ የሚሰማ በጥፍር የሚያቆም ንግግርም ቢሆን ታማኝነቱ ምን ጊዜም ከአጠራጣሪነት አይዘልልም። ጊዜ እያወጣ የሚያሰጣው እውነት ይኖራል።

    ወታደር ዘር የለውም፤ ‘እኔ የኢትዮጵያ ወታደር ነኝ’ ሲል የነበረውን መልካም ወላዲቷ አምጣ የወለደችውን ጀግና እንደዋዛ ማጣት አለው ብዙ ንዴት፣ አለው ብዙ ቁጭት። ገዳይ የተባሉት ወይ በተኩስ ልውውጥ፣ ወይ ራስን በመግደል እየተባለ ሞታቸው ይነገራል። አይታመንም ባይባልም ተጠግቶ ላየው ምኑም አያሳምንም።

    አንደኛ፡- ብርጋዴር ጄኔራል አሳምነው ጽጌ ባሕር ዳር አጠገብ ዘንዘልማ በሚባለው አካባቢ መገደላቸው መነገሩ ጥርጣሬውን ከፍ ያደርገዋል። እኒህ ሰው ተሳዳጅ (fugitive) ሆነው ባለበት ጊዜ አብሯቸው ከነበሩም እንኳ ከጥቂት ተከታዮች በስተቀር ብዙ አጃቢዎች እንደማይኖሯቸው ይታወቃል። ዘንዘልማ ከባሕር ዳር ከተማ ዓባይን ተሻግሮ ያለ አካባቢ እንደመሆኑ በርከት ያለ አጃቢ ይዘው ሊሻገሩ ይችላሉ ብሎ መገመት አይቻልም። በሦስት ምክንያት፥ አንደኛ በከፍተኛ ጥበቃ ሥር ባለችው ከተማ ውስጥ ተሰውረው ቆይተው ነበርና። ሁለተኛ በድልድይ የሚሻገሩ ከሆነ ከፍተኛ ጥበቃ እንደሚደረግበት በመገመት በርከት ብሎ ለማለፍ ቀርቶ ራሳቸው ላለፉበት መንገድ እንኳ ያነጋግራል። ሦስተኛ በድልድይ ካልተሻገሩ ወይ በዋና ወይ በታንኳ ምናልባትም በጨለማ ዓባይን አቋርጠው ሊሆን ይችላል። ይህም በርከት ለማለት የሚመች አይደለም።

    እኒህ ሰው የነገሩ ሁሉ መነሻ እና አቀነባባሪ ተደርገው ስማቸው እየተነሳ ይገኛል። እንደዚህ ያለውን ቀንደኛ በከበባ መያዝ ሲገባ ወደ መግደል የተሔደበት መንገድ ሌላ ጥያቄ ከማስነሳት አያድንም። በዚህ ላይ ሰውዬው ሲታኮሱ ጥይት አልቆባቸው እንደነበር መረጃ ተሰጥቷል። ይህ ከሆነ ደግሞ አስጊነታቸውን በብዙ ደረጃ ቀንሶት ነበርና ለመያዝ የበለጠ ምቹ እንደነበር ያመላክታል። የተባሉት ሁሉ ትክክል ከሆኑ መረጃ ማጥፋት ዓይነተኛ ተልዕኮ ለነበረው ዘመቻ (operation) ብቻ የተፈጸመው ድርጊት ትክክል ይሆናል። ሰውዬው በአካል ቢያዙ የሚያወጡት መረጃ እንደሚኖር በመስጋት በሕይወት ከሚቆዩ ሞታቸውን ማቅረቡ ተመርጦ ሊሆን ይችላል። ራሳቸውን ገደሉ ሳይሆን የተባለው በተኩስ ልውውጥ ተገደሉ ነው። ቀባብቶ ማምጣት ሊኖር ይችላል። እውነትን መልሶ በማቋቋም ‘አይ ሰውየው ራሳቸውን ነው የገደሉት’ የሚል ዜና ከመጣ ደግሞ ነገሩ ዘወርዋራ የሆነበትን ምክንያት ማወቁ ይሻላል።

    ሁለተኛ፡- የአቶ ምግባሩ ከበደ ሞት። ሌላው ተስፋ ሊሰጥ ወደ እውነተኛው መረጃ ሊያደርስ ይችል የነበረው የምግባሩ ከበደ ሞት መረጃ የማጥፋቱን ሥራ አቀላጥፎታል ብሎ ላለማሰብ የሚከለክል ነገር የለበትም። ይህ ሰው በሠዓታት ውስጥ ቅርብ ሀገር እስራኤል ደርሶ ሊታከም ይችል እንደነበር መገመት የማንችልበት ዘመን ላይ አይደለንም። መሞኛኘት እንዳይሆን እንጅ ወዲያው የጸጥታ ቁጥጥር እንደተደረገ ሲነገረን አምሽቷል። በሄሊኮፕተር በታገዘ መንገድ ለተሻለ ሕክምና መወሰድ ነበረባቸው። ይህ ለምን አልሆነም?

    ሦስተኛ፡- የጀኔራል ሰዓረ መኮንን ጠባቂ ሞት*። ‘ተይዘዋል’ እየተባለ በየዜና ማሠራጫው ሲነገር የነበረው ሰው ‘ራሱን ገድሏል’ ወደሚል ዜና የተቀየረበት መንገድ እንድንጠረጥር እንጅ እንድንተማመን የሚያደርገን አይደለም። ራሱን የገደለን ሰው ተይዟል ብሎ ዜና የሚሠራባት ምክንያት ሴራን (conspiracy) ያሻትታል እንጅ ቅቡልነት አያስገኝም። [* የአገሪቱ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄነራል ሰዓረ መኮንንና ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንን ጄነራል ገዛኢ አበራን ተኩሶ ገደለ የተባለው የጄነራል ሰዓረ ጠባቂ ራሱን ያጠፋው ወዲያው መሆኑን የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር እንደሻው ጣሰው ዛሬ በሰጡት መግለጫ መናገራቸው ይታወሳል። ማምሻውን ደግሞ ፌደራል ፖሊስ በብሄራዊው ቴሌቪዥን ኢቢሲ ራሱ የሰጠውን መግለጫ አስተባብሎ ጠባቂው በሕይወት እንደሚገኝ አስታውቋል። – ቢቢሲ ዜና አማርኛ]

    አራተኛ፡- በዚያ ጭንቅ ሰዓት ጀኔራል ሰዓረ ቤት መሆናቸውም ሌላው ያልተፈታ እንቆቅልሽ ነው። ከቤቱ ሆኖ “የመንግሥት ግልበጣ” የተባለን ነገር የሚከታታል ጀኔራል አለ ብሎ ለመናገር አያስደፍርም። ሰውዬውም እንደዚህ ዓይነት ጠባይ የለባቸውም፤ ሀገር ሳታርፍ የሚያርፉ ሰው አልነበሩምና። በቢሯቸው ሆነው ከፍተኛ የአመራር ሥራ ሊሠሩ በሚገባበት ሠዓት ቤታቸው የተኙበት ምክንያት ምንድን ነው? እውን ነገሩን አውቀውት ነበርን?

    አምስተኛ፡- ጉምቱዎቹ ባለሥልጣናት ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ደመቀ መኮንን በግል ጉዳይ፣ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ገዱ አንዳርጋቸው ለሥራ ብለው አንዱ አሜሪካ ሌላው ጀርመን እግራቸው በረገጠበት ቀን የመሆኑ ግጥምጥሞሽስ እንዴት በዋዛ ይታለፍ ዘንድ ይችላል?

    እነዚህ ሁሉ ሲጠቀለሉ አቅጣጫቸው ሌላ ያሳያል። ከተነገረን ምህዋር በዘለለ ሁኔታ አንዳች የተቀነባበረ ሴራ ካልነበረ በቀር ወንድም በወንድሙ ላይ እንደዚህ ዓይነት ጭካኔ ያሳያል ብሎ መገመት ይከብዳል። ገና ደብዛዛ መረጃ ላይ ተቀምጠን ጣት ወደ መጠቋቆሙ መሔዱ አያዋጣም። ይሄኛው መንገድ ሌላ ጥፋት ያመጣልና።

    በዶ/ር አምባቸው መኮንን፣ በምግባሩ ከበደ፣ በእዘዝ ዋሴ፣ በጀኔራል ሰዓረ መኮንን፣ በብርጋዴር ጀኔራል ገዛኢ አበራ፣ በብርጋዴር ጀኔራል አሳምነው ጽጌ ሞት በእጅጉ አዝነናል። ስማቸው ባልተነገረን በሌሎችም ሰዎች ሞት በእጅጉ አዝነናል። በዚህ ሁሉ ውስጥ ግን የምትታየን ኢትዮጵያ ናት። ቁስል የሆንባት እስኪ እንራገፍላት።

    ምንጯ ደፈረሰ እንጅ አልነጠፈም። እስኪጠራ መታገስ ዋጋ ቢያስከፍልም ድፍርሱን ጠጥቶ ከመታመም ታግሶ ጥሩውን መጠጣት ጥምን ይቆርጣል፣ ጤናም ይጠብቃል። በደፈረሰ ውኃ ውስጥ ምን እንዳለ ማወቅ አይቻልም። ሲጠራ ግን ይለያል። የሦስቱን ቀን ሁናቴ በጥሞና እንየው፣ ድፍርሱን ለማጥራት ጊዜ እንስጠው። ለመኮነኑ አንቸኩል። ለመቧደንም አንጣደፍ። እነዚህ ከላይ የተነሡት እና ሌሎችም ጥያቄዎች ሲመለሱ የሚወገዘው ይወገዛል።

    ይህ ጥቁር ደመና መግፈፉ አይቀርም። እስከዚያው ግን ጨለማ መንገሡን ተቀብሎ ለብርሃኑ መትጋት መውጣት እና መውረድ ብቻ ነው አማራጩ። የዘሩን ዘጋተሎ አምዘግዝጎ ወዲያ ጥሎ፣ የሀገርን ሕመም ለመታመም አብሮ ቆስሎ የእናት ልጅ የእናቱን ልጅ ሲደክመው አዝሎ፣ ወድቆ እንዳይቀር ውኃ በልቶት ጉልበቱ ዝሎ፣ እየቆረሰ አጉርሶ እየቀደደ አልብሶ፣ ወደ ብርሃን መውጫው ሥር ካልተጓዘ በማለዳ፣ ተከፍሎ አያልቅም የእናት ሀገር የአደራ ዕዳ።

    አባይነህ ካሴ (ዲ/ን)

    ሀገሬን ምን ነካት?


    Anonymous
    Inactive

    የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር አምባቸው መኮንን መገደላቸው ተረጋገጠ
    —–

    የአማራ ክልል ፕሬዝደንት ዶ/ር አምባቸው መኮንን ትላንት (ሐምሌ 15 ቀን 2011 ዓ.ም.) በነበረው የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ተከትሎ መገደላቸውን የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን አስታውቋል።

    አቶ አምባቸውን ጨምሮ የርዕሰ መስተዳድሩ አደረጃጀት ዘርፍ አማካሪ የሆኑት አቶ እዘዝ ዋሴም በደረሰው ጥቃት ሕይወታቸውን ማጣታቸው ታውቋል። ጥቃቱ የተፈፀመው ግለሰቦቹ ስብሰባ ላይ ባሉበት ወቅት እንደሆነ ኢቲቪ አስታውቋል።

    አቶ አምባቸው መኮንን የቀድሞውን የክልሉን ፕሬዝደንት አቶ ገዱ አንዳርጋቸውን በመተካት የተሾሙት የካቲት 29 ቀን 2011 ዓ.ም. ነበር።

    የአማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (አዴፓ) ሐምሌ 15 ቀን 2011 ዓ.ም. ተፈፀመ በተባለው የመንፈቅለ መንግሥት ሙከራ እጃቸው አለበት የተባሉ ሰዎችን በቁጥጥር ሥር ማዋሉም ተሰምቷል።

    የክልሉ ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ብርጋዴር ጀኔራል አሳምነው ፅጌ መንፈቅለ መንግሥቱን አቀነባብረዋል ተብለው በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ፓርቲው አስታውቋል።

    ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ትላንት ከእኩለ ለሊት በኋላ በብሔራዊው ቴሌቪዥን ቀርበው በሰጡት መግለጫ የአማራ ክልል ባለስልጣናት የተገደሉት እና የቆሰሉት በስብሰባ ላይ እያሉ እንደነበር መናገራቸው አይዘነጋም።

    Semonegna
    Keymaster

    የአቶ ገዱ አንዳርጋቸውን የስልጣን መልቀቅ ጥያቄ ተከትሎ የአዴፓ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል እና የጠቅላይ ሚኒስትር የመሠረተ ልማት እና የከተማ ልማት አማካሪ ሚኒስትር የሆኑት ዶ/ር አምባቸው መኮንን ርዕስ መስተዳደር ሆነው ተሹመዋል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው መልቀቂያ ጥያቄ አቀረቡ። ርዕሰ መስተዳድሩ እየተካሄደ ባለው የክልሉ ምክር ቤት ስብሰባ ላይ ነው ጥያቄውን ያቀረቡ ሲሆን፥ ምክር ቤቱም ጥያቄያቸውን ተቀብሏል። የአማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (አዴፓ)በበኩሉም የርዕሰ መስተዳድሩን ጥያቄ መቀበሉን የ አማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት እና ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ዘግበዋል።

    አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ባለፈው ዓመት የካቲት ወር ለሦስተኛ ዙር በርዕሰ መስተዳድርነት ተመርጠው ሲያገለግሉ እንደነበር ይታወሳል። በአጠቃላይም ከታህሳስ ወር 2006 ዓ.ም. ጀምሮ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር በመሆን አገልግለዋል።

    አቶ ገዱ አንዳርጋቸው “ታላቁን የአማራ ሕዝብ ለመምራት ዕድል የሰጠኝን ፓርቲዬን አመሠግናለሁ፤ በስልጣን ዘመኔ በሰጠኋቸው ውሳኔዎች ያስከፋኋችሁ ካላችሁ ከልብ ይቅርታ እጠይቃለሁ። ወኔና ጉልበት ሆኖኝ የኖረውን የአማራ ሕዝብ አመሠግናለሁ፤ ለአዲሱ ርዕሰ መስተዳድርም መልካም የሥራ ዘመን እመኛለሁ” ብለዋል በመሰናበቻ ንግግራቸው።

    የአቶ ገዱ አንዳርጋቸውን የስልጣን መልቀቅ ጥያቄ ተከትሎ ምክር ቤቱ የአዴፓ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል የሆኑትን ዶ/ር አምባቸው መኮንንን ርዕስ መስተዳደር አደርጎ ሾሟል። ዶ/ር አምባቸው ከአዴፓ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነታቸው በተጨማሪ የጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮን የመሠረተ ልማት እና የከተማ ልማት አማካሪ ሚኒስትር በመሆን እያገለገሉ ነበር።

    እድገታቸው ጋይንት፣ ጎንደር ውስጥ የሆነው ዶ/ር አምባቸው መኮንን የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ ሆነው ከመሾማቸው በፊት በተለያዩ የመንግስት ቦታዎች ለ28 ዓመታት ሠርተዋል።

    ዶ/ር አምባቸው ከኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩንቨርሲቲ በኢኮኖሚክስ፣ ቀጥሎም ደቡብ ኮርያ ከሚገኘው ከኮርያ የልማት ኢንስቲትዩት (Korea Development Institute) በፐብሊክ ፖሊሲ የማስተርስ ዲግሪ፣ ከዚያም እንግሊዝ ሀገር ካንተርበሪ ከተማ ከሚገኘው ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ኬንት (University of Kent) ሌላ ማስተርስ ዲግሪ እና የዶክትሬት ዲግሪያቸውን አግኝተዋል።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    ዶ/ር አምባቸው መኮንን


    Semonegna
    Keymaster

    ለመሆኑ እንቦጭን ለማስወገድ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎች የሚሠሩ የአረም ማስወገጃ ማሽነሪዎች ምን አገልግሎት እየሰጡ ነው? አሁን ሥራ ላይ ያሉት የእንቦጭ ማስወገጃ ማሽኖች ቁጥርስ ምን ያክል ነው?

    ባሕር ዳር – በጣና ኃይቅ ላይ የተከሰተውን የእንቦጭ አረም ለማስወገድ አራት ማስወገጃ መንገዶች በአማራጭነት አገልግሎት ላይ እንዲውሉ ምክረ-ሐሳብ ይቀርባል። ከእነዚህ ማስወገጃ መንገዶች እስካሁን ሁለቱ (የሕዝብ ጉልበት እና ማሽነሪዎች) ጣና ሐይቅ ዙሪያ አገልግሎት ላይ እየዋሉ ነው።

    ለመሆኑ እንቦጭን ለማስወገድ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎች የሚሠሩ የአረም ማስወገጃ ማሽነሪዎች ምን አገልግሎት እየሰጡ ነው? አሁን ሥራ ላይ ያሉት የማሽኖች ቁጥርስ ምን ያክል ነው? ስንል የአማራ ክልል የአካባቢ ደንና ዱር እንስሳት ጥበቃና ልማት ባለስልጣንን ጠየቅን።

    በዚህ ወቅት አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙት ሁለት ማሽኖች ብቻ እንደሆኑ የነገሩን በአካባቢ ደንና ዱር እንስሳት ጥበቃና ልማት ባለስልጣን የጣና ሐይቅ ሥርዓተ ምኅዳር ጥበቃ ዳይሬክተር አቶ መዝገቡ ዳኘው ሁለቱ ማሽኖች ካናዳና እሥራኤል ሀገር በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና በአማጋ ኃላፊነቱ ተወሰነ የግል ማኅበር ድጋፍ የተገዙ ናቸው ብለዋል።

    “በባሕር ዳር እና ጎንደር ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት (ዩኒቨርሲቲዎች) እየተዘጋጁ ያሉ የእንቦጭ ማስወገጃ ማሽኖች መኖራቸውን አውቃለሁ” ያሉት አቶ መዝገቡ፥ እስካሁን ድረስ ግን ከተቋማቸው ጋር ርክክብ ፈፅመው ወደ ሥራ አለመግባታቸውን ገልጸዋል።

    አብመድ የተሰሩት ማሽኖች ለምን ርክክብ ተፈፅሞ አገልግሎት መስጠት አልጀመሩም ሲል ሁለቱን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አነጋግሯል። የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ኢንስቲቲዩት ከሙላት ኢንድስትሪያል ኢንጂነሪንግ ጋር በመተባበር የሠራው የእንቦጭ ማስወገጃ ማሽን ጥቅምት 24 ቀን 2011 ዓ.ም. የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው በተገኙበት ቢመረቅም ይህ ዜና እስከሚጠናቀርበት ጊዜ ድረስ አገልግሎት አይሰጥም።

    “ማሽኑ አገልግሎት ለመስጠት ምንም ዓይነት ችግር የለበትም፤ በቅርቡም ለሦስት ወራት ያክል የሙከራ ትግበራ ከተደረገ በኋላ ከሚመለከተው አካል ጋር ርክክብ ይደረጋል” ያሉት የቴክኖሎጂ ኢንስቲቲዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ዶ/ር ሰይፉ አድማሱ የዘገየው ማሽኑን ለማንቀሳቀስ የሚሠራ ራሱን የቻለ የሰው ኃይል አደረጃጀት ባለመኖሩ ቅጥርና ምልመላ ለመፈፀም ጊዜ በመውሰዱ መሆኑን አስታውቀዋል።

    ከሙላት ኢንዳስትሪያል ኢንጅነሪንግ ጋር በመተባበር ለባለሙያዎቹ ስልጠና ለመስጠት ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን ያስታወቁት ዶ/ር ሰይፉ ስልጠናው ከተጠናቀቀ በኋላ ወደ ተግባር እንደሚገቡም ገልፀውልናል። ማሽኑን በዘላቂነት ለማስተዳደርና ሥራውን ለማስተባበር ራሱን የቻለ ተቋማዊ አደረጃጀት እንደሚያስፈልገውም ገልጸዋል።

    በጎርጎራ ወደብ አካባቢ የሚገኘው ሌላው የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የአረም ማስወገጃ ማሽንም ከአካባቢ ደንና ዱር እንስሳት ጥበቃና ልማት ባለስልጣን ጋር ርክክብ ያልተፈፀመበት ማሽን ነው። የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክተር ኢንጅነር ሰለሞን መስፍን “ለአካባቢ ደንና ዱር እንስሳት ጥበቃና ልማት ባለስልጣን ርክክብ እንዲፈፀሙ ደብዳቤ ልከናል” ብለዋል። የተዘጋጀው ማሽን አገልግሎት ለመስጠት ሙሉ በሙሉ ዝግጁ መሆኑን የገለጹት ዳይሬክተሩ፥ ማሽኑን የሚያንቀሳቅስ የሰው ኃይል (ኦፕሬተር) ማዘጋጀት የአካባቢ ደንና ዱር እንስሳት ጥበቃና ልማት ባለስልጣን ድርሻ እንደሆነም አስታውቀዋል።

    የአካባቢ ደንና ዱር እንስሳት ጥበቃና ልማት ባለስልጣን በበኩሉ ማሽኖቹን ለመረከብና የሰው ኃይል ለመቅጠር በተግር ሲሠሩ ማየት እፈልጋለሁ ብሏል።

    በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ እና በሙላት ኢንድስትሪያል ኢንጅነሪንግ የተዘጋጀው ማሽን ከ19 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ እንደተደረገበትም ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። በዚህ ሳምንት ውጭ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ድጋፍ የተገዛ ሌላ የእንቦጭ ማስወገጃ ማሽን ጣና ሐይቅ ላይ ደርሶ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።

    ምንጭ፦ አብመድ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የእንቦጭ ማስወገጃ ማሽን


    Semonegna
    Keymaster

    ዓባይ ኢንዱስትሪያል የልማት አክስዮን ማኅበር ደጀን ከተማ ውስጥ (አማራ ክልል) የሚያስገነባው ሲሚንቶ ፋብሪካ አጠቃላይ ወጪው 8.8 ቢልዮን ብር እንደሆነና ግንባታው በ24 ወራት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ተጠቁሟል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– ዓባይ ኢንዱስትሪያል የልማት አክስዮን ማኅበር በአማራ ክልል ደጀን ከተማ ላይ ሲሚንቶ ፋብሪካ ለመገንባት ከሁለት የውጭ ሀገር ድርጅቶች ጋር የሦስትዮሽ የሥራ ስምምነት ተፈራረመ።

    አክስዮን ማኅበሩ አክስዮን ማኅበሩ ስምምነቱን የተፈራረመው መቀመጫውን ኮፐንሃገን ከተማ (ዴንማር) ያደረገውና ዓለምአቀፍ የምህንድስና (ግሎባል ኢንጂነሪንግ) ኩባንያ ከሆነው “FLSmidth & Co. A/S” እና መቀመጫውን ያንግጆ ከተማ፣ ቻይና (Yangzhou, China) ያደረገው ሌላው ዓለምአቀፍ የምህንድስና ኩባንያ “Hengyuan Group” ጋር አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ሸራተን አዲስ ሆቴል ውስጥ ነው ነው። በስምምነቱ መሠረት “FLSmidth & Co. A/S” የግንባታ መሣሪያዎችን ሲያቀርብ፣ “Hengyuan Group” ደግሞ የግንባታውን ሥራ ያከናውናል። የፋብሪካው ግንባታ አጠቃላይ ወጪውም 8.8 ቢልዮን ብር እንደሆነና ግንባታው በ24 ወራት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ተጠቁሟል።

    ቪድዮ፦ በ8.8 ቢልዮን ብር በደጀን ከተማ (አማራ ክልል) የሲሚንቶ ፋብሪካ ሊገነባ ነው።

    የዓባይ ኢንዱስትሪያል የልማት አክስዮን ማኅበር ለሚገነባው ፋብሪካ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መጠናቀቃቸውንም የአክስዮን ማኅበሩ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ መላኩ አለበል ጠቁመዋል።

    በስምምነቱ ወቅት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፕሬዝደንት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው፦ “ይሄ ፕሮጀክት ተጠናቆ ለክልሉ ልማት ትልቅ አጋዥ ይሆናል የሚል እምነት አለን፤ ስለዚህ ገንቢዎቹም፣ አቅራቢዎቹም፣ ሁላችሁም ደጀን ላይ ይህንን ሲሚንቶ ፋብሪካ ለማፋጠን በምታደርጉት ጥረት የአማራ ክልል ሕዝብና መንግስት ሁልጊዜም ቢሆን ከጎናችሁ ይሆናል” በማለት የክልሉን መንግስት ደጋፍ አረጋግጠዋል።

    የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንንም በበኩላቸው የመሠረት ድንጋይ ማስቀመጥ ብቻ ትርጉም እንደሌለውና፣ ይልቁንም በፍጥነት ተገንብተው ወደማምረት ሥራና ለኅብረተሰቡ የሥራ ዕድል ፈጠራ መግባት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

    የሲሚንቶ ፋብሪካው ወደ ሥራ ሲገባ በቀን 5 ሺህ ቶን ክሊንከር እና በዓመት 2.25 ሚሊዮን ቶን ሲሚንቶ እንዲያመርት፣ ለዚህም 655 ሰዎችን በቋሚነት የሚቀጥር ሲሆን፥ ፋብሪካው በሙሉ አቅሙ ሥራ ሲጀምር ደግሞ የሠራተኞቹን ቁጥር ወደ 1,500 ለማሳደግ ታቅዶ እንደሚገነባ ማብራሪያ ተሰጥቷል።

    ዓባይ ኢንዱስትሪያል የልማት አክስዮን ማኅበር በህዝብና በግል ባለሀብቶች ባለቤትነት በአክስዮን የተቋቋመ የንግድ ድርጅት ነው። ዋና መሥሪያ ቤቱም የአማራ ክልላዊ መንግስት ዋና ከተማ በሆነችው ባሕር ዳር ከተማ ውስጥ ነው።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    ዓባይ ኢንዱስትሪያል የልማት አክስዮን ማኅበር


    Semonegna
    Keymaster

    ግንባታው ስድስት ዓመታትን የፈጀው የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በቀን 2000 የሚሆኑ ታካሚዎችን ሊያስተናግድ የሚችል፣ 11 የቀዶ ሕክምና ክፍሎች እና 500 አልጋዎች አንዳሉት ተገልጿል።

    ባሕር ዳር (ሰሞነኛ ኢትዮጵያ) – የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በ207 ሚሊዮን ብር ወጪ ያስገነባው ጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ነገ በሦስት አገሮች መሪዎች ይመረቃል።

    የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘ እና የሕክምና ኮሌጅ የሥራ አፈጻጸም ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር የሺጌታ ገላው በጋራ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ዩኒቨርሲቲው የግንባታ ወጪው 207 ሚሊዮን ብር የፈጀውና ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ የሆነውን ጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የፌደራልና የክልል ባለስልጣናት በተገኙበት ህዳር 1 ቀን 2011 ዓ.ም. በድምቀት እንደሚያስመርቅ ገልጸዋል።

    በምረቃ ሥነ ስርዓቱ ላይ ከሦስቱ መሪዎች በተጨማሪ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸውና ሌሎችም ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ ባለስልጣናትና ጥር የተደረገላቸው እንግዶች ይገኛሉ ፕሮፌሰር የሺጌታ ተናግረዋል።

    ከዚሁ መግለጫ ጋር አብሮ እንደተጠቀሰው በዩኒቨርሲቲው የሕክምና ኮሌጅ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ 148 የህክምና ተማሪዎችም ከኮሌጁ ለስድስተኛ ጊዜ ይመረቃሉ።

    በእነዚህ የሆስፒታሉ እና የተማሪዎቹ ምረቃ መርሀ ግብር ላይ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ (ኢፌዴሪ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)፣ የኤርትራ ሀገረ ግዛት ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂና የሱማልያ ፌደራላዊ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት መሐመድ አብዱላሂ መሐመድ በተገኙበት ይከናወናሉ።

    የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንቱ ዶክተር ፍሬው ተገኘ እንደገለጹት በመሪዎቹ የሚመረቀው ሆስፒታሉ የቀዶ ህክምና የሚጠይቁና ወደ ክፍተኛ ሕክምና መስጫ ቦታ የተላኩ (referral) በሽታዎችን የሚያክምና በተለያዩ የትምህርት ክፍሎች (ዲፓርትመንቶች) ውስጥ በሕክምና እና በጤና ባለሙያነት ተማሪዎችን የሚያሰለጥን ነው።

    Ethiopia: Are Ethiopian hospitals constructed in environment-suitable and climate-friendly way?

    ግንባታው ስድስት ዓመታትን የፈጀው ጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በቀን 2000 የሚሆኑ ታካሚዎችን ሊያስተናግድ የሚችል፣ 11 የቀዶ ሕክምና ክፍሎች ያሉት፣ 500 አልጋዎችን መያዝ የሚችል መሆኑን ፕሮፌሰር የሺጌታ አብራርተዋል። በክልሉ ካሉት ስፔሻላይዝድ ሆስፒታሎች በጥራትም ሆነ በአገልግሎት የተሻለ ሆኖ ለመገኘት መዘጋጀቱንም ገልጸዋል።

    ሀምሌ 7 ቀን 2006 ዓ.ም. ከተመረቀው የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ሆስፒታል በመቀጠል በክልሉ ስድስተኛ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እንደሚሆን አስታውቀዋል። አያይዘውም ሆስፒታሉ ለምርቃቱ ቀን ይብቃ እንጅ እጅግ ዘመናዊ የሆኑ የህክምና ቁሳቁሶችና ሌሎች መሟላት ያለባቸው ነገሮች ስላሉ ከመንግስት በተጨማሪ ለጋሽ አካላትና በዚህ ዙሪያ የሚሠሩ ወገኖችን ትብብር የሚጠይቅ መሆኑን ገልጸዋል።

    ሚያዝያ 28 ቀን 1992 ዓ.ም በኢፌዴሪ የትምህርት ሚኒስቴር ስር በሙሉ ዩኒቨርሲቲነት የተመረቀው የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሀገሪቱ ውስጥ ካሉት ግዙፍ ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ ሲሆን፥ በ2010 ዓ.ም  52,830 ተማሪችዎችን፣  219 የትምህርት  ዘርፎች (69 በመጀመሪያ/ባችለር ዲግሪ፣ 118  በሁለተኛ/ማስተር  እና 32 በሶስተኛ/ዶክትሬት ዲግሪዎች) ተቀብሎ ያስተምራል። ዩኒቨርሲቲው ስምንት ካምፓሶች ሲኖሩት፥ በውስጣቸውም አምስት ኮሌጆች፣ አራት ተቋማት (institutes)፣  ሁለት ፋኩልቲዎችና አንድ የሕግ ትምህርት ቤት (School of Law)  አሉት።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል

    Semonegna
    Keymaster

    “ለኢንቨስትመንት በሚል ሰበብ አርሶ አደሩን በማደህየት ኢንቨስትመንቱን ማሳደግ አይቻልም፤ መሬታቸው የሚወሰድባቸው አርሶ አደሮች ተመጣጣኝ ካሳ ማግኘት አለባቸው።” ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው

    ዘጋቢ፡-ደጀኔ በቀለ (አብመድ)

    ባሕር ዳር – የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ቢሮ በ2011 ዓ.ም በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ፣ በሕግ ማዕቀፎች እና አሠራሮች ላይ ሲሰጥ የነበረውን ክልላዊ የምክክር መድረክ ዛሬ አጠናቅቋል።

    የአማራ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ለኢንቨስትመንት በሚል ሰበብ ብዙ አርሶ አደሮች መብታቸው ተጥሶ እንደነበር በመጥቀስ አርሶ አደሩን በማደህየት ኢንቨስትመንቱን ማሳደግ አይቻልም፤ መሬት የሚወሰድባቸው አርሶ አደሮች ተመጣጣኝ ካሳ ማግኘት አለባቸው ሲሉ አስገንዝበዋል። ቀደም ሲል ካሳ የማያገኙበት ሕግ የነበረ ቢሆንም ሕጉን የማስተካከል እርምጃ መወሰዱንም አስታውቀዋል።

    አርሶ አደሮች እና የነባር ይዞታ ባለቤቶች መሬታቸውን ሕጋዊ በሆነ መንገድ እንዲጠቀሙ መደረጉ ጥያቄ በሚያነሱበት ጊዜ በመረጃ ላይ የተመሠረተ ምላሽ ለመስጠት ከማገዙም በላይ ህብረተሰቡ ተረጋግቶ እንዲሠራ ያደርገዋል። በመሆኑም አርሶ አደሩን ከአላስፈላጊ እንግልት የምናድንበት በመሆኑ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ርዕሰ መስተዳድሩ አሳስበዋል።

    አርሶ አደሮች በጉልበተኛ ጥቅማቸውን የሚያጡበት ፍትሃዊ ያልሆነ አሠራር ካለ የገጠር መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም ቢሮ ህዝባዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ጠንክሮ መሥራት እና የፍትህ ስርዓቱን ማስከበር ይጠበቅበታልም ነው ያሉት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው።

    ሕገ-ወጥ የመሬት ወረራን በተመለከተ ትኩረት ተሰጥቶት እንዲሠራ ርዕሰ መስተዳድሩ በጥብቅ አሳስበዋል። በተለይ የወል መሬቶች በሕገ-ወጥ መንገድ ወደ ግለሰቦች ይዞታ ስር እየገቡ በመሆኑ በፍጥነት መግታት ካልተቻለ ስር እየሰደደ ሄዶ ግለሰቦች ላይ ጫና ማሳደሩ እንደማይቀር አስገንዝበዋል።

    በመድረኩ የተሳተፉ አካላት በባለቤትነት ይዞ በመንቀሳቀስ ከሚመለከተው ባለድርሻ አካላት ጋር ትኩረት ሰጥተው ሊሠሩ እንደሚገባም አፅንዖት ሰጥተው ተናግረዋል።

    ለተከታታይ አምስት ቀናት የቆየውን የምክክር መድረክ የተካፈሉ አስተያየት ሰጪዎች በበኩላቸው በሚችሉት አቅም ሁሉ ህብረተሰቡን ለማገልገል ፍቃደኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።

    ተጨማሪ ዜና፦ ኢትዮጵያዊው ባለሃብት አቶ በላይነህ ክንዴ እያስገነቡ ያሉት የምግብ ዘይት ፋብሪካ በቅርቡ ሥራ ይጀምራል

    አቶ ወዳጅ ምስክር ከሰሜን ወሎ ዞን፣ ወይዘሮ በላይነሽ አሻግሬ ደግሞ ከደቡብ ጎንደር ፋርጣ ወረዳ በምክክር መድረኩ የተገኙ ተሳታፊዎች ናቸው። ከውይይቱ በቂ ግብዓት እንዳገኙ ነግረውናል። ተሳታፊዎቹ እንደተናገሩት ወቅቱን መሰረት ያደረገ የገጠር መሬት አጠቃቀም ስልጠና መውሰዳቸው ለቀጣይ የተጣለባቸውን የሕዝብ ኃላፊነት በብቃት ለመወጣት ዝግጁ እንደሚያደርጋቸው ለአብመድ ጋዜጠኞች አረጋግጠዋል።

    በመዝጊያ ሥነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት ርዕሰ መስተዳድር ገዱ አንዳርጋቸው የገጠር መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም ቢሮ ከወረዳ እስከ ክልል ድረስ ተቋማዊ በሆነ መንገድ ሥራውን በአግባቡ ለመወጣት ጥረት እያደረገ ያለ ተቋም መሆኑን አውስተው፥ መሬት ሀብት እና የማንነት መገለጫ መሆኑን በመረዳት የኃላፊነት ስሜት በተሞላበት መንገድ ሲንቀሳቀስ ለቆየው ለተቋሙ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ ሥራው አድካሚ መሆኑን በመጥቀስ ወደ ዘመናዊ የመረጃ ቋት ለማስገባት ተቋሙ እያደረገ ያለው ጥረት የሚበረታታ ነው ብለዋል።

    ከገጠር መሬት ጋር በተያያዘ ለሚከሰቱ ማንኛውም ጥያቄዎች ምላሽ መስጠት የሚችለው በመድረኩ ላይ የተሳተፈው ባለሙያ ነው፤ በተለይ በምዕራብ ቆላማው የክልሉ አካባቢዎች ለበርካታ ዘመናት ጥሩ አሠራር ያልነበረባቸውን ቦታዎች በዚሁ ተቋም ውስጥ በተሰማሩ ሙያተኞች እና አመራሮች አማካኝነት ውጤታማ በሆነ መንገድ ማስተካከል ተችሏል ብለዋል።

    በከተሞች ዙሪያ የሚኖሩና ትኩረት የማያገኙ አርሶ አደሮች ጥቅማቸው እና መብታቸው እንዲከበር በማድረግ በኩል ትልቅ ሥራ ተሰርቷል፤ ተገፍተው ለነበሩ አርሶ አደሮች በተገቢው መንገድ ካሳ እንዲያገኙ ተደርጓል ብለዋል።

    ምንጭ፦ የአማራ መገናኛ ብዙሀን ድርጅት (አብመድ)

    ገዱ አንዳርጋቸው

    Semonegna
    Keymaster

    የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ያስገነባው የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ የግንባታ ሥራው የተጀመረው በጥቅምት ወር 2009 ዓ.ም ሲሆን የቻይናው ግዙፍ ኩባንያ ቻይና ሲቪል እንጂነሪንግ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ግንባታውን ሲያከናውን ነበር።

    አዳማ (Semonegna) – በኦሮሚያ ክልል፣ አዳማ ከተማ የተገነባው የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ በዛሬው ዕለት (መስከረም 27 ቀን 2011 ዓ.ም.) ተመርቋል። በምርቃቱ ስነ ስርዓት ላይም ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) እና የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ምክትል ፕሬዝደንት አቶ ለማ መገርሳ፣ የአማራ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው፣ የእንደስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር አርከበ ዕቁባይ እና የኮርፖሬሽኑዋና ሥራ አስፈጻሚ ወ/ት ሌሊሴ ነሜ እንዲሁም ሌሎች የክልልና የፌደራል ባለስልጣናት ከፍተኛ ተገኝተዋል።

    የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ያስገነባው የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ የግንባታ ሥራው የተጀመረው በጥቅምት ወር 2009 ዓ.ም ሲሆን የቻይናው ግዙፍ ኩባንያ ቻይና ሲቪል እንጂነሪንግ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን (China Civil Engineering Construction Corporation/ CCCC) ግንባታውን ሲያከናውን ነበር።

    ከአዲስ አበበ ከተማ 99 ኪሎ ሜትሮች ርቆ የሚገኘው የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ በተለያየ ዘርፍ ለሚሰማሩ አምራች ኩባንያዎች የሚያገለግሉ በአጠቃላይ 19 (በዝርዝር፦ ስድስት 11 ሺህ ካሬ ሜትር፣ ዘጠኝ 5 ሺህ 500 ካሬ ሜትር፣ አራቱ ደግሞ በ3 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፉ) የመሥሪያ ጠለላዎች ወይም የመሥሪያ ቦታዎችን (shades) የያዘ ነው። የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ በአጠቃላይ ሊለማ ከታቀደው 2 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ በመጀመሪያው ዙር ልማት 354 ሄክታር መሬት የሚይዝ ሲሆን ከዚህ ውስጥ ለምቶ ለዛሬ ምረቃ የበቃው በ100 ሄክታር መሬት ላይ የተገነባው ክፍል መሆኑን፣ ይህም ግንባታ 4.1 ቢልዮን ብር መፍጀቱን፣ እንዲሁም ፓርኩ በመጀመሪያው ምዕራፍ በሙሉ አቅም ወደ ምርት ሲገባ እስከ 25 ሺህ ለሚደርሱ ዜጎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ወ/ት ሌሊሴ ነሜ በምረቃው ንግግራቸው ላይ አስታውቀዋል።

    ◌ RELATED: A visit to Hawassa Industrial Park by Dire Dawa Industrial Park & City’s Administration people

    የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ተመርቆ ሥራ መጀመር በሀገሪቱ ወደማምረት የገቡ የኢንዱስትሪ ፓርክኮች ቁጥር ወደ አምስት የሚያሳድገው ሲሆን፥ ከሌሎቹ አራቱ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ለየት የሚያደርገው ፓርኩ ያለበት ከተማ (አዳማ) በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ትልቅ አስተዋጽዖ ያመጣል ተብሎ የታመነበተና አምና ሥራ የጀመረው የአዲስ አበባ-ጅቡቲ የባቡር መስመር በሚያልፍባት የአዳማ ከተማ መገኘቱ ነው። ይህ የባቡር መስመርና የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ እርስ በርሳቸው ጉልህ የሆነ የጥቅም ግንኙነት ይኖራቸዋል ተብሎ ይታመናል። ከዚህ በተጨማሪ የኢንዱስትሪ ፓሩኩ በከተማ ከሚገኘው የአዳማ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩንቨርሲቲ ጋር በማምረት ዘርፍ እና በመማር፣ ማስተማርና ምርምር ዘርፎች መካከል ቁልፍ የሆነ ግንኙነት ይፈጥራሉ ይጠበቃል።

    የሀገሪቱ የማኑፋክቸሪንግ ሴክተር (manufacturing sector) ከኢትዮጵያ ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) መጠን አራት ነጥብ አምስት በመቶ (4.5%) ድርሻ ብቻ የሚሸፍን ሲሆን፥ መንግስት እስከ 2022 ዓ.ም (እ.ኤ.አ) ይህን አናሳ ድርሻ ወደ ሀያሁለት በመቶ (22%) ለማሳደግ አቅዳለች። ከዚህ በተጨማሪ ኢትዮጵያ እስከ 2025 ዓ.ም (እ.ኤ.አ) አሁን ያሏትን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ቁጥር ከአምስት ወደ ሀያ አምስት የማሳደግ ዕቅድ አላት። በያዝነው ዓመት ስድስት የኢንዱስትሪ ፓርኮች (ድሬ ዳዋ፣ ቂሊንጦ II፣ ቦሌ ለሚ II፣ ጅማ፣ ባህር ዳር እና ደብረ ብርሃን) ግንባታቸው ተጠናቆ ወደምርት ተግባር እንደሚገቡ ዶክተር አርከበ ዕቁባይ አስታውቀዋል። 

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ

Viewing 12 results - 1 through 12 (of 12 total)