Search Results for 'ጌታሁን መኩሪያ'

Home Forums Search Search Results for 'ጌታሁን መኩሪያ'

Viewing 11 results - 1 through 11 (of 11 total)
  • Author
    Search Results
  • Anonymous
    Inactive

    በሳይንስና ሂሳብ ትምህርቶች ዙሪያ ጥራትን ማስጠበቅ ያስችላል የተባለ ረቂቅ ስትራቴጂያዊ ዕቅድ ተዘጋጀ
    በ2014 ዓ.ም. ከ50ሺህ በላይ ትምህርት ቤቶች ውስጥ የመንገድ ደህንነት ትምህርት ይሰጣል

    አዲስ አበባ (ትምህርት ሚኒስቴር) – በሳይንስና ሂሳብ ትምህርቶች ዙሪያ ጥራትን ማስጠበቅ ያስችላል የተባለ ረቂቅ ስትራቴጂያዊ ዕቅድ ተዘጋጀ። በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የሂሳብና ሳይንስ ትምህርቶች ማዕከላትን ለማቋቋም የትምህርት ቤት ማኅበረሰብ ያላቸውን ፍላጎት እና የቤተ ሙከራ ኬሚካሎች አጠቃቀም እንዲሁም አወጋገድ ሥርዓት ዙሪያ ጥናታዊ ዳሰሳ ግኝት ቀርቦ ውይይት መካሄዱን የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።

    መድረኩ የማዕከሉ አምስት ዓመት ስትራቴጂያዊ ዕቅድ እና ዓመታዊ የዕቅድ አፈጻፀም ለመገምገም ያለመ ነበር፡፡

    በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የሂሳብና ሳይንስ ትምህርቶች ማዕከል የሥነ ህይወት ትምህርት ባለሙያ የሆኑት አቶ ጌታዬ ሞላልኝ የአምስት ዓመት ስትራቴጂያዊ እቅዱ ዘመናዊ የአሠራር ሥርዓቶችን ተግባራዊ በማድረግ የሂሳብ፣ የሳይንስ፣ የምህንድስና ትምህርቶችን ከጥበብ እና በቴክኖሎጂ በማስደገፍ ለመስጠት የሚያግዝ ነው ብለዋል።

    ቤተ ሙከራ ተማሪዎች በፅንሰ ሃሳብ የተማሩትን የትምህርት ይዘት በተግባር ሙከራ አስደግፈው ይበልጥ ትምህርቱን በቀላሉ እንዲረዱ ጉልህ ድርሻ እንዳለው ባለሙያው ጠቁመዋል፡፡ በክልል ደረጃ በቴክኖሎጂ የተደገፉ ስምንት የስልጠና ማዕከላት እንደሚቋቋሙ አቶ ጌታዬ ተናግረዋል፡፡

    በትምህርት ቤቶች የቤተ ሙከራ ኬሚካሎች አጠቃቀምና አወጋገድ ሥርዓት ዙሪያ አንዳንድ ችግሮች እንዳሉ ከቀረበው ጥናታዊ ዳሰሳ ለማወቅ ተችሏል፡፡

    በመድረኩ ከክልል እና ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮዎች የተውጣጡ የዘርፉ ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

    ከዚህ ቀደም በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በምህንድስና፣ በጥበብና ሂሳብ ዘርፍ የሚቀርቡትን የተማሪዎችን የፈጠራ ውጤቶች በአግባቡ መምራት የሚያስችል ረቂቅ መመሪያ መዘገጀቱንም ሚኒስቴሩ አስታውሷል።

    ከትምህርት ዜና ሳንወጣ፥ በ2014 ዓ.ም ከ50ሺህ በላይ ትምህርት ቤቶች ውስጥ የመንገድና ትራንስፖርት ደህንነት ትምህርት እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር ሰኔ 7 ቀን፥ 2013 አስታውቋል።

    የትምህርት ሚኒስቴርና የትራንስፖርት ሚኒስቴር በትብብር ያዘጋጁት “የመንገድ ደህንነት ለሁሉም” በሚል የመንገድ ደህንነት ሥርዓተ ትምህርት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በሳምንቱ ውስጥ ተካሂዷል።

    የመንገድ ደህንነት ሥርዓተ ትምህርት ከቅደመ መደበኛ እስከ 12ኛ ክፍል፣ እንዲሁም በጎልማሶች ትምህርት እንዲካተት ተደርጎ በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የተቀረፀ ሲሆን በ2014 ወደ ሥራ ይገባል።

    የትምህርት ሚኒስትሩ ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ር ኢንጂ) በ2014 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን ወደ ትግበራ የሚገባው አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት፣ የትምህርት ጥራትን ታሳቢ ያደረገና ባለፉት ዓመታት የታዩ ችግሮችን ነቅሶ ያወጣ መሆኑን ተናግረዋል።

    በቀጣይ ዓመት ከ50ሺህ በላይ ትምህርት ቤቶች ውስጥ የመንገድ ደህንነት ትምህርት ተግባራዊ እንደሚደረግ የገለፁት ሚኒስትሩ፥ የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ የትራፊክ ደህንነት ትምህርት በሥርዓተ ትምህርት ውስጥ መካተቱ በዜጎች ላይ የሚደርሰውን አደጋ እንዲቀንስ ያስችላል ብለዋል።

    የትራንስፖርት ሚነስትሯ ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ ደህንነቱ የተጠበቀ የመንገድ አጠቃቀምን ባህል ለማድረግና የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ ሚኒስቴሩ ከተለያዩ ተቋማት ጋር በጋራ እየሰራ መሆኑን ገለፀዋል።

    የመንገድ ደህንነት ትምህርት በሥርዓተ ትምህርት ውስጥ መካተቱ ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ከማምጣቱም በላይ የመንገድ አጠቃቀምን ባህል ለማድረግ የሚረዳ መሆኑን ሚኒስትሯ ገልፀዋል።

    ሥርዓተ ትምህርቱ ዜጎች የመንገድ ትራፊክ ሕግና ደንብን በአግባቡ አውቀው ተግባራዊ እንዲያደርጉ እና ሌሎችንም እንዲያሳውቁ ዕድል እንደሚፈጥርም ተገልጿል። በዝግጅቱም የመንገድ ደህንነት ትምህርትን ለማስተማር  የሚያስችሉ ቋሳቁሶችን ትምህርት ሚኒስቴር ከትራንስፓርት ሚኒስቴር ተረክቧል።

    በበ2014 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን ተግባራዊ በሚደረገው የመንገድና ትራንስፖርት ደህንነት ትምህርት ላይ በ11 የትምህርት ዓይነቶች የመንገድ ደህንነት ትምህርት የሚተገበር ሲሆን ከ34 ሚሊዮን  በላይ ተማሪዎችን ለመድረስ ያስችላል።

    ምንጭ፦ የኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር

    የመንገድ ደህንነት ትምህርት

    Anonymous
    Inactive

    ለመጪው የትምህርት ዘመን ትምህርት ቤቶች ከነሐሴ 20 ጀምሮ ምዝገባ እንደሚጀምሩ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)፦ የ2013 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን ምዝገባ ከነሐሴ 20 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ እንደሚጀመር ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴሩ ትምህርት ቤቶች የቀጣይ ዓመት የትምህርት ምዝገባን ከነሐሴ 20 ጀምረው ማካሄድ ይችላሉ ብሏል።

    የትምህርት ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ወ/ሮ ሀረጓ ማሞ፥ ትምህርት ቤቶች ምዝገባውን ሲያካሂዱ ኮሮና ቫይረስን (ኮቪድ 19) ለመከላከል በዓለም የጤና ድርጅት እና በኢፌዲሪ ጤና ሚኒስቴር የተቀመጡ ቅድመ ዝግጅቶችንና መከላከያ መንገዶችን በሚገባ በመተግበር መሆን እንዳለበት አሳስቧል።

    ትምህርት የሚጀመርበት ቀን በቀጣይ እንደሚወሰንና ይፋ እንደሚደረግም የገለፁት ዳይሬክተሯ፥ የቀጣዩ ዓመት የትምህርት ሂደት ስኬታማ እንዲሆንም ተማሪዎች፣ መምህራን፣ ወላጆችና መላው የትምህርት ማኅበረሰብ ይህን አስቸጋሪ ወቅት ለማለፍ የሚተላለፉትን ገዢና አስፈላጊ መልዕክቶች ብቻ በመከታተልና ቫይረሱ ሊተላለፍ የሚችልባቸውን መንገዶች ከውዲሁ በማስወገድ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚያስፈልግም አሳስበዋል።

    አካላዊ ርቀትን ጠብቆ ለማስተማር፣ የንፅህና መጠበቂያዎችን ከማዘጋጀትና መሰል የኮሮና ቫይረስን  የመከላከያ መንገዶችን ተግባራዊ ለማድረግ በሚያስችል መልኩ ቀድመው ዝግጅት የሚደረግባቸው ተግባራትም እንደሆኑ አክለው ገልጸዋል።

    በምን ዓይነት መልኩ ትምህርት መጀመር እንዳለበት የተለያዩ አማራጮችን ለማመላከት ሰፊ ውይይት እየተደረገባቸው ሲሆን፥ ውሳኔዎች ላይ ሲደረሱ በቀጣይ ይፋ ይደረጋሉ።

    የ8ኛና የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ጊዜን በተመለከተ ትምህርት ሚኒስቴር በቅርብ የሚያሳውቅ ሲሆን ተማሪዎች ራሳቸውን እያዘጋጁ እንዲቆዩ ሚኒስቴሩ አሳስቧል።

    በመጪው የትምህርት ዘመን ተማሪዎች ለኮሮና ተጋላጭ እንዳይሆኑ ትምህርት ሚኒስቴር ምን ዓይነት ዝግጅት እያደረገ ነው?

    በ2013 የትምህርት ዘመን ተማሪዎች ለኮሮና ተጋላጭ እንዳይሆኑ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር ነሐሴ 19 ቀን 2012 ዓ.ም. አስታወቋል።

    የትምህርት ሚኒስትሩ ዶ/ር ኢ/ር ጌታሁን መኩሪያ እንደገለጹት፥ የቀጣዩ ዓመት ትምህርት ምዝገባ ከነገ ነሐሴ 20 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ በመንግሥት እና በግል ትምህርት ቤቶች እንደሚጀመር እና ትምህርት ቤቶች የኮሮና ቫይረስ መከላከያ ቅደመ ዝግጅቶችንና  ተግባራትን በተገቢው መንገድ በመተግበር ምዝገባ እንዲያከናውኑ አሳስበዋል።

    የበሽታው ሁኔታ እየተስፈፋ ቢሆንም የትምህርት ዝግጅት እና እንቅስቃሴ መጀመር አስፈላጊ ሆኑ መገኘቱን ነው ሚኒስትሩ የተናገሩት።

    ወደ መማር ማስተማር ተግባር በሚገባበት ወቅት ለተማሪዎች ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር እንደሚሠራ ገልጸው፥ የፊት መሸፈኛ ጭንብል (face mask)፣ የእጅ ማፅጃ (sanitizer) እና መሰል አቅርቦቶችን ከባላድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለማቅረብ በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ሚኒስትሩ ተናግረዋል።

    በግልም ሆነ በመንግሥት ትምህርት ቤቶች የኮሮና ቫይረስ ስርጭት እንዳይከሰት ተማሪዎች የፊት መሸፈኛ ጭንብል በማድረግ፣ አካላዊ ርቀትን በመጠበቅ እና እጅን በተደጋጋሚ በመታጠብ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚኖርባቸው ሚኒስትሩ አሳስበዋል።

    ከቅድመ መደበኛ ጀምሮ እስከ 12ኛ ክፍል ላሉት ተማሪዎች በ2012 የትምህርት ዘመን በ2ኛ ሴሚስተር ያለፋቸውን ትምህርቶች ማካካሻ ለመስጠት መታሰቡንም ዶ/ር ኢ/ር ጌታሁን ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮሮፖሬሽን (EBC) ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልጸዋል።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    በመጪው የትምህርት ዘመን ተማሪዎች

    Anonymous
    Inactive

    72 ኪሎ ግራም የምትመዝነው ETRSS-1 ሳተላይት በቻይና መንግሥት ድጋፍና በኢትዮጵያ መንግሥት በጀት የተገነባች ሲሆን፥ ለግብርና፣ ለማዕድን ፍለጋ፣ ለአካባቢ ጥበቃ፣ ለአየር ንብረት ለውጥ ክትትል/ ምርምርና ለመሳሰሉት ጥቅም ላይ ትውላለች።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ኢትዮጵያ የመጀመሪያዋን የመሬት ምልከታ ሳተላይት ታህሳስ 10 ቀን 2012 ዓ.ም. (በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር) ላይ ከቻይና ዋና ከተማ ቤይጂንግ 400 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከሚገኘው የቻይና ሳተላይት ማስወንጨፊያ ጣቢያ ወደ ህዋ ትመጥቃለች። ጉዳዩን በማስመልከት የኢፌዴሪ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ር ኢንጂ.) እና የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ቴክኖሎጂ ኢንስቲቲዩት ጀነራል ዳይሬክተር ሰለሞን በላይ (ዶ/ር) ኅዳር 12 ቀን 2012 ዓም መግለጫ ሰጥተዋል። [ከአንድ ሳምንት በፊት ይህ ዜና በተዘገበበት ጊዜ ቀኑና ሰዓቱ ታህሳስ 7 ቀን 2012 ዓ.ም. ከጠዋቱ 12 ሰዓት ከ21 ደቂቃ ተብሎ የነበረ ሲሆን vኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ር ኢንጂ.) በትዊተር ገጻቸው ቀኑ ወደ ታህሳስ 10 ቀን 2012 ዓ.ም. መዛወሩን አስታውቀዋል]።

    ETRSS-1 የተሰኘችው ይህች ሳተላይት በቻይና መንግሥት ድጋፍና በኢትዮጵያ መንግሥት በጀት የተገነባች ሲሆን፥ ከቻይና መንግሥት የጠፈር ኤጀንሲ ጋር በትብብር የማምጠቅ ሥራው ይከናወናል። 72 ኪሎ ግራም (~159 ፓውንድ) የምትመዝነው ETRSS-1 ሳተላይት ለግብርና፣ ለማዕድን ፍለጋ፣ ለአካባቢ ጥበቃ፣ ለአየር ንብረት ለውጥ ክትትል/ ምርምርና ለመሳሰሉት ጥቅም ላይ ትውላለች።

    መግለጫ በሚሰጡበት ጊዜ፥ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ር ኢንጂ.) ኢትዮጵያ የመጀመሪዋን ሳተላይት ለማምጠቅ ዝግጅቷን ማጠናቀቋ ወሳኝ ጊዜ ላይ እንደምትገኝ ማሳያ ነው ብለዋል። የሳተላይቷ ቁጥጥር ሙሉ ለሙሉ በኢትዮጵያ እና በኢትዮጵያውያን የዘርፉ ባለሙያዎች የሚከናወን እንደሚሆን ተናግረዋል። ይህንን ለማድረግም ከአዲስ አበባ ከተማ ወጣ ብሎ በተቋቋመው እንጦጦ ኦብዘርቫቶሪና የምርምር ማዕከል (Entoto Observatory and Research Center) ቅጥር ግቢ ውስጥ የመቆጣጠሪያ ጣቢያ ግንባታው ተጠናቅቋል። ይህ ጣቢያ የሳተላይቷ ደኅንነት ክትትል የሚደረግበትና ከሳተላይቷ የሚገኙ መረጃዎች የሚሰበሰቡበት ነው።

    የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ቴክኖሎጂ ኢንስቲቲዩት ጀነራል ዳይሬክተር ሰለሞን በላይ (ዶ/ር) በበኩላቸው በሳተላይቷ ግንባታ ከንድፍ ጀምሮ ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች መሳተፋቸውንና በሀገር ውስጥ ከሚገኙም ሆነ ከውጭ አገራት ከመጡ ምሁራን እና ባለሙያዎች መካከል የዕውቀትና የቴክኖሎጂ ሽግግር የተገኘበት መሆኑን ተናግረዋል።

    ETRSS-1 ሳተላይት  ከተወነጨፈች በግማሽ ሰዓት ውስጥ ከመሬት 700 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኝ ህዋ ላይ ቦታዋን ትይዛለች። የሳተላይቷ ግንባታ 2008 ዓ.ም. ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በነበሩበት ጊዜ የተፈረመና 2009 ዓ.ም. ላይ የተጀመረ ነው።

    የሳተላይቷ መምጠቅ ኢትዮጵያ ለሳተላይት ምስል ግዢ በዓመት የምታወጣውን ከ350 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የሚያስቀር ነው።

    ምንጭ፦ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ETRSS-1 satellite

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ (ኢፌዴሪ) የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አማካኝነት የተሠራው ለእርሻ አገልግሎት የሚውል ባለሞተር ማረሻ ተመረቀ።

    የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ጌታሁን መኩሪያን (ዶ/ር ኢንጂ.) ጨምሮ የሚኒስቴሩ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና የሮዳ ኢንጂነሪን ሠራተኞች በተገኙበት ተመርቋል።

    ከዚህ ቀደም ከውጭ ሀገራት የአርሶ አደሩን ድካም ያቃልላሉ ተብለው የተገዙ ዘመናዊ የማረሻ መሣሪያዎች ከሀገራችን ድንጋያማ መሬት ጋር ባለመስማማታቸው የሚጠበቅባቸውን ጥቅም ሳይሰጡ በ አጭር ጊዜ ውስጥ ከጥቅም ውጭ ይውላሉ። ይህ በኢትዮፕያውያን ዲዛይን ተደርጎ የተሠራው ባለሞተር ማረሻ ግን ለሀገራችን መሬት ተስማሚ እንዲሆን ተደርጎ የተሠራ ነው።

    ማረሻው ከተገጠመለት ሞተር ውጪ በኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች የተሠራ በመሆኑ ለጥገና፣ ማሻሻያ ለማድረግና ተጨማሪ ጥቅሞችን ለመጨመር የተመቸ መሆኑን የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

    በቀጣይ በዚሁ ባለሞተር ማረሻ ላይ አርሶ አደሩ ተቀምጦ የሚያርስበት፣ መሬቱን ለመጎልጎል የሚያስችል፣ ምርቱን ማረሻው ላይ ለመጫን የሚያስችሉ አዳዲስ ግልጋሎቶችን እንዲሰጥ ተደርጎ እንደሚዘምን የሮዳ ኢንጂነሪን ባለቤት አቶ አክሊሉ አባተ ተናግረዋል። ማጨድና መውቃት፣ እንዲሁም ምርት መሰብሰብ የሚችል መጎታችም በቀጣይ እንደሚሠራለት ተጠቁሟል። አርሶ አደሩ በቀላሉ ነዳጅ ማግኘት እንዲችል ከእፀዋት ተረፈ ምርት መሠራት የሚችል ባዮፊዩል (biofuel) እንዲጠቀምም ይደረጋል።

    አርሶ አደሮቻንን እስከ ዛሬ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ አላደርግናቸውም ያሉት ሚኒስትሩ ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ር ኢንጂ.) በቀጣይ ችግሮቻቸውን የሚያቃልሉ ቴክኖሎጂዎችን ማላመድና መፍጠር ላይ በትኩረት እንሠራለን ብለዋል። አክለውም፥ ባለሞተር ማረሻውን አርሶ አደሮች የመግዛት አቅም ኖሯቸው እንዲጠቀሙበት ለማድረግም ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በትብብር ይሠራል ነው ያሉት።

    ባለሞተር ማረሻውን ከማዘመንና ጠጨማሪ አገልግሎቶችን አንዲያረክት ማሻሻያዎችን ከማድረግ በተጨማሪ ዋጋውም ከጥንድ በሬዎች መግዣ ባነሰ ዋጋ አርሶ አደሩ እጅ እንዲገባ ጥረት ይደረጋል ተብሏል። ባለሞተር ማረሻው በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርና በሮዳ ኢንጂነሪንግ ትብብር የተሠራ ነው።

    ምንጭ፦ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    ባለሞተር ማረሻ


    Semonegna
    Keymaster

    የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የጥናትና ምርምር ማኅበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዚዳንት ዶ/ር አልማዝ አፈራ በዚህ ፕሮጀክት የተሳተፉ ተመራማሪዎችን ያሉትን ተግዳሮቶች ተቋቁመው ለዚህ በመብቃታቸው ምስጋና ቸረዋቸዋል።

    ደብረ ብርሃን (ሰሞነኛ)– የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የጥናትና ምርምር ማኅበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት ከኢፌዴሪ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታና ግድም ወረዳ ይምሎ ቀበሌ በተቀናጀ የአሳ፣ የዶሮ፣ የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶች ላይ ሲያካሂድ የቆየውን የምርምር ፕሮጀክት አጠናቆ ለዞኑ አስተዳደርና ለአካበቢው ማኅበረሰብ አስረከበ።

    በርክክብ ሥነ-ስርዓቱ ወቅት የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ መምህርና መሪ ተመራማሪ ዶ/ር ገዛኸኝ ደግፌ እንደተናገሩት ምርምሩ በትንሽ ቦታ አሳን፣ ዶሮንና አትክልትን አቀናጅቶ ማልማት የሚያስችል የቴክኖሎጅ ዕውቀትን በመጠቀም የአሳ፣ የዶሮና የአትክልት ልማቱን አቀናጅቶ መሥራት እንደሚቻል ነው ብለዋል። በዚህም የዶሮ ኩስን ለአሳዎች ምግብ እንዲውል እንዲሁም “vermicompost” ቆሻሻን ወደ ጠቃሚ ነገርነትና ማዳበሪያነት የሚቀይሩ ትሎችን ለዶሮዎችና ለአሳ ምግብነት እንዲውል የሚያስችል እንደሆነ አብራርተዋል።

    በምስራቅ ጎጃም ዞን ስንዴ አምራች ወረዳዎች ለገበሬዎች የቀረቡላቸው ኮምባይነሮች በምርታቸው ላይ ጉልህ አስተዋጽዖ እያደረጉ ነው

    አቶ ተፈራ ወንድማገኘሁ የሰሜን ሸዋ ዞን ዋና አስተዳደሪ እንዳሉት ይህ ለምርቃት የበቃው የምርምር ሥራ የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በዞኑ ከሚያከናውናቸው ምርምሮች አንዱ ሲሆን ፣ በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ፈጻሚነትና በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የገንዘብ ድጋፍ የተሠራ መሆኑን ተናግረዋል። ዋና አስተዳዳሪው አክለው እንዳስታወቁት ይህንን ምርምር በዞኑ በሚገኙ ወረዳዎችና ቀበሌዎች ለማስፋፋት ትልቅ ኃላፊነትና አደራ የተጣለባቸው መሆኑን አውስተው ለተግባራዊነቱም እንደሚሠሩ ተናግረዋል።

    የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ኢንጅነር ጌታሁን መኩሪያ ባደረጉት ንግግር ሚኒስቴር መሥሪያ ቤታቸው ከሚደግፋቸው በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች በሚባል ደረጃ ከ60 በላይ ምርምሮች መካከል የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ አንዱና ውጤታማው በመሆኑ ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ በሚችሉ ትናንሽ ፕሮጀክቶች በመደገፍ የሀገራችንን ልማት ማረጋገጥ ይኖርብናል ብለዋል። ይህን ፕሮጀከት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ለሁሉም ዞኖችና ወረዳዎች እንዲተላለፍ ማኑዋልና ስታንዳርድ ተዘጋጅቷል። የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳደርም በአማራ ክልል ለሚገኙ ሁሉም ዞኖች እንዲያደርስ ኃላፊነት የተሰጣቸው ሲሆን በቀጣይ በሀገር አቀፍ ደረጃ እንዲሰራጭ አናደርጋለን ብለዋል።

    ዶ/ር አልማዝ አፈራ የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የጥናትና ምርምር ማኅበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዚዳንት በበኩላቸው በዚህ ፕሮጀክት የተሳተፉ ተመራማሪዎችን ያሉትን ተግዳሮቶች ተቋቁመው ለዚህ በመብቃታቸው ምስጋና ቸረዋቸዋል። እንደ ፕሬዚዳንቷ ገለፃ፥ በሀገራችን እስከ ሁለት ሚሊዮን የሚደርሱ ሥራ-አጥ ወጣቶች መኖራቸው የሚታወቅ ሲሆን እንደነዚህ ዓይነት የምርምር ሥራዎች ደግሞ ወጣቶችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚ በማድረግ ሚናቸው የጎላ ነው ብለዋል። ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲም ብዙ የምርምር ውጤቶች ያሉት ሲሆን እነዚህን ምርምሮች ወደ ፕሮጀክት መቀየር የሚያስችል ተሞክሮ ስለሆነ ይህ ትልቅ ማሳያ ይሆነናል ብለዋል። በመጨረሻም የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርንና የኤፍራታና ግድም ወረዳ አስተዳደርን ላደረጉት ድጋፍና ትብብር ምስጋና አቅርበዋል።

    ምንጭ፦ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የተቀናጀ የግብርና ምርምር ፕሮጀክት


    Anonymous
    Inactive

    ተረፈ-ምርትን በመጠቀም ማምረት የሚያስችል ፕሮጀክት ይፋ ሆነ
    —–

    ቆሻሻና አነስተኛ ውሃን በመጠቀም የአሳና ዶሮ ምግብ፣ ማዳበሪያ፣ አትክልትና ፍራፍሬ በቀላሉ ማምረት የሚያስችል የተቀናጀ የግብርና ዘዴ የምርምር ፕሮጀክት ተጠናቆ ወደ ስራ ሊገባ ነው፡፡

    በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ድጋፍ የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ለ3 ዓመታት ባደረገው ምርምር አርሶ አደሩ በአነስተኛ የጓሮ መሬትና ውስን የጉድጓድ ውሃ በማዘጋጀት ዘርፈ ብዙ ምርት መሰብሰብ የሚቻልበት ፕሮጀክት ተጠናቆ ለትግበራ ተዘጋጅቷል፡፡

    ምርምሩ በተደረገበት በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታና ግድም ወረዳ ይምሎ ቀበሌ የተደራጁ ወጣቶችን በማሳተፍ ውጤታማ የአሳ፣ የዶሮ፣ የማዳበሪያ፣ የሙዝና የሸንኮራ አገዳ ምርቶችን በአነስተኛ መሬት ላይ ማሳካት ተችሏል፡፡

    በፕሮጀክቱ ምረቃ ላይ የተገኙት የአ.ፌ.ዴ.ሪ. ኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ጌታሁን መኩሪያ ይህን ፕሮጀክት ትልቅ የሚያደርገው ወጣቶች በአነስተኛ ወጪ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሊጠቀሙበት የሚችሉበት መሆኑ ነው ብለዋል፡፡

    ሚኒስትሩ የፕሮጀክቱን የአተገባበር ሰነድ ለዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ለአቶ ተፈራ ወንድማገኘሁ አስረክበዋል፡፡

    ምንጭ፦ ዋልታ ሚዲያ

    Anonymous
    Inactive

    ኢትዮጵያ የኤሌክትሮኒክስ ግብይትን ለመዘርጋት የጀመረችውን ስራ ዴንማርክ እንድታግዝ ጠየቀች፡፡
    —–

    በኢትዮጵያ የዴንማርክ አምባሳደር ካሪን ፖውልሰን ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የስራ ሃላፊዎች ጋር በግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያና በኤሌክትሮኖክስ ግብይት ዙሪያ ምክክር አድርገዋል፡፡

    የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ር ኢንጂ.) ኢትዮጵያ የጀመረችውን የኤሌክትሮኒክስ ግብይት ዴንማርክ እንድታግዝና ቴክሎጂን በሚጠቀም የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ዘረፍ እንድትሳተፍ ጠይቃዋል፡፡

    1ቢሊየን ዶላር ገደማ የውጭ ምንዛሬ የሚያስገኘውን ቡና እሴት ጨምሮ በኤሌክትሮኖክስ ግብይት ወደ ገበያ ማቅረብ ቢጀመር ገቢውን በ4 እና 5 እጥፍ ማሳደግ እንደሚቻል ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡

    የኤሌክትሮኒክስ ግብይትን በኢትዮጵያ ለመጀመር የአለም አቀፉ ፖስታል ድርጅት ቴክኒካል ኮሚቴ ጥናት መጀመሩ ይታወሳል፡፡

    የኢትዮጵያ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር

    Anonymous
    Inactive

    የኤሌክትሮኒክስ ግብይት በኢትዮጵያ ለመጀመር የአለም አቀፉ የፖስታ ድርጅት ቲክኒካል ኮሚቴ ጥናት ጀመረ፡፡
    —–

    አፍሪካን በተለያዩ ቀጠናዎች ከፍሎ የኤሌክትሮኒክስ ግብይት ለመጀመር እየሰራ የሚገኘው ዓለማቀፍ የፖስታ ኅብረት (Universal Postal Union) አጥኚ ቡድኑን ወደ ኢትዮጵያ የላከው ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በተፈራረመው ስምምነት መሰረት ነው፡፡

    ቡድኑ የኢትዮጵያ ዝግጁነት ከፖሊሲ፣ ከመሰረተ ልማትና ከኢ-ታክስ አኳያ፤ ኢትዮጵያ ስርዓቱን ለመዘርጋት ምን ማድረግ አለባት፣ ትግበራውን በምን መልኩ መከናወን ይኖርበታል የሚሉትንና የመሳሰሉትን ጉዳዮች ያጠናል፡፡

    የግብይት ስርዓትን ለማዘመን፣ ገዢና ሻጭን በቀጥታ ለማገናኘት፣ ቀጠናዊ ትስስር ለመፍጠር፣ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን ሃብት ለማሳደግ ትልቅ ጠቀሜታ ይኖረዋል ተብሎ የሚታሰበው የኤሌክትሮኒክስ ግብይት ስርዓት በኢትዮጵያ በቅርቡ ተግባራዊ ለማድረግ ርብርብ እንደሚደረግ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ር ኢንጂ.) ተናግረዋል፡፡

    የአለም አቀፉ የፖስታል ድርጅት የምስራቅ አፍሪካ ማዕከሉን ኢትዮጵያ ውስጥ ለመገንባት ማቀዱ ይታወሳል፡፡

    በ2017 በአፍሪካ በኤሌክትሮኒክስ ግብይት ከ85 ቢሊየን እስከ 100 ቢሊየን ዶላር የገበያ ድርሻ ይይዛል ተብሎ ይገመታል፡፡

    የኢትዮጵያ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– ግዙፉ የመኪና አምራች የሆነው የጀርመኑ ኩባንያ ቮልስዋገን በኢትዮጵያ ኢንቨስት ለማድረግ የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ፈረመ። ስምምነቱን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽነር አበባ አበባየሁ እና ከሰሃራ በታች የኩባንያው የአፍሪካ ቀጣና ሥራ አስፈጻሚ ቶማስ ሻፈር ተፈራርመዋል። በስምምነቱ መሠረትም ኩባንያው የመኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካ መክፈት፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫ ዕቃዎችን ማቅረብ፣ የስልጠና ማዕከል መክፈት እና ተጓዳኝ ሥራዎችን ይሠራል።

    በስምምነቱ ላይ በኢትዮጵያ የሥራ ጉብኝት ላይ የሚገኙት የጀርመኑ ፕሬዚዳንት ፍራንክ ዋልተር ስታይንማየር እና የኢፌዴሪ የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ ተገኝተዋል።

    ቮልስዋገን ኩባንያ ከሰሃራ በታች ካሉ የአፍሪካ አገራት መካከል ኢትዮጵያን የማስፋፊያ ማዕከሉ አድርጎ ሲመርጥ፣ ከኩባንያው ጋር የመግባቢያ ስምምነት በመፈረም ከሰሃራ በታች ካሉ አገራት ኢትዮጵያ ሦስተኛዋ አገር (ከጋና እና ናይጄሪያ ቀጥሎ) ሆናለች።

    ◌ VIDEO: የጀርመኑ ግዙፍ የመኪና አምራች ኩባንያ ኢትዮጵያ ውስጥ ሰፊ ኢንቨስትመንት ለመጀመር እየተንቀሳቀሰ ነው

    ኩባንያው ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ለመሥራት መስማማቱ በቀጥታ የእሴት ሰንሰለት የተቀናጀ የአውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪ ክላስተር ለመፍጠር ወሳኝ ምዕራፍ ይከፍታል ነው የተባለው።

    ኮሚሽነር አበበ አበባየሁ በፊርማ ሥነ-ስርዓቱ ላይ እንዳሉት መንግሥት አገሪቷን ቀዳሚ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ለማድረግ በቁርጠኝነት እየተንቀሳቀሰ ነው።

    ”በአውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪው መስክ ልዩ ክላስተር እንዲመሠረት መንግሥት ያለሰለሰ ጥረት ያደርጋል” ያሉት ኮሚሽነሩ ይህን ተግባራዊ ለማድረግ ቮልስዋገንን ጨምሮ ፍላጎት ካላቸው ተቋማት ጋር በቅንጅት ለመሥራት ‘ዝግጁ ነው’ ብለዋል።

    ◌ VIDEO: German companies including Volkswagen and Siemens embarking to invest in Ethiopia

    የኩባንያው የአፍሪካ ቀጣና ሥራ አስፈጻሚ ቶማስ ሻፈር በበኩላቸው የኢትዮጵያ መንግሥት ለአውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪው እድገት ትኩረት መስጠቱ ‘የሚደነቅ ነው’ ሲሉ ተናግረዋል። ከዚህ በተጨማሪ ቶማስ ሻፈር ‘ኢትዮጵያ ፈጣን እድገት በማስመዝገብ ላይ ያለች እና በሕዝብ ብዛትም ከ አህሪካ አገራት በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠች በመሆኗ፥ ከሰሃራ በታች ባሉ ሀገራት ለመስፋፋት በምናደርገው ጥረት ኢትዮጵያን ሁነኛ ተመራጭ አገር አድርገናታል፤ በተጨማሪም ቮልስዋገን ኩባንያ ሀገሪቱ ያላትን የስትራቴጂ ጥቅም ከግምት በማስገባት በ አውቶሞቲቭ ዘርፍ ከፍትኛ እድገት እንድታስመዘግብ ይተጋል’ ብለዋል።

    ከዚህ ጋር በተያያዘ የጀርመን የቢዝነስ ልኡካን ቡድን ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የሥራ ሃላፊዎችና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በኢትዮጵያ በኢንቨስትመንት መስክ በሚሰማሩበት ሁኔታ ላይ መክረዋል።

    ሲመንስ የተሰኘው በግዙግነቱ ከአውሮፓ ኩባንያዎች ቀዳሚውን ስፍራ የሚይዘው የጀርመን የቴክኖሎጂ ኩባንያ በኢትዮጵያ ከዚህ በፊት ሲሠራቸው ከነበሩ የቴክሎጂ ዘርፍ ሥራዎች በተጨማሪ በተጠናከረ መልኩ ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን አሳውቋል።

    NEWS: German automaker Volkswagen develops automotive industry in Ethiopia

    የጀርመን የቴክኖሎጂ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ማኅበርም ቢሮውን አዲስ አበባ በመክፈት ወደ ሥራ ለመግባት ፍቃደኛ መሆኑን አሳውቋል። ማኅበሩ ጀርመን ውስጥ ያሉ የቴክኖሎጂ ድርጅቶች ማኅበር እንደመሆኑ ድርጅቶቹ በመስኩ ለመሰማራት የሚያስችላቸውን ሁኔታ ለማመቻቸት መልካም አጋጣሚን እንደሚፈጥር ይታመናል።

    በኢትዮጵያ መንግስት በኩል በጊዜያዊነት በነፃ ቢሮ በመስጠት ጭምር ማንኛውንም እገዛ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑንም ተገልጿል።
    የልኡካን ቡድኑ አባላት በኢትዮጵያ ውስጥ በኢንቨስትመንት የተሰማሩ ድርጅቶች ከምንዛሬ እጥረት፣ በደላላ ምክንንያት ምርቶቻቸው ተጠቃሚው ጋር በተጋነነ ዋጋ መድረስ የመሳሰሉ ችግሮች እንደገጠሟቸው ተናግረዋል።

    የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ር ኢንጂ.) የኤሌክትሮኒክስ ግብይት ለመጀመር ሥራዎች እየተሰሩ በመሆኑ ወደ ሥራ ሲገባ ችግሩ እንደሚቀረፍ ተናግረዋል።

    ምንጮች፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) / የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ቮልስዋገን


    Semonegna
    Keymaster

    የሚገነባው የኤሌክትሮኒክ ግብይት (ኢ-ኮሜርስ) ማዕከል በኢትዮጵያ በቀዳሚነት በግል ዘርፉ የሚመራ ሆኖ መንግስት ክበባዊ ሁኔታን የማመቻቸት ሥራ ይሠራል። መንግስት ለማዕከሉ ግንባታ የሚያስፈልገው የቦታ መረጣም ሆነ መሠረት ልማት በፍጥነት እንደሚያሟላም ተጠቁሟል።

    አዲስ አበባ (ኢ.ፕ.ድ)– የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት የኤሌክትሮኒክ ግብይት (ኢ-ኮሜርስ) ማዕከል በኢትዮጵያ ለመገንባት በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና በዓለም አቀፍ ፖስታል ዩኒየን መካከል ስምምነት ተደርጓል።

    የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር ኢንጂነር ጌታሁን መኩሪያ እና የዓለም አቀፍ ፖስታል ዩኒየን (Universal Postal Union) ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ቢሻር ሁሴን ስምምነቱን ተፈራርመዋል። ሚኒስትሩ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ የኢትዮጵያ መንግስት የቦታ አቅርቦትና መሠረተ ልማት የማሟላት ኃላፊነት የተሰጠው ሲሆን፤ የዓለም አቀፍ ፖስታል ዩኒየን ደግሞ ሥርዓቱን የመዘርጋት ኃላፊነቱን ወስዷል።

    እንደ ዶ/ር ኢንጅነር ጌታሁን ገለጻ፥ በአዲስ አበባ ይገነባል የተባለው ማዕከል በአፍሪካ ውስጥ ከሚገነቡ አራት ኢ-ኮሜርስ ማዕከላት አንዱ ሲሆን፥ ቀድሞ የምስራቅ አፍሪካ የኢ-ኮሜርስ ማዕከል ኬንያ ናይሮቢ ሊገነባ ታቅዶ የነበረው ነው። ወደ አገራችን የመጣበት ምክንያት ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂ እያደገች መምጣቷ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ተለያዩ ሀገራት የሚያደርገው በረራ መበራከቱና የኢትዮጵያ መንግስት ለዘርፉ የሰጠው ልዩ ትኩረት ዋንኞቹ ናቸው።

    ተመሳሳይ ዜና፦ Chinese giant e-commerce Alibaba Group & its affiliate Ant Financial entering Ethiopian market

    ማዕከሉ በኢትዮጵያ በቀዳሚነት በግል ዘርፉ የሚመራ ሆኖ መንግስት ክበባዊ ሁኔታን የማመቻቸት ሥራ ይሠራል። መንግስት ለማዕከሉ ግንባታ የሚያስፈልገው የቦታ መረጣም ሆነ መሠረት ልማት በፍጥነት እንደሚያሟላም ጠቁመዋል።

    የማዕከሉ መገንባት ከፍተኛ ሀገራዊና አህጉራዊ ጠቀሜታ አለው ያሉት ዶ/ር ኢንጅነር ጌታሁን፥ ለ100ሺህ ወጣቶች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥርና በሀገሪቱ ውስጥ ከፍተኛ የገንዘብ አቅም እንደሚሆን ተናግረዋል። የአፍሪካ ምርቶች ለማንኛውም ሀገራት በቀላሉ እንዲታዩ በማድረግ ገበያውን በቀላሉ እንዲቀላቀሉ ዕድል ይሰጣል ብለዋል።

    በኢትዮጵያ የገንዘብ ዝውውር በኤሌክትሮኒክ እንዲሆን ማድረግ የሚያስችል የህግ ማዕቀፍ እየተዘጋጀ መሆኑን የጠቆሙት ሚኒስትሩ፥ በቅርቡ ወደ ትግበራ እንደሚገባና የገንዘብ ዝውውርን ለማቀላጠፍና የግብይት ሥርዓቱን ለማዘመን ሚናውን ይወጣል። ዓለም በአሁኑ ወቅት በኤሌክትሮኒክ ግብይት በጣም ርቆ መሄዱን ተከትሎ በአፍሪካ ደረጃ አስፍቶና ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሠራም ተናግረዋል።

    በዘርፉ ኢትዮጵያ ብዙም ተጠቃሚ እንዳልሆነች የገለጹት ሚኒስትሩ፥ ዘመኑ የኤሌክትሮኒክ ግብይት (ኢ-ኮሜርስ) ዓለም ነውና ከዓለም ጋር እኩል ለመጓዝ ማዕከሉን ተግባራዊ ማድረግ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። በዓለም ላይ እንደ አማዞን (Amazon)፣ አሊባባ ግሩፕ (Alibaba Group) እና የመሳሰሉ በኤሌክትሮኒክ ግብይት በዓመት እስከ አምስት ትሪሊን ዶላር እንደሚያንቀሳቅሱ ሁሉ በማዕከሉ አማካኝነት አገሪቱ ለማደግ የሚያስችላትን ተግባራት ሁሉ ትሠራለች ብለዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት (ኢ.ፕ.ድ) | ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ኢ-ኮሜርስ ማዕከል


    Semonegna
    Keymaster

    አዲሱ የካቢኔ አባላት ሹመት የቀረበው የአስፈፃሚ አካላት ስልጣንና ተግባር ለመወሰን የወጣውን አዋጅ እንደገና ለማሻሻል የቀረበውን አዲስ ረቂቅ አዋጅ በምክር ቤቱ መፅደቁን ተከትሎ መሆኑን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት  አስታውቋል።

    አዲስ አበባ – የኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከ20 አዳዲስ የካቢኔ አባላት ሹመት ውስጥ 50 በመቶ ሴቶች ሆነው እንዲያገለግሉ በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) የቀረበውን ሹመት ጥቅምት 6 ቀን 2011 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ አፀደቀ።

    የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባውን እያደረገ የሚገኝ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ከሚሾሙት 20 ካቢኔዎች ውስጥ 10 ሴቶች ሆነው በተሰጣቸው ኃላፊነት እንዲያገለግሉ ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።

    አዲሱ የካቢኔ አባላት ሹመት የቀረበው የአስፈፃሚ አካላት ስልጣንና ተግባር ለመወሰን የወጣውን አዋጅ እንደገና ለማሻሻል የቀረበውን አዲስ ረቂቅ አዋጅ በምክር ቤቱ መፅደቁን ተከትሎ ነው።

    በዚህም መሠረት የሹመቱ ዋና መስፈርት ብቃት፣ የትምህርት ዝግጅትና ለውጥን የመምራት አቅም መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ከሚሾሙት ካቢኔዎች 50 በመቶ (በቁጥር፥ ወይም ከ20ዎቹ 10 ሴት) ካቢኔዎች መሆናቸውንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልፀዋል።

    ይህም በኢትዮጵያ ምናልባትም በአፍሪካ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ መሆኑም በምክር ቤቱ ተገልጿል።

    በዚህ በተደረገው የካቢኔ ሹመት ለውጥ ውስጥ ከዚህ በፊት “የፐብሊክ ሰርቪስ እና ሰው ሀብት ልማት ሚኒስቴር” ተብሎ ይጠራ የነበረው ሚኒስቴር ተለውጦ አሁን “ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን” (Civil Service Commission) በሚል እንደተተካ ታውቋል። ከዚህ በተጨማሪ ሶስት ኮሚሽኖችም በአዲስ መልክ ተካተዋል፤ እነዚህም (1) የሥራ ፈጠራ ኮሚሽን (Job Creation Commission)፣ የአካባቢ፣ የደንና የአየር ንብረት ለውጥ ኮሚሽን (Environment, Forestry and Climate Change Commission) እና የፕላንና እድገት ኮሚሽን (Plan and Development Commission) ናቸው።

    አዲስ በተዋቀረው ካቢኔ ውስጥ የተሰየሙት ባለስልጣናትና የተሰየሙበት ስልጣን ዝርዝር

    1. ዶ/ር ሂሩት ካሳው ― የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር
    2. ዶ/ር ሂሩት ወልደማርያም ― የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር
    3. ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል ― የሰላም ሚኒስቴር
    4. ዶ/ር ሳሙኤል ሆርቃ ― የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር
    5. ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ ― የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር
    6. አቶ ብርሃኑ ጸጋዬ ― ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ
    7. አቶ አህመድ ሺዴ ― የገንዘብ ሚኒስቴር
    8. ዶ/ር አሚን አማን ሐጎስ ― የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር
    9. ወ/ሮ አዳነች አበበ ― የገቢዎች ሚኒስቴር
    10. ኢ/ር አይሻ መሀመድ ሙሳ ― የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር
    11. አቶ ኡመር ሁሴን ― የግብርና ሚኒስቴር
    12. ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ ― የሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር
    13. ወ/ሮ የዓለምፀጋይ አስፋው — የሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ሚኒስቴር
    14. ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ ― የትራንስፖርት ሚኒስቴር
    15. አቶ ጃንጥራር አባይ ― የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር
    16. ዶ/ር ኢ/ር ጌታሁን መኩሪያ ― የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር
    17. ዶ/ር ጥላዬ ጌጤ ― አምባዬ የትምህርት ሚኒስቴር
    18. ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ ― የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
    19. ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገብረ-እግዚአብሔር ― የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር
    20. ዶ/ር ፍፁም አሰፋ ― የፕላን ልማት ኮሚሽን ኮሚሽነር

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የካቢኔ አባላት ሹመት

Viewing 11 results - 1 through 11 (of 11 total)