Search Results for 'ትምህርት ሚኒስቴር'

Home Forums Search Search Results for 'ትምህርት ሚኒስቴር'

Viewing 15 results - 1 through 15 (of 127 total)
  • Author
    Search Results
  • Semonegna
    Keymaster

    ጋዜጠኛ መዓዛ ብሩ የክብር ዶክትሬታቸውን ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተቀበሉ

    ባሕር ዳር፥ ኢትዮጵያ (ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ) – ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሐምሌ 16 ቀን፥ 2015 ዓ.ም ባካሄደው የተማሪዎች ምረቃ ለጋዜጠኛ መዓዛ ብሩ የክብር ዶክትሬት መስጠቱ ይታወሳል። በዕለቱ ጋዜጠኛ መዓዛ ብሩ በሥራ መደራረብ ምክንያት በምረቃ ዕለቱ ተገኝተው ባለመቀበላቸው፥ ኅዳር16 ቀን፥ 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ስካይላይት ሆቴል በአካል ተገኝተው ተቀብለዋል።

    በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የ2015 ዓ.ም የተማሪዎች ምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ የመጀመሪያዋ የክብር ዶክትሬት ተሸላሚ የጠንካራ ጋዜጠኝነት ተምሳሌቷ እና የባለታሪኮች ባለአደራ ጋዜጠኛ መዓዛ ብሩ ናት።

    የክብር ዶክተር መዓዛ ብሩን ለክብር ዶክትሬት ሽልማት ያበቋቸው ሥራዎች በዝርዝር:-

    • በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የግል ኤፍ ኤም ሬዲዮ (ሸገር ኤፍ ኤም 1) መሥራች እና ባለቤት፤
    • የመጀመሪያዋ ሴት የሬዲዮ ማሰራጫ ድርጅት መሥራችና ባለቤት፤
    • በእንግዶች ምርጫዋ፤ በምርምር በተደገፈ የመጠይቅ ዘይቤዋ፣ በትህትናዋ፣ በአነጋገር ለዛዋ በቀጥታ አዘጋጅታ ከምታቀርባቸው መርሃ ግብሮች (የቅዳሜ ጨዋታ እና ሸገር ካፌ) በተጭማሪ በተለያዩ የሸገር ሬዲዮ መርሃ ግብሮች እንዲሁም በሌሎች ሬዲዮም ሆነ ቴሌቪዥን መርሃ ግብሮች ላይ አሻራ የተወች እና ባጠቃላይ በዚህ ዘርፍ ለተሰማሩ ጋዜጠኞች አርአያ የሆነች፤

    ምናልባት ከሁሉ በላይ ታዋቂ የሆነችበትና አምሳያ የሌለው የላቀ አስተዋፅኦ ተብሎ ሊወሰድ ከሚችሉት ሥራዎቿ ውስጥ አንዱ፥ በቀላሉ ተተኪ የማይገኝላቸውን በርካታ ባለታሪክ ምሁራን፣ የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎች፤ የኪነ-ጥበብ ሰዎች፤ ጋዜጠኞች እና ሌሎች ባለሙያዎች የህይውት ታሪክ፣ ሥራ፣ አስተሳሰብ እና ለሌሎች አርአያ የሚሆነውን የሕይወት ፍልስፍናቸው በራሳቸው አንደበት ተሰናድቶ ለታሪክ እንዲቆይ ማድረጓ ነው። በዚህም ለኢትዮጵያውያን በዓይነቱ ተወዳዳሪ የሌለውና ከጊዜ ወደጊዜ እያደገ የሚሄድ የታሪክ የድምጽ መዘክር አበርክታለች ማለት ይቻላል። የጨዋታ እንግዳ መሰናዶ እንግዶቿ ያካበቱት ልምድ፤ አበርክቶታቸው፤ ያልተጻፉ ሃገራዊ ጉዳዮች እና ሚስጥሮች ከኃላፊ ባለታሪኮቹ ጋር እንዳያልፉ፤ በመቅረጸ-ድምጽ ተሰንቀው በሰፊው እንዲታወቁ እና ከትውልድ ትውልድ እንዲተላለፉ አድርጋለች። በእርግጥም ጋዜጠኛ መዓዛ ብሩ ከየተደበቁበት ፈልጋ ቃለ መጠይቅ ካደረገቻቸው ጉምቱ እንግዶች መካከል ጥቂት የማይባሉት አሁን በመሃከላችን አይገኙም፤ ታሪካቸው ግን ህያው ሆኗል።

    ጋዜጠኛ መዓዛ ብሩ በ1950 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ የተወለደች ሲሆን፥ ዘጠኝ ዓመት ገደማ እስኪሆናት በምዕራብ ሃረርጌ በምትገኘው ሂርና ከተማ አደገች። ሂርና ሳለች ጎረቤቶቿ የኦሮሞ፣ የሃረሪና የሶማሌ እንዲሁም የየመን ተወላጆች ስለነበሩ በተለያዩ ባሕላዊ ዕሴቶች እና እርስ በእርስ ትስስር የዳበረ አስተዳደግ ነበራት። ይህም ለሥነ-ጽሁፍ ከነበራት ዝንባሌ ጋር ተዳምሮ ለዛሬው ማንነቷ መሠረት ሆኗታል።

    • ጋዜጠኛ መዓዛ ብሩዘጠኝ ዓመት ሲሆናት ወላጆቿ አዲስ አበባ ወደሚገኘው የቅድስተ ማርያም የልጃገረዶች ካቶሊክ አዳሪ ትምህርት ቤት አሰገቧት።
    • 1967 ዓ.ም. የሁለትኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ እያለች በእድገት በሕብረት ዘመቻ ወደ ውቅሮ፥ ትግራይ ተልካ ለስድስት ወራት አገልግላለች።
    • በ1970 ዓ.ም. አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ገብታ በሥነ ልሳን ትምህርት ዘርፍ የመጀመሪያ ዲግሪዋን ተቀብላለች።
    • ከሬዲዮ ሥራ ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ የተዋወቀችው የመጨረሻ ዓመት ተማሪ ሳለች በአጋጣሚ ሲሆን፥ በወቅቱ ተወዳጅ ከነበረው የእሁድ ፕሮግራም ጋር ለነበራት ለስምንት ዓመታት ያክል የቆየ ትስስር ምክንያት ሆኖታል። ይሁን እንጂ በመጀመሪያ በቋሚነት የተመደበችበት ሥራዋ በባህል ሚኒስቴር ስር የመርሃ ስፖርት ጋዜጣ የስፖርት ዘጋቢነት ነበር።
    • በመቀጠልም በኢትዮጵያ ሬዲዮ የእሁድ ፕሮግራም ተሳትፎዋን ሳታቆም በባህል ሚኒስቴር የዓለም አቀፍ አግልግሎት ክፍል አገልግላለች።
    • ከዚያም በብሔራዊ ባንክ የብሪቱ መጽሄት ዋና አዘጋጅ በመሆን የፋይናንስ ዜናዎችን እና አጫጭር ታሪኮችን በመጻፍ እና በአርትኦት አገልግላለች።
    • በ1984 ዓ.ም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን ተቀላቅላ የፕሬስ እና ኮሚኒኬሽን ኦፊሰር በመሆን ለአራት ዓመታት ሠርታለች።
    • ከዚያም በግል በአማካሪነት እና በሕዝብ ግንኙነት እና ማስታወቂያ ስትሠራ ከቆየች በኋላ፤ በ1987 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ሬዲዮ በ1 የሬዲዮ ጣቢያን የአየር ሰዓት በመጠቀም የቅዳሜ ከሰዓት የጨዋታ መርሀ ግብርን ከባለቤቷ ከአርቲስት አበበ ባልቻ እና ከረዥም ጊዜ ጓደኛዋ አርቲስት ተፈሪ ዓለሙ ጋር የማዘጋጀት ዕድል አግኝታ መርሀ ግብሩን ለስምንት ዓመታት ያክል ስታቀርብ ቆይታለች።
    • በመጨረሻም በ2000 ዓ.ም. አንጋፋና ተወዳጅ የሆነውን ሸገር ኤፍ ኤም1ን እዉን ለማድረግ በቅታለች።

    በአጠቃላይ ጋዜጠኛ መዓዛ ብሩ በኢትዮጵያ የጋዜጠኝነት ሙያ የጥንካሬ ተምሳሌትና በዘርፉ ለበርካቶች አርአያ ለመሆኗ ተገቢ ዕውቅና ይሆን ዘንድ የባሕር ዳር ዩኒቨርሰቲ ሴኔት በከፍተኛ ትምህርት አዋጅ ቁጥር 1152 / 2011 በተሰጠው ስልጣን መሠረት በአርት የዓመቱ የክብር ዶክትሬት እንዲሰጣቸው ወስኗል።

    ምንጭ፦ ባሕር ዳር ዩኒቨርሰቲ

    Semonegna
    Keymaster

    ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ጆርናል ለማስጀመር በምሁራን አስገመገመ

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – በማስተማርና በምርምር ሥራዎቻቸው ዕውቅናን ያተረፉ ፕ/ር አማረ አስግዶም እና ፕ/ር ያለው እንዳወቅ እንዲሁም በኢፌዲሪ የትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ምርምርና ስርጭት (research and dissemination expert) ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት ዶ/ር ተስፋማርያም ሽመክት፣ ብሎም የዩኒቨርሲቲው ምሁራን በተገኙበት የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ‘ኮተቤ የትምህርት ጆርናል’ (Kotebe Journal of Education, KJE) የተሰኘውን ጆርናል ለማስጀማር ዝግጅቱን አጠናቆ ለዚሁ ዓላማ የተሰነዱ ፖሊሲንና መመሪያን የካቲት 16 ቀን፥ 2015 ዓ.ም አስገምግሟል።

    የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በአዋጅ ከተቋቋመ እነሆ አንድ ዓመት ከጥቂት ወራት በሆነ ጊዜ ውስጥ በርካታ የማቋቋም ሥራዎችን ሲሠራ ቆይቷል ። ከእነዚህም አንዱ ዩኒቨርሲቲው የሚታወቅበት የራሱ መለያ ጆርናል እንዲኖረው ማስቻል ነው። ጆርናል ምሁራን ጥናትና ምርምሮቻቸውን ከዩኒቨርሲቲው ባሻገር ለሶስተኛ ወገን ተጠቃሚ የሚያደርሱበት ድልድይ ነው። ለዩኒቨርሲቲ ይህ ድልድይ አንዱ የሀገራዊነት እና ከዚያም ባሻገር መለኪያ ነውና በጥንቃቄ የምንይዘው ነው ብለዋል። በመሆኑም ይህንኑን እውን ለማድረግ ስንሠራ ቆይተን የሚተገበርበትን አሠራር (ፖሊሲ እና የአሠራር መመሪያ) ቀርፀን ለዛሬ ማስጸደቂያ ቀን (validation) አድርሰናልና፤ ለስኬቱ አስተዋጽኦ ላደረጋችሁ በሙሉ ትልቅ አክብሮት አለኝ ሲሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

    በመልዕክታቸው አያይዘውም ፕሬዝዳንቱ ‘ኮተቤ የትምህርት ጆርናል’ (KJE) በዓይነቱ ለየት ያለ፣ ሀገራችንን፣ ተቋማችንን እና ትውልዱን የሚያሻግር እንዲሆን ከፍተኛ ጥንቃቄ በተሞላበትና ደረጃውን በጠበቀ መልኩ እንዲታተም ለዚሁ ሥራ አመራርነት ለተሠየመው ቲም አደራ ብለዋል።

    የ‘ኮተቤ የትምህርት ጆርናል’ አስመልክቶ የተዘጋጀ ፖሊሲን ያቀረቡት የጆርናሉ ዋና አርታኢ የሆኑት ዶ/ር ሩቂያ ሀሰን፥ የጆርናሉ ዋና ዓላማ ላቅ ባለ ሁኔታ ለተመራማሪዎች ሀገራዊ እና ዓለም ዓቀፋዊ የትምህርት እና የምርምር ውጤቶቻቸውን የሚያሳትሙበትን ተጨማሪ ዕድል መፍጠር መሆኑን ገልፀዋል። የጆርናሉ ተባባሪ አርታኢ ሆነው የተመደቡ ዶ/ር ይታያል አዲስም በበገለጻቸው የሚቀርቡ ጽሑፎች ከዚህ በፊት በማንኛውም ጆርናል ላይ ያልቀረቡና ሳይንሳዊ ሥነ-ዘዴዎችን (guidelines) ያሟሉ ስለመሆናቸው በጥብቅ ዲሲፕሊን ተገምግመውና የተቀመጠላቸውን መስፈርቶችን አሟልተው ሲገኙ ብቻ ለህትመት እንደሚበቁ ተናግረዋል። የዩኒቨርሲቲው የመረጃና ግንኙነት ቴክኖሎጂ (ICT) መሠረተ ልማት ቡድን መሪ አቶ ማቲያስ አድማሱ በበኩላቸው፥ ለህትመት የሚቀርቡ ጽሑፎች በኦንላይን ሲስተም ሆነው ጆርናሉ ለህትመት እስኪበቃ ድረስ ያለው ሂደት ደህንነቱ የተጠበቀና አስተማማኝ እንዲሆን ይሠራል ብለዋል።

    ምንጭ፦ የዩኒቨርሲቲው የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

    Semonegna
    Keymaster

    ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል የሚያግዝ የመምህራን አቅም ማጎልበቻ ፍኖተ-ካርታ ማዘጋጀቱን ገለጸ

    አዲስ አበባ (ኢዜአ) – ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል የሚያግዝ የመምህራን አቅም ማጎልበቻ ፍኖተ-ካርታ ማዘጋጀቱን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ብርሀነመስቀል ጠና ገለጹ።

    መንግሥት ዩኒቨርሲቲው በትምህርት ዘርፍ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ እያከናወናቸው ያሉ ተግባራትን በመደገፍ ረገድ የጀመረውን ሥራ አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጥሪ አቅርበዋል።

    የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ብርሀነመስቀል ጠና ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ጋር ባደረጉት ቆይታ፥ ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በትምህርት ሥርዓቱ ላይ ከመዋቅር ጀምሮ ማሻሻያዎች እየተደረጉ ስለመሆናቸው ተናግረዋል።

    ለአብነትም 10ኛ ክፍል ይሰጥ የነበረው ብሔራዊ ፈተና በ12ኛ ክፍል እንዲሰጥ ከማድረግ ጀምሮ በዩኒቨርሲቲዎች በ3 ዓመት ይመረቁ የነበረውን ወደ 4 ዓመት እንዲያድግ መደረጉን አስታውሰዋል።

    ባለፉት ዓመታት በተለይ በትምህርት ፍኃዊነትና ተደራሽነት ላይ በርካታ ሥራ የተሠራ ቢሆንም በትምህርት አግባብነትና ጥራት ላይ የተሳካ ወይንም አጥጋቢ ሥራ ባለመሠራቱ ውጤት ሊመዘገብ አልተቻለም ብለዋል። ለዚህም በቅርቡ የወጣው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት የኢትዮጵያ የትምህርት ጥራት ችግር ምን ላይ እንዳለ በግልጽ አሳይቷል ብለዋል።

    በተመሳሳይ ከዚህ ቀደም ለመምህራን ምዘና ተሰጥቶ በርካቶቹ ዝቅተኛ ውጤት ማስመዝገባቸውን አውስተው፤ ይህ ለትምህርት ጥራት ችግሩ ዓይነተኛ አስተዋፆኦ እንዳለው ነው ያስረዱት። ለተማሪዎቹ ዝቅተኛ ውጤት መመዝገብ መምህራንን ጨምሮ አጠቃላይ የትምህርት ማኅበረሰቡ ኃላፊነት ያለበት በመሆኑ ችግሩን በጋራ መፍታት ይገባል ነው ያሉት።

    መንግሥት የትምህርት ዩኒቨርሲቲ አለመኖር ለትምህርት ጥራት መጓደል አንዱ ምክንያት መሆኑን በመረዳት ችግሩን ለማቃለል ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ማቋቋሙን ገልፀዋል። ጨምረውም፥ በተለያዩ ችግሮች እየተፈተነ የሚገኘውን የኢትዮጵያ የትምህርት ዘርፍ ለማከም ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በርካታ ሥራዎችን እየሠራ እንደሚገኝ አንስተዋል።

    ዩኒቨርሲቲው የመምህራንን ትምህርት ዋነኛ ምሰሶ በማድረግ የትምህርት አመራሮች፣ ተመራማሪዎች፣ አማካሪዎችና ፖሊሲ አውጪዎችን ማፍራት ላይ አተኩሮ እየሠራ እንደሚገኝም ተናግረዋል። በመሆኑም ዩኒቨርሲቲው የትምህርት ስብራቱን ለመጠገን የሚያስችል የመምህራን አቅም ማጎልበቻ ፍኖተ-ካርታ ማዘጋጀቱን ነው የተናገሩት። ፍኖተ-ካርታው በቀጣይ ለትምህርት ሚኒስቴር እንደሚቀርብም ነው የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ብርሃነመስቀል ጠና የገለጹት።

    መንግሥት ዩኒቨርሲቲው በትምህርት ዘርፍ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ እያከናወናቸው ያሉ ተግባራትን በመደገፍ ረገድ የጀመረውን ሥራ አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጥሪ አቅርበዋል። ሁሉም ባለድርሻ አካላት የመምህራን ሙያ በማክበርና የማስከበር ኃላፊነት እንዳለባቸው ገልፀው፥ የመምህራን ዕውቀትንና አቅምን ማጎልበት ደግሞ ለነገ የማይባል የዛሬ የቤት ሥራ መሆኑን አመላክተዋል።

    ምንጭ፦ ኢዜአ

    Semonegna
    Keymaster

    በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ግማሽ (50%) እና ከዚያ በላይ ውጤት ያስመዘገቡ
    እና የማጠናከሪያ መርሐ ግብር የሚከታተሉ ተማሪዎች ወደ ከፍተኛ ትምህርት እንደሚገቡ ተገለፀ

    አዲስ አበባ (ትምህርት ሚኒስቴር) – የትምህርት ሚኒስቴር የ2014 ዓ.ም 12ኛ ክፍል ፈተና የዉጤት ትንታኔ፣ ወደ ከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ውጤትና ተያያዥ ጉዳዮች አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል።

    መግለጫውን የሰጡት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የተገኘው የፈተና ውጤት ከስርቆትና ከኩረጃ በፀዳ መልኩ በትክክል የተመዘገበ መሆኑን ገልጸዋል።

    በ2014 ዓ.ም ለተሰጠው ፈተና በጠቅላላ የተመዘገቡት ተፈታኞች ቁጥር 985,354 ሲሆኑ፤ ከእነዚህ ውስጥ 92 ከመቶ የሚሆኑት ፈተናውን ወስደዋል። 20,170 ተማሪዎች በፈተናው ከተገኙ በኋላ በተለያዩ የደንብ ጥሰቶች ምክንያት ተባረዋል።

    ከፍተኛ ውጤት የተበመገበበት የትምህርት መስክ — በተፈጥሮ ሳይንስ 666 ከ700 ከፍተኛ ውጤት ሆኖ የተመዘገበ ሲሆን በማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ 524 ከ600 ከፍተኛ ውጤት ሆኖ ተመዝግቧል። በሀገር አቀፍ ደረጃ ፈተናውን ካስፈተኑ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ሰባት ትምህርት ቤቶች ያስፈተኑትን ተማሪዎች 100% አሳልፈዋል ተብሏል።

    በጾታ ደረጃ የወንዶች አማካይ ውጤት 30.2 ከመቶ ሲሆን፤ የሴቶች አማካይ ውጤት ደግሞ 28.1 ከመቶ እንደሆነ፥ ይህም በወንዶች እና በሴቶች መካከል በአሐዛዊ ምልከታ (statistically) የጎልላ ልዩነት እንዳለና፤ ወንዶች ከሴቶች አሐዛዊ ብልጫ (statistically higher) ውጤት እንዳስመዘገቡ አስረድተዋል።

    በክልሎች ደረጃ በዉጤት ደረጃ የጎላ ልዩነት እንደሌለ ገልፀው፤ አዲስ አበባ፣ ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም የሐረሪ ክልል አሐዛዊ የተሻለ (statistically significantly higher) ውጤት ያስመዘገቡ መሆኑን ፕሮፌሰር ብርሃኑ አብራርተዋል።

    በ2014 ዓ.ም በተሰጠው የ12ኛ ክፍል ፈተና ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሊያስገባ የሚችል ወጤት፥ ማለትም ግማሽ (50%) እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡት ተማሪዎች ቁጥር ሲታይ፥ የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና ከወሰዱት አጠቃላይ 339,642 ተማሪዎች መካከል 22,936 (6.8%) ተማሪዎች፣ የማኅበራዊ ሳይንስ ፈተና ከወሰዱት አጠቃላይ 556,878 ተማሪዎች መካከል 6,973 (1.3%) ተማሪዎች ግማሽ (50%) እና ከዚያ በላይ አስመዝግበዋል።  የሁለቱም የትምህርት መስኮች በድምር ሲታይ፥ ፈተናውን ከወሰዱት 896,520 ተማሪዎች ውስጥ 29,909 (3%) የሚሆኑት ተማሪዎች 50% እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ መሆናቸውን ገልፀዋል።

    ከተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች የተገኘው አማካይ ውጤት 31.6 ከመቶ ሲሆን፤ ከማኅበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች የተገኘው አማካይ ውጤት ደግሞ 27.8 ከመቶ ነው። በሁሉም የትምህርት ዓይነቶች የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች አማካይ ውጤት ከማኅበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች አማካይ ውጤት አሐዛዊ ጉልህ (statistically significant) ብልጫ እንዳላቸው ሚኒስትሩ አመላክተዋል።

    በአጠቃላይ ከፍተኛ ውጤት፥ በመላው ሀገሪቱ በማኅበራዊ ሳይንስ  ከ500 በላይ (ከሙሉ 600 ነጥብ) ያስመዘገቡ 10 (አስር) ተማሪዎች ብቻ ሲሆኑ፤ በተፈጥሮ ሳይንስ ከ600 በላይ (ከሙሉ 700 ነጥብ) ያስመዘገቡ ደግሞ 263 (ሁለት መቶ ስድሳ ሦስት) ተማሪዎች ናቸው። ወደፊት ጊዜው ሲደርስ እነዚህን እጅግ ከፍተኛ (great distinction) ላመጡ ተማሪዎች ትምህርት ሚኒስቴር ልዩ እውቅና እንደሚሰጣቸው ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አስታውቀዋል።

    ፈተናውን ከወሰዱ አጠቃላይ 485,393 ወንድ ተማሪዎች መካከል ግማሽ (50%) እና ከዚያ በላይ ያገኙት 20,343 (4.2 በመቶ) ወንድ ተፈታኞች ሲሆኑ፤ ከተፈተኑት አጠቃላይ 411,127 ሴት ተማሪዎች መካከል ግማሽ (50%) እና ከዚያ በላይ ያገኙት 9,566 (2.3 በመቶ) ሴት ተፈታኞች ናቸው።

    ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያላመጡ ተማሪዎች በማጠናከሪያ መርሐግብር (remedial program) እንደ ዩኒቨርሲቲዎቹ የመቀበል አቅም ተማሪዎችን ውጤት መሠረት አድርጎ በሚጸም የምልመላ መስፈርት ለዚህ ዓመት ብቻ ወደ ዩኒቨርሲቲዎች ገብተው በልዩ ሁኔታ በደከሙባቸው የትምህርት ዓይነቶች የተሻለ ዉጤት እንዲያስመዘግቡ የሚያስችል ድጋፍ ተደርጎላቸዉ ፈተና ተፈትነው የሚያልፉ ተማሪዎች የከፍተኛ ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉ ይደረጋል ብለዋል። በዚህ የማጠናከሪያ መርሐግብር መሠረት፥ ዩኒቨርሲቲ ከሚቀላቀሉት እና መደበኛ ትምህርት (regular course) ከሚጀምሩ 29,909 ተማሪዎች ውጭ ያሉ ሌሎች ከ100 ሺህ የሚልቁ ተማሪዎች በውጤታቸው ተለይተው እንደ ዩኒቨርሲቲዎች የመቀበል አቅም እየታየ ለአንድ ዓመት የማሻሻያ ትምህርት ወስደው በድጋሚ እንዲፈተኑ ይደረጋል ብለዋል።

    የዚህ ዓመት የ12ኛ ክፍል ፈተና አንድምታ ለዓመታት ሲንከባለል የቆ የበርካታ ችግሮች መገለጫ እና ተሸፋፍኖ የቆየውን እውነተኛ የትምህርት ሥርዓታችን ያለበትን ደረጃ ያመላከተ መሆኑን የሚያሳይ ሲሆን ለዚህም ሁሉም የትምህርት ባለድርሻ አካላት በጋር የሚወስዱት ኃላፊነት በመሆኑ ለቀጣይ ሥራ መረባረብ ይገባል ብለዋል።

    ከዚሁ ጋር በተያያዘ የትምህርት ሚኒስትሩ ከተገኘው የፈተናና የተፈታኞች ውጤት ባሻገር፥ አጠቃላይ ስለ አዲሱ የትምህርት እና ምዘና ሥርዓት አንዳንድ ማብራሪያዎችን ሰጥተዋል። ከዚህ በፊት የነበረው የትምህርት እና ምዘና ሥርዓት በርካታ ብልሹ አሠራሮች እንደነበሩበት ያነሱት ሚንስትሩ፤ የአሁኑ የፈተና ሥርዓት ይህን ብልሹ አሠራር ለማረም የተወሰደ የመጀመሪያ እርምጃ ነው ብለዋል።

    የዚህ ዓመት ውጤት አንድምታ ሲታይ፥ ለዓመታት ከትውልድ ትውልድ ሲንከባለል የተሻገረውን እና ተሸፋፍኖ የቆየውን የትምህርት ሥርዓት ብልሽት የሚያሳይ ነው ብለዋል ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በመግለጫቸው።

    ለዚህም መንግሥት የትምህርት ሥርዓቱን ባለማሻሻል፣ ወላጆች ልጆቻቸውን ባለመከታተልና በሥነ ምግባር ባለመቅረፅ፣ ትምህርት ቤቶች እና ባለሀብቶች በጋራ የወድቀቱ ተጠያቂ ናቸው ብለዋል። ከላይ የተጠቀሱ አካላት ቀጣይ መፍትሄዎች ላይ የአንበሳውን ድርሻ በመውሰድ ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል።

    በ2014 ዓ.ም ከተሰጠው ፈተና እና ተፈታኞች የተገኘው ውጤትአስደንጋጭ እንደሆነ እንረዳለን ያሉት ሚኒስትሩ፥ ነገ የተሻለ ትውልድ ለመፍጠር በዚህ ውስጥ ልናልፍ ግድ ይለናል፤ ይህ የማንቂያ ደወል ሊሆን ይገባል ብለዋል። በበጎ ጎን ከተነሱጥ ነጥቦች መካከል፥ ፈተናው ሙሉ ለሙሉ ከስሮቆት የፀዳ እንደነበረም ተነስቷል።

    የፈተናው አሰጣጥ በብዙ ፈተናዎች ውስጥ ያለፈ እንደሆነ አንስተው፤ በስኬት ለመጠናቀቁ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።

    ምንጭ፦ ትምህርት ሚኒስቴር/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት መግለጫ ከትምህርት ሚኒስቴር

    Semonegna
    Keymaster

    በዲላ ዩኒቨርሲቲ አጠቃላይ ሆስፒታል በመጀመሪያ ዙር መልሶ ግንባታ የተጠናቀቁ ህንፃዎች ተመረቁ
    የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ጠቅላላ ሆስፒታል ደረጃን ለማሻሻል በተሠሩ ሁለተናዊ የለውጥ ሥራዎች በአጭር ጊዜ አበረታች ውጤት እያስመዘገበ መሆኑ ተገለፀ

    ዲላ (ዲላ ዩኒቨርሲቲ እና የጤና ሚኒስቴር) – የዲላ ዩኒቨርሲቲ አጠቃላይ ሆስፒታል ደረጃን ለማሻሻል የሚደረግ የመልሶ ግንባታ አካል የሆኑና በመጀመሪያው ዙር ታድሰው የተጠናቀቁ ህንፃዎች የምረቃ በሥነ ሥርዓት ታኅሣሥ 27 ቀን፥ 2015 ዓ.ምተካሂዷል።

    በዲላ ዩኒቨርሲቲ የሕክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ማስተማሪያ ጠቅላላ ሆስፒታል የእድሳት ግንባታ ሥራ በከፊል ርክክብ ሥነ ሥርዓት ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት በተገኙበት ታህሳስ 27/2015 ዓ.ም ተካሂዷል።

    ከስድስት ወራት በፊት በአገልግሎት አሰጣጥ እንዲሁም በመልካም አስተዳደር እጦት ከፍተኛ የሕብረተሰብ እሮሮ የተነሳበት የዲላ ዩኒቨርስቲ ማስተማሪያ ጠቅላላ ሆስፒታል ከፌደራል እና ክልል ከፍተኛ አመራሮች በተሰጠው አቅጣጫ መሠረት ሁሉን አቀፍ የሥርዓት ማሻሻያ የሪፎረም ሥራዎችና ምቹና ደህንነቱን የጠበቀ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል የሥራ ቦታ ለመፍጠር የግንባታ እድሳት ሥራ በተቀላጠፈ መልኩ እየተከናወነ እንደሆነ በመልስ ምልከታ ማየት ተችሏል።

    የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት እንደገለጹት የዩኒቨርስቲ ማኔጅመንት ባሳለፈው ውሳኔ መሠረት ከሐምሌ ወር መጨረሻ 2014 ዓ.ም ጀምሮ 112 ሚሊዮን ብር በሆነ ወጪ የመማር ማስተማር እና የሕክምና አገልግሎት ሳይቋረጥ በሦስት ዙር እድሳቱ እንዲካሄድ ወደ ሥራ መገባቱን ገልጸዋል።

    በሥነ ሥርዓቱ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የሕክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጠቅላላ ሆስፒታል ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ምፅዋ ሩፎ እንደገለፁት፥ አዲሱ የሆስፒታል አመራር ወደ ሥራ ሲገባ የአሠራር ሥርዓት ክፍተት ስለነበር ክፍተቶችን ለመቅረፍ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ሰፋፊ ሥራዎች እንደተሠሩ እድሳቱንም በቅርብ ክትትል እየተሠራ መሆኑን አብራርተዋል።

    ክብርት ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ሚንስትር እና የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ እንደተናገሩት፥ የሆስፒታሉን አገልግሎት ለማጠናከር በየደረጃው ያለው አመራር ቁርጠኝነት እንደሚፈልግ ገልፀው፤ ለዚህም አስፈላጊ ድጋፍና ክትትል እንደሚደረግ ገልጸዋል።

    በጤና ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ ዶ/ር አየለ ተሾመ የተጀመረው ሪፎርም፣ የ”SBFR” ትግበራ እና የህንፃዎች እድሳት የሆስፒታሉን ደረጃ ከፍ ከማድረግ ባሻገር የጤና አገልግሎት አሰጣጥ መሻሻል እና የጤና ባለሙያው ላይ ከፍተኛ መነቃቃት እንዲሁም የተገልጋይ እርካታን መጨመር መቻሉን ገልፀው ለዚህ ውጤት መምጣት በቁርጠኝነት ለሠሩት የዪኒቨርስቲው፣ የጌዲዮ ዞን፣ የዲላ ከተማና የሆስፒታሉ አመራር አካላት እንዲሁም መላው የሆስፒታል ማኅበረሰብ በተለይም በሥራ አንጋፋ (senior) ሐኪሞችና ነርሶች ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

    በምርቃት ሥነ ሥርዓቱ ላይ አባገዳዎች፣ የጤና ሚኒስቴር፣ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልላዊ መንግሥት ጤና ቢሮ፣ የጌዲዮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ፣ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች፣ የሆስፒታሉ የበላይ አመራሮች፣ የሕክምና ባለሙያዎች፣ የአከባቢው ማኅበረሰብ ተወካዮች፣ ሠራተኞች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ታድመዋል።

    ምንጮች፦ ዲላ ዩኒቨርሲቲ እና የጤና ሚኒስቴር

    ዲላ ዩኒቨርሲቲ አጠቃላይ ሆስፒታል

    Semonegna
    Keymaster

    በሀገር አቀፍ ደረጃ የተቀናጀ የኩፍኝ መከላከያ ክትባት ዘመቻ ተጀመረ 

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ ኢትዮጵያ) – ከታኅሳስ 13 ቀን እስከ ታኅሳስ 22 ቀን፥ 2015 ዓ.ም በሀገር አቀፍ ደረጀ የሚካሄደው የተቀናጀ የኩፍኝ መከላከያ ክትባት ዘመቻ የኩፍኝ በሽታ መከላከያ ክትባት፣ የኮቪድ-med19 መከላከያ ክትባት፣ የአጣዳፊ የምግብ እጥረት ልየታ፣ የቫይታሚን ኤ ጠብታ እደላ፣ የሆድ ጥገኛ ትላትል መድኃኒት እደላ፣ የሕፃናት የዞረ እግር ልየታ እንዲሁም በወሊድ ምክንያት የሚከሰት ፊስቱላ ልየታ በቅንጅት የሚሠራበት ዘመቻ ነው።

    በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ሰርጢ ጤና ጣቢያ የማስጀመሪያ መርሃ-ግብር ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ እንደገለጹት፥ ለእናቶች እና ለሕፃናት ትኩረት ያደረገው የጤና ፖሊሲ ውስጥ አንዱ እና ባለፉት አራት አስርት ዓመታት በትግበራ ላይ የቆየው የክትባት ፕሮግራም መሆኑን ገልፀው፤ እንደሀገር ከ14 በላይ የሚሆኑ የክትባት ዓይነቶችን በመስጠት ዜጎችን ከህመምና ከሞት መታደግ እንደተቻለ ገልጸዋል።

    በሀገራችን በተወሰኑ አካባቢዎች ተከስተው በነበሩ ሰው ሠራሽና ተፈጥራዊ ችግሮች ምክንያት በሥርዓተ ምግብ እጥረት እና በኩፍኝ በሽታ የሚያዙ ሕፃናት ከፍ ብሎ መታየቱን የገለፁት ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ፥ በዚህ ዘመቻ ዕድሜያቸው ከዘጠኝ ወር እስከ አምስት ዓመት የሆኑ ሕፃናትን የኩፍኝ በሽታ መከላከያ ክትባት፣ የአጣፊ የምግብ እጥረት፣ የዞረ እግር ልየታ እንደሚከናወን እና በወሊድ ምክንያት የሚከሰት ፊስቱላ ልየታም ይካሄዳል።

    ሕፃናት በመደበኛ ክትባት መርሃ-ግብር የሚሰጠውን የኩፍኝ በሽታ መከላከያ ክትባት ካልወሰዱ በቀላሉ በኩፍኝ በሽታ የመያዝና ለከፋ የጤና ችግር የመጋለጥ ዕድላቸው ከፍተኛ  ነው ያሉት የእናቶች እና ሕፃናት ጤና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር መሠረት ዘላለም፥ በአሁኑ ጊዜ በሀገራችን  ባለፉት 3 ወራት ብቻ የኩፍኝ በሽታ ወረርሽኝ በ6 ክልሎች የታየ ሲሆን፤ በወረርሽኙም ከተያዙ ውስጥ 47 በመቶ  የሚሆኑት ዕድሜያቸው ከአምስት ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናት ሲሆኑ፥ ከእነዚህም መካከል 46 በመቶ የሚሆኑት ምንም ዓይነት የኩፍኝ በሽታ መከላከያ ክትባት ያልወሰዱ ናቸው ብለዋል። ለዘመቻው እንቅስቃሴ መሳካት አጋርና ለጋስ አካላት ላደረጉት የተቀናጀ አስተዋጽኦ አመስግነዋል።

    በአዲስ አበባ ከተማ ከ5 ዓመት በታች ለሆናቸው ለ520 ሺህ ሕፃናት ክትባቱ እንደሚሰጥም እና በስድስት የመንግሥት ሆስፒታሎች በ101 የመንግሥት ጤና ጣቢያዎች ከሰኞ አስከ አርብ በሥራ ሰዓት እንደሚሰጥ የገለጹት ደግሞ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ዮሐንስ ጫላ ናቸው።

    ሀገር አቀፍ የተቀናጀ  የኩፍኝ መከላከያ ክትባት ዘመቻ  የማስጀመሪያ መርሃ-ግብሩ የጤና ሚኒስቴር እና የአዲስ አበባ ከፍተኛ አመራሮች፣ የሀይማኖት አባቶችና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ተካሂዷል።

    ዘመቻው ለአስር ቀን የሚቆይ ሲሆን ከ15 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ሕፃናት የኩፍኝ መከላከያ ክትባት ተደራሽ የሚሆን ሲሆን፤ የኮቪድ-19 መከላከያ ክትባት መርሃ-ግብርም በተያያዘ የሚከናወን ይሆናል። ለዘመቻው ስኬታማነት በየተዋረድ ያሉ የጤናው ዘርፍ ባለሙያዎችና አመራሮች፣ አጋር ድርጅቶችና የየመገናኛ ብዙኃን አካላት ትብብር እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል።

    ምንጭ፦ የጤና ሚኒስቴር

    የኩፍኝ መከላከያ ክትባት

    Semonegna
    Keymaster

    አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ይዟቸው የመጡ አዳዲስ ነገሮች ምን ምን ናቸው?

    የትምህርት ሚኒስቴር በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ፣ በ2015 ዓ.ም ትምህርት አጀማመር እና በተዛማጅ ጉዳዮች ላይ ለጋዜጠኞች ማብራሪያ ሰጥቷል።

    በያዝነው 2015 ዓ.ም ተግባራዊ የሚደረገው አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ተገቢውን ዕውቀትና ክህሎት ከሥነ ምግባር ትምህርት ጋር አጣምሮ ለመስጠት የሚያስችል በመሆኑ በትምህርት ዘርፉ የሚታዩ ክፍተቶችን ለመሙላት ቁልፍ ሚና እንደሚኖረው በትምህርት ሚኒስቴር የተፈጥሮ ሳይንስ ትምህርት ሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ ወ/ሮ ዛፉ አብርሃ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አብራርተዋል።

    መስከርም 6 ቀን 2015 ዓ.ም የትምህርት ሚኒስቴር ባዘጋጀው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ለጋዜጠኞች ማብራሪያ የሰጡት ወ/ሮ ዛፉ፥ ከዚህ በፊት የነበረው ሥርዓተ ትምህርት የነበሩበት ክፍተቶች በጥናት የተለየ መሆኑንም አክለው ገልፀዋል።

    በመሆኑም አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ሀገር በቀል እውቀትን፣ ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን፣ እንዲሁም ተግባር ተኮር ትምህርትን ከሥነ ምግባር ትምህርት ጋር አቀናጅቶ ለመስጠት እንዲያስችል ተደርጎ የተቀረጸ በመሆኑ በእውቀትና ከህሎት የታነጸ ትውልድ ከመገንባት አንጻር ፋይዳው የጎላ መሆኑን አብራርተዋል።

    በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የአደረጃጀት ለውጥ የተደረገ ሲሆን፥ በዚህም 6፣2፣2፣2 የነበረው አደረጃጀት ቅድመ መደበኛ 2 ዓመት፣ አንደኛ ደረጃ ከ1ኛ እስከ 6ኛ ክፍል (6 ዓመት)፣ መካከለኛ ደረጃ 7 እና 8ኛ ክፍል (2 ዓመት)፣ እንዲሁም 2ኛ ደረጃ ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል (4 ዓመት) /2፣6፣2፣4/ እንዲሆን ተደርጓል።

    በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ከቅድመ መደበኛ እስከ 8ኛ ከፍል አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ የሚደረግ ሲሆን በ9ኛ እና 10ኛ ክፍል ደግሞ የሙከራ ትግበራ በተመረጡ 80 ትምህርት ቤቶች የሚካሄድ መሆኑን ወ/ሮ ዛፉ ገልፀዋል።

    በሌላ በኩል የትምህርት ፕሮግራሞች ጥራትና ማሻሻል መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዮሃንስ ወጋሶ በሀገሪቱ ሁሉም ክልሎች በሚገኙ ትምህርት ቤቶች መስከረም 9 /2015 ዓም ተከፍተው የመማር ማስተማር ሥራ እንደሚጀምሩ አስታውቀዋል።

    በልዩ ልዩ አስገዳጅ ምክንያቶች ሰኞ መስከረም 9 ቀን፥ 2015 ዓ.ም ትምህርት የማይጀምሩ ትምህርት ቤቶች ቢኖሩ ተገቢውን ክትትልና ድጋፍ በማድረግ የመማር ማስተማር ሥራ እንዲጀምሩ እንደሚደረግ ተናግረዋል።

    የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ አመለወርቅ ህዝቅኤል በበኩላቸው ሁሉም እድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ ሕብረተሰቡ የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።

    አምስት ዓመታትን በፈጀውና ከ3 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ የማኅበረሰብ ክፍሎች የተሳተፉበት አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ክለሳ የያዛቸው አዳዲስ ነገሮች

    • አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት በሁሉም የሀገሪቱ ክፍል ባሉ የግል እና የመንግሥት ትምህርት ቤቶች የሚተገበር ቢሆንም፤ ኢንተርናሽናልና የማህበረሰብ አቀፍ ትምህርትቤቶችን አያካትትም፤
    • በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ግብረ ገብ፣ ሀገር በቀል ዕውቀት፣ ሙያና የቀለም ትምህርት፣ ቴክኖሎጂ፣ ምርትና ተግባር፣ ጥናትና ምርምር ትኩረት ተደርጎባቸው እንዲሰጡ ይሆናሉ፤
    • ከአንደኛ እስከ ስድስተኛ ክፍል ላሉ የክፍል ደረጃዎች ትምህርት በአፍ መፍቻ ቋንቋ ይሰጣል፤
    • ከሰባተኛ ክፍል እስከ 12ኛ ክፍል ያሉት ደግሞ ሁሉም ተማሪ በእንግሊዘኛ ቋንቋ ይማራል፤
    • ከአንደኛ ክፍል ጀምሮ እስከ 12ኛ ክፍል ድረስ ያሉት ተማሪዎች የእንግሊዘኛ ቋንቋን እንደ አንድ የትምህርት ዓይነት ይወስዳሉ፤
    • ሦስተኛ ክፍል ላይ ተጨማሪ ቋንቋዎችን መስጠት ይጀመራል፤ በክልሎቹ ውስጥ በስፋት የሚነገረውን ተጨማሪ ቋንቋ በመምረጥ ተማሪዎቹ እንደ አንድ የትምህርት ዓይነት እንዲወስዱት ይደረጋል፤
    • በቀድመው የትምህርት ሥርዓት 10ኛ ክፍል ይሰጥ የነበረው ሀገራዊ የመልቀቂያ ፈተና ይቀርና በምትኩ አጠቃላይ ፈተናው በክልል ደረጃ ስድስተኛ ክፍል እንዲሁም በሀገር አቀፍ ደረጃ ስምንተኛ እና 12ኛ ክፍል ላይ ይሰጣል፤
    • ከዚህ ቀደም ሦስት ዓመት የነበረው የተማሪዎች የዩኒሸርስቲ ቆይታ ደግሞ ዝቅተኛዉ አራት ዓመት ይደረጋል፤
    • ለሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ተማሪዎች በመጀመሪያ ዓመት ከሚሠጡ ትምህርቶች ውስጥ እንደ ጂኦግራፊ፣ አንትሮፖሎጂ፣ ሶሺዮሎጂ እና ሥነ-ምግባር የመሳሰሉት ይካተታሉ፤
    • ከአንደኛ እስከ ስድስተኛ ክፍል የግብረገብ ትምህርት ይሰጣል፤ በተጨማሪም የማኅበራዊና የተፈጥሮ ሳይንስ (social and natural sciences) ውህድ የሆነ ትምህርት ይሰጣል፤
    • ሰባተኛ እና ስምንተኛ ክፍል በተናጠል ይሰጡ የነበሩት ፊዚክስ፣ ኬሚስትሪ እና ባይሎጂ አጠቃላይ ትምህርት ወይም ጀነራል ሳይንስ (general science) ተብለው እንዲሁም ጆግራፊና ታሪክም ተቀናጅተው የሚሰጡ ይሆናል፤
    • የሰባተኛ እና ስምንተኛ ክፍል ተማሪዎች የእርሻ ትምህርት፣ አካውንቲንግ፣ ቢዝነስ እና ጀነራል የሆነውን የሥራና ክህሎት ትምህርት በሙያ ትምህርት ተካቶላቸው የሚሰጣቸው ይሆናል፤
    • 11ኛ እና 12ኛ ክፍሎች ላይ ደግሞ ጤና፣ ግብርና፣ የእርሻ ትምህርት፣ ማኒፋክቸሪንግ፣ ኮንስትራክሽን፣ ቢዝነስ፣ አካውንቲንግ የመሳሰሉት የሙያ ትምህርትነቶችን እንዲማሩ ይደረጋል፤
    • የዘጠነኛ እና የ10ኛ ክፍልን እንዲሁም ከአንድ እስከ ስምንተኛ ክፍል ያሉ የተመረጡ አምስት የትምህርት ዓይነቶችን መጽሐፍት ዝግጅት ትምህርት ሚኒስቴር ያከናውነዋል፤
    • ከአንደኛ እስከ ስምንተኛ ክፍል ያለውን የትምህርት መጽሐፍት ክልሎች በራሳቸው ባህልና አካባቢያዊ ሁኔታ ቃኝተው ያዘጋጁታል።

    ምንጭ፦ የትምህርት ሚኒስቴር/ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት

    አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት

    Semonegna
    Keymaster

    ሳንቴ የሕክምና ኮሌጅ ለ5ኛ ጊዜ ያሰለጠናቸውን የጤና ባለሙያዎች አስመረቀ

    አዲስ አበባ (የጤና ሚኒስቴር) – ሳንቴ የሕክምና ኮሌጅ በአጠቃላይ ሕክምና ዶክትሬት ዲግሪ፣ በጥርስ ሕክምና ዶክትሬት ዲግሪ፣ በሕብረተሰብ ጤና አጠባበቅ በBSc እና MPH ዲግሪ፣ በሕብረተሰብ ጤና አጠባበቅ፣ ኒውትሪሽን በMPH ዲግሪ እና በሥነ-ተዋልዶ ጤና በMPH ዲግሪ ያሰለጠናቸውን የጤና ባለሙያዎች አስመረቀ።

    በምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ በክብር እንግድነት ተግንኝተዉ መልዕክታቸውን ያስተላለፉት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር አየለ ተሾመ እንዳሉት፥ ተመራቂዎች በኮሌጁ ቆይታችሁ ፈታኙን የሕክምናና የጤና ሳይንስ ትምህርት እንዲሁም ሌሎች ተግዳሮቶችን አልፉችሁ ነውና የእናንተን የአካልና የመንፈስ ጥንካሬ ያረጋገጣችሁበት ስለሆነ ላደረጋችሁት ጥረት፣ ውጤታማነት ምስጋናና አድናቆት እንደሚገባቸው ተናግረዋል።

    ዶ/ር አየለ አያይዘውም የተመራቂ ቤተሰቦችንና የኮሌጁ መምህራን እንዲሁም አመራር/አስተዳደር አባላት ተማሪዎች በስኬት መንገድ እንዲጓዙና ውጤታማ እንዲሆኑ ለከፈላችሁት ዋጋ የሚያስመሰግናቸውና የሚያኮራ ተግባር መሆኑን ገልፀው፤ በዛሬው ጊዜ ልጆችን በኃላፊነት አንፆ ለፍሬ ማብቃትና ሀገር ተረካቢ ትውልድ እንዲሆኑ የወላጅ፣ መምህራን እንዲሁም የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ጥረት እንደሚያስፈልግ አንስተው፣ ለትውልድ ቅብብሎሹ ላደረጉት መስዋዕትነት ሀገርም እንደምታመሰግናቸው ተናግረው እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።

    የጤና ሚኒስቴር ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት በዘርፉ የሚስተዋለውን የጤና ባለሙያዎች እጥረት ለመቅረፍ ከትምህርት ሚኒስቴር፣ ከከፍተንኛ ትምህርት ተቋማት፣ እንዲሁም ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ዘርፈ ብዙ ሥራዎች እያከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፥ የጤናና የሕክምና ትምህርት የሚሰጡ በርካታ የመንግሥትና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ወደ ሥራ እንዲገቡ መደረጉን ሚኒስትር ዴኤታው አክለዋል።

    የኮሌጁ ተጠባባቂ ዲን ዶ/ር አህመዲን ኑርሁሴን በበኩላቸው፥ የኮሌጁ ዓላማ ከኮሌጁ ተመርቀው የሚወጡ ባለሙያዎች ሰውን ወዳድ እና አክባሪ፣ አዋቂ፣ በተለያዩ ክህሎቶች የታነፁ፣ ብቁ ለህሙማንና ለማኅበረሰቡ ተቆርቋሪና በጎ አመለካከት ያላቸው ጠቅላላ ሀኪሞች፣ የጥርስ ሀኪሞች፣ ጤና መኮንኖች፣ የሜዲካል ላብራቶሪ ሳይንስ ባለሙያዎች፣ የሕብረተሰብ ጤና አጠባበቅ (ፐብሊክ ሔልዝ)፣ ሥነ ምግብ (ኒውትሪሽን) እና የሥነ-ተዋልዶ ጤና ባለሙያዎችን ማፍራት እንደሆነ ገልፀው፥ ተመራቂዎች ለሀገርና ለወገን ጠቃሚ ትውልድ እንዲሆኑ ትኩረት ተደርጎ እየተሠራ እንደሆነ ጠቁመው ለ5ኛው ዙር ተመራቂዎችና ቤተሰቦቻቸው እንኳን ደስ አላችሁ ብለው መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

    ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ የኮሌጁ የቦርድ አባል በተጨማሪ ባስተላለፉት መልዕክት፥ ተመራቂዎች የተማራችሁት የትምህርት ዓይነት ስለ ሰው ነው፤ ሰው ደግሞ ክቡር የሆነ ህይወትን የተላበሰ ልዩ የሆነ የእርሱ ፍጡር እንደሆነ አንስተው፤ ተመራቂዎች በተማራችሁበት ትምህርት ማኅበረሰቡን ለመርዳትና ሀገራችንን በሕክምናው ዘርፍ የላቀ ደረጃ ለማድረስ ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ የበኩላችሁን አስተዋፅኦ እንድትወጡ በማለት ለተመራቂዎችና ቤተሰቦቻቸው መልካም የምርቃ ጊዜ እንዲሆንላቸው ተመኝተዋል።

    ምንጭ፦ የጤና ሚኒስቴር

    Semonegna
    Keymaster

    ከ350 በሚበልጡ የግል የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ላይ እርምጃ መውሰዱን
    የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን አስታወቀ

    አዲስ አበባ (አዲስ ዘመን) – የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን በ2014 በጀት ዓመት የሥነ-ሥርዓት ጥሰት በፈጸሙ ከ350 በላይ የግል የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ላይ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ። ባለስልጣኑ በበጀት ዓመቱ ከአረጋገጣቸው 10 ሺህ የትምህርት ማስረጃዎች 505 ቱ ሀሰተኛ ናቸው ብሏል።

    የባለስልጣኑ ዋና ዳሬክተር ዶ/ር አንዷለም አድማሴ ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ በ2014 በጀት ዓመት ከየትኛውም በጀት ዓመት የበለጠ የትምህርት ጥራትን ሊጎዱ የሚችሉ ነገሮችን የማጽዳት ሥራ ተከናውኗል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተቋሙን የሥራ እንቅስቃሴ ገምግሞ አቅጣጫ ካስቀመጠ ጊዜ ጀምሮ ከ350 በላይ በሚሆኑ የግል የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ላይ እርምጃ ወስዷል።

    መንግሥት የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ እየወሰዳቸው ካሉ ተጨባጭ እርምጃዎች ውስጥ ሕገ-ወጥ የትምህርት ተቋማትን መቆጣጠር አንዱ ተግባር ነው ያሉት ዶክተር አንዷለም፤ አሁን ላይ የትምህርት ጥራት በኢትዮጵያ ጥያቄ ውስጥ እንዲገባ ካደረጉት ምክንያቶች አንዱ ኃላፊነት የማይሰማቸውና ትርፍን ብቻ አላማ ያደረጉ ሕገ ወጥ የግል የትምህርት ተቋማት መስፋፋት መሆናቸውን ገልጸዋል።

    ተቋምና ፕሮግራም መዝጋት አማራጭ አይደለም ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ ነገር ግን የእውቅና ፈቃድ ሳይሰጣቸው በትውልድ ህይወት የሚነግዱ አካላት ላይ ጥብቅ እርምጃ ይወሰዳል ነው ያሉት።

    እንደ ዶ/ር አንዷለም ገለጻ፥ በርካታ ዜጎች እውቅና በሌለው የግል የከፍተኛ የትምህርት ተቋም ገንዘባቸውን ከፍለው ከተማሩ በኋላ ባለስልጣኑ ማረጋገጫ ሲሠራላቸው ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ሲሆንባቸው ለተመሰቃቀለ ህይወት እየተዳረጉ ነው። በተቋማት ላይ ድንገተኛ ፍተሻ በማድረግ በ355 የግል የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ላይ ከፕሮግራም መዝጋት እስከ ተቋሙን ሙሉ በሙሉ እስከ መዝጋት የደረሰ የማስተካከያ እርምጃ ተወስዷል። ለዚህም መገናኛ ብዙኃን የነበራቸው ሚና ከፍተኛ ነው።

    የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጥ ሥራ በበጀት ዓመቱ በትኩረት ከተሠራባቸው መካከል መሆኑን ያስታወሱት ዶክተር አንዷለም፤ በዘርፉ የጤና ሚኒስቴርና ጉምሩክ ኮሚሽን ለሚቀጥሯቸው ሠራተኞች ቅጥር ከመፈጸማቸው በፊት የትምህርት ማስረጃቸው በባለስልጣኑ እንዲረጋገጥ የሚያደርጉበት አግባብ ለሕገ-ወጥ የትምህርት ማስረጃ ቁጥጥር ጉልህ አስተዋጽኦ አለው ብለዋል። ዕድገትና ቅጥር ሲያከናውኑም በሙሉ ሳያስፈትሹ እንደማያከናውኑ ተናግረዋል።

    ዋና ዳይሬክተሩ የትምህርት ማስረጃ ሲረጋገጥ በቀጣሪ መሥሪያ ቤቶች ተገደው የሚመጡ አካላትን የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጥና ከውጭ ሀገር የተገኘ የትምህርት ማስረጃን አቻ ግምት በመስጠት በሁለት መልኩ የሚረጋገጥ ነው ብለዋል። የማረጋገጥ ሥራ የሚጀምረው ከሀገር አቀፍ ፈተናዎች እንደሆነና በወቅቱ ከነበረው የመቁረጫ ነጥብ በመጀመር እያንዳንዱ የትምህርት ማስረጃ ተፈትሾ እስከ ዲፕሎማና ዲግሪ እንደሚረጋገጥም ጠቁመዋል።

    በ2014 በጀት ዓመት የጤና ሚኒስቴርና የጉምሩክ ኮሚሽንን ሳያካትት ተገደው ከመጡ ከ10 ሺ በላይ የትምህርት ማስረጃዎችን ማረጋገጥ ተችሏል ያሉት ዶክተር አንዷለም፤ ከተረጋገጡት የትምህርት ማስረጃዎች 505 የሚሆኑት ትክክለኛ ያልሆኑ የትምህርት ማስረጃዎች እንደሆኑም ተናግረዋል።

    ፈቃድ ሳያገኙ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ክፉኛ እየጎዱ ያሉ ትውልድን እያቀጨጩ የሚገኙ ሕገ-ወጥ የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ለመቆጣጠር በሚደረገው ሂደት ሕብረተሰቡ ጥቆማ በመስጠት ድጋፍ እንዲያደርግም ዶ/ር አንዷለም ጥሪ አቅርበዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት

    የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን

    Semonegna
    Keymaster

    ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ 2891 ተማሪዎችን በደማቅ ሥነ-ሥርዓት አስመረቀ

    ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች በድህረ ምረቃ፣ በቅድመ ምረቃ እና ዲፕሎማ ፕሮግራሞች ያሰለጠናቸውን 2891 ተማሪዎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ሐምሌ 10 ቀን፥ 2014 ዓ.ም በደማቅ ሥነ ሥርዓት አስመርቋል።

    የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ዶክተር ብርሃነመስቀል ጠና ለዕለቱ ተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ባሰሙበት ንግግራቸው፥ ነባሩ እና አንጋፋው ዩኒቨርሲቲ በመደበኛ፣ በማታና በተከታታይ የዲፕሎማ፣ የዲግሪ እና የማስትሬት መርሐግብሮች ትምህርታቸውን በሚገባ አጠናቀው፣ አስፈላጊውን የምረቃ መስፈርት አሟልተው በዕለቱ ለምረቃ የበቁት የ2014 ዓ.ም ተመራቂዎች 2891 መሆናቸውን ተናግረዋል። ከእነዚህም ተመራቂዎች መካከል ወንድ 1409፣ ሴት ደግሞ 1482 ሲሆኑ፣ ይህም የሴት ተመራቂዎች ቁጥር ብልጫ ያለው መሆኑንና ዩኒቨርሲቲውም ለሴቶች ከፍተኛ ትኩረት እንደሚሰጥ ያሳያል ሲሉ ዶክተር ብርሃነመስቀል ተናግረዋል። በመጨረሻም ፕሬዝዳንቱ የዕለቱ ተመራቂዎች በዩኒቨርሲቲው አዲሱ ስያሜ፣ ተልዕኮ፣ ሎጎ እና ህብረ ዝማሬ በመመረቃቸው የተቋሙ ታሪክ አካል እንደሚያደርጋቸው አስገንዝበዋል።

    የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር እና የዕለቱ የክብር እንግዳ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአዲስ መልክ እየተዋቀረ ያለው ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የሀገሪቱን የትምህርት ችግሮች ለመቅረፍ በከፍተኛ ደረጃ ኃላፊነት የተጣለበት በመሆኑ፣ ይህንን ልዩ ተልዕኮውን ለመወጣት በሚያደርገው ጥረትም የትምህርት ሚኒስቴር አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግለት ገልጸዋል።

    በሥነ ሥርዓቱ ላይም በትምህርታቸው ብልጫ ላሳዩ ተመራቂዎች የዋንጫ እና ሌሎች ሽልማቶች ተሰጥቷቸዋል። እንዲሁም በዩኒቨርሲቲው የሽግግር ወቅት ልዩ ልዩ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላትም የዕውቅና ምስክር ወረቀትና ስጦታ ተበርክቶላቸዋል፡፡

    ከከፍተኛ ትምህርት ዜና ሳንወጣ፥ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጀርመን ስቱትጋርት ከተማ ውስጥከሚገኘው የሆኸንሃየም ዩኒቨርሲቲ (University of Hohenheim) ጋር የአጋርነት ስምምነት ተፈራርሟል።

    የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር አያኖ በራሶ ከዩኒቨርሲቲው የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝደንት እና ከዩኒቨርሲቲው ተመራማሪዎች ጋር በመሆን በጀርመን ሀገር በግብርናና በሥነ ምግብ ሳይንስ ቀዳሚ ከሆነው ከሆኸንሃየም ዩኒቨርሲቲ (University of Hohenheim) ጋር ላለፉት 8 ዓመታት ሲተገበር በነበረው የCLIFOOD ፕሮጀክት ወርክሾፕ ላይ ተሳትፈዋል፡፡ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የግብርና ኮሌጅ ተመራማሪ በዶ/ር ስንታየሁ ይግረም አስተባባሪነት የሚመራው ይህ የCLIFOOD ፕሮጀክት በአየር ንብረት ለውጥና በምግብ ዋስትና ዙሪያ የሚሠራ ሲሆን ለ27 የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የሦስትኛ ዲግሪና የድኅረ-ዶክትሬት (postdoctoral)  ትምህርት እንዲማሩና፣ የዩኒቨርሲቲው የምርምር ላቦራቶሪዎች አቅም እንዲያድግ ከፍተኛ ሚና በመጫወት ላይ ይገኛል፡፡ በዚሁ አጋጣሚ ሁለቱ አንጋፋ የትምህርትና ምርምር ተቋማት ግንኙነታቸውን ለማደስና በሌሎች ዘርፎችም አብረው ለመሥራት የሚያስችላቸውን ውል ተፈራርመዋል፡፡

    ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ

    Semonegna
    Keymaster

    ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ 2891 ተማሪዎችን በደማቅ ሥነ-ሥርዓት አስመረቀ

    ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች በድህረ ምረቃ፣ በቅድመ ምረቃ እና ዲፕሎማ ፕሮግራሞች ያሰለጠናቸውን 2891 ተማሪዎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ሐምሌ 10 ቀን፥ 2014 ዓ.ም በደማቅ ሥነ ሥርዓት አስመርቋል።

    የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ዶክተር ብርሃነመስቀል ጠና ለዕለቱ ተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ባሰሙበት ንግግራቸው፥ ነባሩ እና አንጋፋው ዩኒቨርሲቲ በመደበኛ፣ በማታና በተከታታይ የዲፕሎማ፣ የዲግሪ እና የማስትሬት መርሐግብሮች ትምህርታቸውን በሚገባ አጠናቀው፣ አስፈላጊውን የምረቃ መስፈርት አሟልተው በዕለቱ ለምረቃ የበቁት የ2014 ዓ.ም ተመራቂዎች 2891 መሆናቸውን ተናግረዋል። ከእነዚህም ተመራቂዎች መካከል ወንድ 1409፣ ሴት ደግሞ 1482 ሲሆኑ፣ ይህም የሴት ተመራቂዎች ቁጥር ብልጫ ያለው መሆኑንና ዩኒቨርሲቲውም ለሴቶች ከፍተኛ ትኩረት እንደሚሰጥ ያሳያል ሲሉ ዶክተር ብርሃነመስቀል ተናግረዋል። በመጨረሻም ፕሬዝዳንቱ የዕለቱ ተመራቂዎች በዩኒቨርሲቲው አዲሱ ስያሜ፣ ተልዕኮ፣ ሎጎ እና ህብረ ዝማሬ በመመረቃቸው የተቋሙ ታሪክ አካል እንደሚያደርጋቸው አስገንዝበዋል።

    የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር እና የዕለቱ የክብር እንግዳ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአዲስ መልክ እየተዋቀረ ያለው ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የሀገሪቱን የትምህርት ችግሮች ለመቅረፍ በከፍተኛ ደረጃ ኃላፊነት የተጣለበት በመሆኑ፣ ይህንን ልዩ ተልዕኮውን ለመወጣት በሚያደርገው ጥረትም የትምህርት ሚኒስቴር አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግለት ገልጸዋል።

    በሥነ ሥርዓቱ ላይም በትምህርታቸው ብልጫ ላሳዩ ተመራቂዎች የዋንጫ እና ሌሎች ሽልማቶች ተሰጥቷቸዋል። እንዲሁም በዩኒቨርሲቲው የሽግግር ወቅት ልዩ ልዩ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላትም የዕውቅና ምስክር ወረቀትና ስጦታ ተበርክቶላቸዋል፡፡

    ከከፍተኛ ትምህርት ዜና ሳንወጣ፥ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጀርመን ስቱትጋርት ከተማ ውስጥከሚገኘው የሆኸንሃየም ዩኒቨርሲቲ (University of Hohenheim) ጋር የአጋርነት ስምምነት ተፈራርሟል።

    የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር አያኖ በራሶ ከዩኒቨርሲቲው የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝደንት እና ከዩኒቨርሲቲው ተመራማሪዎች ጋር በመሆን በጀርመን ሀገር በግብርናና በሥነ ምግብ ሳይንስ ቀዳሚ ከሆነው ከሆኸንሃየም ዩኒቨርሲቲ (University of Hohenheim) ጋር ላለፉት 8 ዓመታት ሲተገበር በነበረው የCLIFOOD ፕሮጀክት ወርክሾፕ ላይ ተሳትፈዋል፡፡ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የግብርና ኮሌጅ ተመራማሪ በዶ/ር ስንታየሁ ይግረም አስተባባሪነት የሚመራው ይህ የCLIFOOD ፕሮጀክት በአየር ንብረት ለውጥና በምግብ ዋስትና ዙሪያ የሚሠራ ሲሆን ለ27 የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የሦስትኛ ዲግሪና የድኅረ-ዶክትሬት (postdoctoral)  ትምህርት እንዲማሩና፣ የዩኒቨርሲቲው የምርምር ላቦራቶሪዎች አቅም እንዲያድግ ከፍተኛ ሚና በመጫወት ላይ ይገኛል፡፡ በዚሁ አጋጣሚ ሁለቱ አንጋፋ የትምህርትና ምርምር ተቋማት ግንኙነታቸውን ለማደስና በሌሎች ዘርፎችም አብረው ለመሥራት የሚያስችላቸውን ውል ተፈራርመዋል፡፡

    ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ

    Semonegna
    Keymaster

    በዲላ ዩኒቨርሲቲ የሕክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የሪፈራልና ማስተማሪያ ሆስፒታል የእድሳት ግንባታ ሥራ በይፋ ተጀመረ

    ሰሞነኛ (ዲላ ዩኒቨርሲቲ) – በዲላ ዩኒቨርሲቲ ሕክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የሪፈራልና ማስተማሪያ ሆስፒታል የእድሳት ግንባታ ሥራ ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር ተካሄደ። የእድሳት ሥራው መጀመሩን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ችሮታው አየለ ይፋ አድርገዋል።

    ዶ/ር ችሮታው ባደረጉት ንግግር፥ ሆስፒታሉ ያሉበትን መሠረታዊ ችግሮች በትኩረት መፍታት ከተቋሙ ዋና ዋና ተግባራት አንዱ መሆኑን ገልፀዋል።

    በተለያዩ ሀገራዊና ተቋማዊ ምክንያቶች ግንባታው ቶሎ ያልተጠናቀቀውን አዲሱን የሕክምና እና ማስተማሪያ ሆስፒታል ለማጠናቀቅ ከሚደረገው ጥረት በተጓዳኝ ነባሩን ሆስፒታል በልዩ ሁኔታ እድሳት አድርጎ ለታካሚሆችና ለአካሚዎች ጭምር በሚመጥን ሁኔታ አገልግሎት እንዲሰጥ ለማድረግ ይሠራል ብለዋል ፕሬዝዳንቱ።

    ነባሩ ሆስፒታል አሁን ባለበት ደረጃ የጌዴኦ ዞንን እና አጎራባች አካባቢዎችን ማኅበረሰቦች የሕክምና ፍላጎት ለማስተናገድ ችግሮች እንዳሉ የሚታወቅ መሆኑን የጠቀሱት ዶ/ር ችሮታው፥ ስለሆነም በሆስፒታሉ ሥራ አመራር ቦርድ ታምኖበት አጠቃላይ የእድሳት ሥራው መንግሥት በሚፈቅደው የፋይናንስ ሂደት አልቆ ዛሬ [ሐምሌ 5 ቀን፥ 2014 ዓ.ም] በይፋ እንዲጀመር ተደርጓል ብለዋል።

    ዶ/ር ችሮታው አክለውም፥ እንደ ሀገር ከፍተኛ የሆነ የግንባታ ዘርፉ መቀዛቀዝ ውስጥ ቢሆንም ሆስፒታሉ ካለበት ደረጃ እንዲሁም ከሕብረተሰቡ የሕክምና አገልግሎት አንገብጋቢ ጥያቄ አንፃር አዲሱ እንሰኪጠናቀቅ ነባሩን ሆስፒታል በልዩ ሁኔታና በጥራት አድሶ ጥቅም ላይ ማዋል በትኩረት የሚሠራ ነው ብለዋል። ለዚህም ሥራውን በተቀላጠፈ እና ደረጃውን በጠበቀ ሁኔታ አድሶ የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት የሚመለከተው ሁሉ በርብርብ እንደሚሠራ ተገልጿል።

    የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪና የዩኒቨርሲቲው ሥራ አመራር ቦርድ አባል አቶ አብዮት ደምሴ በበኩላቸው፥ ሆስፒታሉ ለጌዴኦ ዞን ብቻ ሳይሆን ለአጎራባች ክልሎች ጭምር አገልግሎት ሰጪ በመሆኑ “መከፈል ያለበት መስዋዕትነት ሁሉ ተከፍሎ በአጭር ጊዜ ውስጥ እድሳቱ እንዲጠናቀቅ ቦርዱም ሆነ የዞን አመራሩ ጥብቅ ክትትልና ድጋፍ ያደርጋል” ብለዋል። የሥራ ተቋራጭ ድርጅቱ የተጣለበት ኃላፊነት ከፍተኛ መሆኑን ገልፀው፥ የዩኒቨርሲቲው አመራር፣ የዞኑና አካባቢው አመራር እንዲሁም ሕብረተሰቡ በጋራ ተባብረው ውጤታማ የሆነ እድሳት እንዲከናወን ይሠራሉ ብለዋል።

    የዲላ ከተማ ከንቲባና የሆስፒታሉ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ተስፋፅዮን ዳካ በበኩላቸው፥ ሆስፒታሉ ብዙ ማኅበረሰብ የሚገለገልበት ሆኖ ሳለ ከጊዜ ወደ ጊዜ አገልግሎት አሰጣጡ እየተዳከመ ከአቅም በታች የሆነ አገልግሎት እየሰጠ መጥቷል፤ ስለሆነም ከዚህ ችግር እንዲወጣ እና ሕብረተሰቡ ማገኘት ያለበትን አገልግሎት የመስጠት አቅሙን በተሻለ ለመመለስ በርብርብ ይሠራል ብለዋል።

    የእድሳት ሥራውን ለማከናወን ውል የወሰደው ደሳለኝ አሥራደ ህንጻ ሥራ ተቋራጭ የተባለ ድርጅት ሲሆን ተወካዩ አቶ ፍጹም እምሩ ሆስፒታሉ ከአምስት ሚሊዮን ህዝብ በላይ የሚታከምበት ብቸኛ የዞኑ ሆስፒታል እንደመሆኑ የእድሳት ግንባታውን በአጭር ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለማስረከብ በትኩረት እንደሚሰሩ ገልፀዋል።

    ተወካዩ አክለውም የተሻለ ብቃት ያላቸውን ባለሙያዎች በመመደብ በተሻለ ጥራትና በተፋጠነ ጊዜ ግንባታውን አጠናቀው በማስረከብ ሕብረተሰቡ እና ዩኒቨርሲቲው የጣሉብንን አደራ እንወጣለን ነው ያሉት።

    የዲላ ዩኒቨርሲቲ ግንባታ ፕሮጀክት ፅሕፈት ቤት ኃላፊ ኢንጂነር በፍቃዱ መኩሪያ በዕለቱ የእድሳት ግንባታውን አስመልክቶ ባቀረቡት ገለፃ የሆስፒታሉን አጠቃላይ ገፅታ በከፍተኛ ጥንቃቄ ጥናት ተደርጎ ዲዛይን ተሠርቷል ብለዋል።

    ይሄው የእድሳት ዲዛይን ለጤና ሚኒስቴር ቀርቦ ከተገመገመ በኋላ የሚጠበቀውን ደረጃ ማሟላቱ በመረጋገጡ የእድሳት ግንባታው መፈቀዱን ገልፀው፣ በጥናቱ የተለየቱን ችግሮች የሚፈታ እድሳት እንደሚሠራ እና የተወሰኑ ተጨማሪ አዳዲስ ግንባታዎችም እንደተካተቱ አስረድተዋል።

    በእድሳት ግንባታ ሥራ ማስጀመሪያ መርሃግብሩ የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የሆስፒታሉ የሥራ አመራር ቦርድ ኃላፊዎች፣ የዩኒቨርሲቲውና የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሆስፒታሉ ማኅበረሰብ አካላት የተገኙ ሲሆን ግንባታው መጀመሩን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ችሮታው አየለ ይፋ አድርገዋል።

    ምንጭ፦ ዲላ ዩኒቨርሲቲ

    የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሕክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ሆስፒታል እድሳት ተጀመረ

    Anonymous
    Inactive

    የጅማ እና ዲላ ዩኒቨርሲቲዎች ከ7,390 በላይ ተማሪዎችን አስመረቁ

    ጅማ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛ፣ በማታውና በተከታታይ የትምህርት መርሀግብሮች ያሰለጠናቸውን 3,926 ተማሪዎች በደማቅ ሥነ-ሥርዓት ነሐሴ 1 ቀን፥ 2013 ዓ.ም. አስመርቋል።

    በምርቃ ሥነ-ሥርዓቱ የተገኙት የዕለቱ የክብር እንግዳ የኢፌዲሪ የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል ባስተላለፉት መልዕክት፥ ከሀይማኖትና ብሔር ልዩነት ባለፈ ተዋድደንና ተፈቃቅረን እንደኖርነው ሁሉ፣ አሁንም በአንድነት እጅ ለእጅ ተያይዘን የሀገራችንን ብልጽግና እናረጋግጣለን ብለዋል።

    የኢፌዲሪ የጤና ሚኒስትር ዴኤታና የጅማ ዩኒቨርሲቲ ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ በበኩላቸው፥ በቀጣይ ዩኒቨርሲቲውን የላቀ የምርምር ማዕከል ለማድረግ የሥራ አመራር ቦርዱ ተግቶ ይሠራል ብለዋል።

    የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ዶ/ር ጀማል አባፊጣ ባደረጉት ንግግር፥ ከከፍተኛ ትምህርት ተልዕኮዎች መካከል የመጀመሪያው ጥራት ያለው ትምህርት በመስጠት በእውቀት፣ በክህሎት እና በሥነ-ምግባር የዳበረና ሀገር ተረካቢ ዜጋ ማፍራት ነው። ግቡም ተመራቂው ባካበተው የቴክኖሎጂ አቅም ራሱን አብቅቶ ሀገርንና ወገንን መቀየር ሲሆን፥ ጅማ ዩኒቨርሲቲም ይህንኑ ዓላማ እውን ለማድረግ ተግቶ በመሥራት ላይ ይገኛል ብለዋል። ለዚህም ምስክሩ በምርምርና ተቋማዊ አመራር የላቀ ውጤት ማስመዝገቡ ነው በማለት አክልዋል።

    በዕለቱ ከተመረቁት ተማሪዎች መካከል በቅድመ ምረቃ 2,260 ወንድ ሲሆኑ፣ 1234 ሴቶች ተመራቂዎች ናቸው።

    በድኅረ ምረቃ መርሀ ግብር ከተመረቁት 402 ተማሪዎች ውስጥ 318 ወንዶች ሲሆኑ፣ 85 ሴቶች ናቸው፡፡ ከድኅረ ምረቃ መርሀ ግበሩ 18 የሦስተኛ ዲግሪ (ፒ ኤችዲ) ምሩቃን ሲሆኑ፣ በጅማ ዩኒቨርሲቲ ታሪክ ከፍተኛው የሦስተኛ ዲግሪ መርሀግብር ተማሪዎች የተመረቁበት ነው። የሦስተኛ ዲግሪ ተማራቂዎቹ ከሒሳብ፣ ከጤና ግንኙነት (health communication)፣ እና ከኢንፎርሜሽን ሳይንስ ትምህርት ክፍሎች ናቸው።

    በተጨማሪም ጅማ ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያ ዲግሪ መርሀግብር በሶፍትዌር ኢንጅነሪንግና በቪዥዋል አርት (ሥነ-ስዕል) የሰለጠኑ ተማሪዎችን ለመጀመሪያ ግዜ አስመርቋል።

    ከተማሪዎች ምርቃት ጋር በተያያዘ ዜና፥፥ ዲላ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛና በሁለተኛ ዲግር እንዲሁም በተከታታይ መርሀግብር ያሰለጠናቸውን ከ3,450 በላይ ተማሪዎችን እሁድ ነሐሴ 2 ቀን፥ 2013 ዓ.ም. አስመርቋል።

    ዩኒቨርሲቲው ያስመረቃቸው ተማሪዎች 2,101 ወንድና 983 ሴት በድምሩ 3,084 ተማሪዎችን በመጀመሪያ ዲግሪ፤ 317 ወንድና 72 ሴት በድምሩ 384 ተማሪዎችን በሁለተኛ ዲግሪ፤ በአጠቃላይ 3,468 ተማሪዎችን በዕለቱ አስመርቋል።

    የዘንድሮው የዲላ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ምርቃት ለ23ተኛ ጊዜ የተከናወነ ሲሆን፥ ከተመሠረተበት ከ1989 ዓ.ም. ጀምሮ እስካሁን ድረስ ከ71,475 በላይ ተማሪዎችን አሰልጥኖ ለሀገር ኢኮኖሚ የበኩሉን አስተዋጽኦ አበርክቷል። በአሁኑ ወቃትም ከ26ሺህ በላይ የሚሆኑ ተማሪዎችን በመደበኛ እና በተከታታይ የትምህርት መርሀግብሮች እያሰለጠነ  ይገኛል።

    ዩኒቨርሲቲው በዋናው ግቢው ያከናወነው የተማሪዎች ምርቃት ሥነ-ሥርዓት በፋና ቴሌቪዥን በቀጥታ እንደተተላለፈ የዩኒቨርሲቲው የሕዝብ ግንኙነትና ሚዲያ ዘርፍ ዘግቧል።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የጅማ እና ዲላ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎችን አስመረቁ

    Anonymous
    Inactive

    ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ፕሮግራሞች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች በድምቀት አስመረቀ፤ ለቴዲ አፍሮ የክብር ዶክትሬት ሰጠ

    ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ፕሮግራሞች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ሐምሌ 24 ቀን፥ 2013 ዓ.ም በድምቀት አስመረቀ። በዚህ ደማቅ የምረቃ ሥነ ሥርዓት የኢፌዴሪ የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚንስትርና የበዓሉ ልዩ የክብር እንግዳ የተከበሩ ዶ/ር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ፣ አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ)፣ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር አሥራት አጸደወይን፣ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ከንቲባና የዩኒቨርሲቲው ሥራ አመራር ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ሞላ መልካሙ፣ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ብርሀኑ ፈይሳ፣ የቀድሞ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንትና የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ፕ/ር መንገሻ አድማሱ፣ የተለያዩ የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ አባላት፣ የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የተመራቂ ወላጆችና ቤተሰቦች እንዲሁም የዕለቱ ተመራቂዎች ተገኝተዋል።

    በዓመቱ በዩኒቨርሲቲው በተካሄደው በዚህ በሁለተኛው ዙር የተማሪዎች የምረቃ ሥነ ሥርዓት በመደበኛ፣ በተከታታይና በክረምት መርሀግብሮች ወንድ 4153፣ ሴት 2421 በአጠቃላይ 6574 ተማሪዎችን በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ፣ በሦስተኛና በስፔሻሊቲ የትምህርት ደረጃዎች አስመርቋል፤ እንዲሁም ለአንጋፋው የሙዚቃ ሰው አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) የክብር ዶክትሬት ማዕረግ ሰጥቷል።

    የነገ የሀገራችን ተስፋ የሆኑ የዕለቱ ተመራቂዎች በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ፈታኝ ሁኔታዎችን ሁሉ በጽናትና በታላቅ ጀግንነት ተቋቁመው ለዚህች ልዩ ቀን በመድረሳቸው የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክታቸውን የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር አሥራት አጸደወይን አስተላልፈዋል። ተመራቂዎቻችን ወረርሽኙ የፈጠረውን አዲስ ሁኔታ በመቋቋም ለዚህ መብቃታቸውም ልጆቻችን በአስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥም ቢሆን ተፈትነው ማለፍ እንደሚችሉ ከወዲሁ ያረጋገጠ ታሪካዊ አጋጣሚ ነው ሲሉም አክለዋል።

    ፕሬዚዳንቱ እንደገለጹትም በጎርፍ መጥለቅለቅ ለተጎዱ ዩኒቨርሲቲው የቻለው ድጋፍ አድርጓል፤ የወረታ ግብርና ኮሌጅን የሳተላይት ማዕከል አድርጎ ከፍቷል፤ 6ኛው አጠቃላይ ሀገራዊ ምርጫ በሰላም እንዲካሄድ ብዙ ሠርቷል፤ እንቦጭን ለማስወገድ በርካታ ጥረት አድርጓል፤ ከተለያዩ የውጭ ሀገራት ተማሪዎችን ተቀብሎ በማስተማርና ሀገራዊ ትስስርን የመፍጠር ሥራ ተሠርቷል፤ በማይካድራና ሌሎች አካባቢዎች በተደረጉ ዘር-ተኮር ጥቃቶች ላይ በዩኒቨርሲቲው ምሁራን ጥናቶች እየተካሄዱ ነው፤ የኮቪድ ወረርሽኝን ለመከላከል አስፈላጊው ጥንቃቄ እየተደረገ ይገኛል፤ እንዲሁም በገበታ ለሀገር መርሀ ግብር ከገንዘብ ድጋፍ በተጨማሪ በዲዛይን ሥራ እና የጎርጎራ ከተማን መሪ ዕቅድ በማዘጋጀት ትልቅ አስተዋጽኦ እያደረገ ነው። በአጠቃላይ 54 የሚሆኑ የማኅበረሰብ አገልግሎት ፕሮጀክቶች መተግበራቸውን የገለፁት ዶ/ር አሥራት አፀደወይን፥ በዚህ አመርቂ ተግባሩም ዩኒቨርሲቲው የተለያዩ እውቅናና ሽልማቶች ከተለያዩ አካላት እንደተበረከቱለት በመክፈቻ ንግግራቸው አንስተዋል። “ከአባይ ወንዝ የምንቀዳው ፍቅር እንጅ ጥላቻ እንዳልሆነ ለተመራቂ ልጆቻችን በጓዳም በአደባባይም ነግረን አሳድገናቸዋል” በማለትም አለመግባባቶች በሰላም ይፈቱ ዘንድ በአባይ ተፋሰስ ለሚገኙ ሀገራት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

    የኢፌዴሪ የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚንስትርና የበዓሉ ልዩ የክብር እንግዳ የተከበሩ ዶ/ር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ፣ እንደአድዋ በአንድ ያቆመን የአባይን ግድብን የውሃ ሙሌት በድል ባከናወንበት ወቅት በመካሄዱ የዛሬውን ምረቃ ልዩ ያደርገዋል ብለዋል። የራሳችንን የተፈጥሮ ሀብት በአግባቡ ባለመጠቀማችንና ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ማፍለቅና መጠቀም ባለመቻላችን በድህነት እንኖራለን፤ ለዚህ ደግሞ በእውቀት የተደራጀ ኃይል ያስፈልጋል ያሉት ዶ/ር ኢንጅነር ስለሺ በቀለ፥ ስለሆነም ለትምህርት ትልቅ ትኩረት መስጠት አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል። ተመራቂዎች በትምህርት ህይወታቸው ያገኙትን እውቀት በራስ በመተማመን ስሜት ከሁሉም ጋር በመከባበርና በመሥራት ታላቅ የሆነችውን ሀገር ታላቅነቷን ማስጠበቅ እንደሚችሉ ያላቸውን የጸና እምነት በመግለጽ ለተመራቂዎች መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

    የዕለቱ የክብር እንግዳ አያይዘውም የግድቡ ሥራ ሀገር አቀፍና አለማአቀፍ ትኩረትና ድጋፍ እንዲያገኝና በስኬት እንዲጠናቀቅ ላደረገው ጉልህ ሚና ለጎንደር ዩኒቨርሲቲ እውቅና ሰጥተዋል። ሁሉም ሰው በተሰማራበት ሥራ መልካም ውጤት በማስመዝገብ ራስንም፣ ሀገርንም የሚያስከብር መሆኑን ከድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን ሁሉ ሊማር ይገባል በማለት ለአርቲስት ቴዎድሮስ፣ ለተመራቂዎችና ቤተሰቦቻቸው እንኳን ደስ ያላችሁ ብለዋል።

    ምንጭ፦ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ

    ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ለቴዲ አፍሮ የክብር ዶክትሬት ሰጠ

    Anonymous
    Inactive

    የኢፌዴሪ ባህል እና ቱሪዝም ሚኒስቴር በ2013 በጀት ዓመት በባህል ኢንዱስትሪ ልማት ዋና ዋና ክንውኖች
    ሐምሌ 2013 ዓ.ም.
    አዲስ አበባ

    • በባህል ፖሊሲ፣ በቋንቋ ፖሊሲ በባህል እሴቶችና ሀገር በቀል ዕውቀቶች፣ በዕደ ጥበብ ማበልፀግና የገበያ ትስስር ስትራቴጂዎችና አዘገጃጀት ሂደት እና አተገባበር ላይ ከ10 ክልሎች እና ከ2 የከተማ መስተዳድር ለተውጣጡ 53 የባህል ዘርፍ ሙያተኞች እና አስፈጻሚዎች ስልጠና ተሰጥቷል።
    • ከኢትዮጵያ ደረጃዎች ኤጀንሲ ጋር በመተባበር ለባህል ተቋማት በሲኒማ ቤት፣ በቴአትር ቤት እና ቤተ መፃሕፍት ላይ የደረጃ ሰነድ (standard) ተዘጋጅቷል።
    • በኪነጥበብ እና በሥነ ጥበብ ተቋማት ዘርፍ ላይ የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ግለሰቦች የማበረታቻ ሽልማት የሚሰጥበትን አሰራር ሥርዓት በመዘርጋት የመጀመሪያው ሀገር አቀፍ የሽልማትና ዕውቅና መርሃ ግብር በሙዚቃ፣ በቴአትር፣ በድርሰት፣ በሰርከስ፣ በስዕልና ቅርፃ ቅርፅ፣ በፋሽን ዲዛይን፣ በውዝዋዜ እና በፊልም 2013ዓ.ም የሽልማትና ዕውቅና ለመስጠት ሥራዎች ተሠርተዋል።
    • ኢትዮጵያ ያላትን ሀብትና የተፈጥሮ ፀጋ ለማስተዋወቅ እንዲሁም ወደ ኢንቨስትመንት አማራጭ ለመለወጥ ያለመ “የኢትዮጵያ ሳምንት” በወዳጅነት አደባባይ ተካሂዷል። ክልሎች ልዩ መገለጫችን ነው ያሉትን ባህላቸውን በተለያዩ ቅርፃ ቅርፆች፣ በተንቀሳቃሽ ምስሎች እንዲሁም ልዩ ልዩ ጭፈራዎችን በማቅረብ ተከብሯል።
    • የባህል ኢንዱስትሪ መረጃዎችን ለማዘመንና ወጥነት ያላቸው እንዲሆኑ ለማስቻል ከኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽንና ቴክኖሎጂ ጋር በጋራ በመሆን የመረጃ ቋት (ዳታቤዝ) በማዘጋጀት የ2013 ዓ.ም የባህል ኢንዱስትሪ ተቋማትና ሙያተኞች መረጃ ተደራጅተዋል።
    • በባህል ዘርፍ (በባህል፣ በፊልም፣ በቋንቋ ፖሊሲዎችና በእደ ጥበብ ልማት በሀገር በቀል እውቀቶች)፣ በጎጂና መጤ ባህላዊ ድርጊቶች እና ባህል ዘርፍ ተቋማት አከፋፈት የኮቪድ 19 ጥንቃቄና ደህንነት መመሪያን ማስተዋወቅ ሥራ ለ7 ክልሎችና ከሁለት ከተማ አስተዳደር ለተውጣጡ ለ52 አሰልጣኞች የማስተዋወቅ ሥራ ተሠርቷል።
    • ከሙያ ማኅበራት ጋር በመተባበር በኮቪድ ወቅት ጥንቃቄና ደህንነትን መሠረት ባደረገ ሁኔታ የወረርሽኙን አስከፊነት የጥንቃቄ ትኩረትን የሚያስገነዝብና ከ100 በላይ ማስታወቂያዎች (ስፖት) በተለያዩ ሚዲያዎች ተለቋል።
    • የኮቪድ 19 ወረርሽኝን ለመከላከል የባህል ዘርፍ አገልግሎት ተቋማትን ሥራ ለማስጀመር እንዲቻል ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ የአሠራር መመሪያ ተዘጋጅቷል።
    • ለክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች እንዲሁም የባህል ጥበባት ዘርፍ ለባለድርሻ አካላት በሁለት ዙር መድረክ ሥልጠና ተሰጥቷል።
    • በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ የተመለከቱት ሥዕል ኤግዚቪሽን ለሶሰት ቀናት ለሕዝብ ዕይታ ቀርቧል።
    • በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ምክንያት ትምህርት ቤቶች በተዘጉ ወቅት በቤት ተቀምጠው የነበሩ ተማሪዎች እና ሕፃናት የተሳተፉበት የኪነ ጥበብ ፈጠራ ውድድር ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር የአንድ ወር የቴሌቪዥን ፕሮግም ተሠርቷል።
    • ኮቪድ 19 ወረርሽኝን ለመከላከል በተደረገ ዘመቻ ለተሳተፉ አካላትና መመሪያውን ተግባራዊ ላደረጉ ለሁለት ክልልና ለአንድ ከተማ መስተዳድር በድምሩ ለ25 ተቋማት እውቅና የመሥጠት ሥራዎች ተከናውነዋል።
    • የባህል ኢንዱስትሪ ዘርፍ በተመለከተ 6 የአሰራር ሥርዓት ሰነዶችና መመሪያዎች ተዘጋጅተዋል።
    • ከዩኔስኮ በተገኘው ዓለም አቀፋዊና ሀገራዊ ኤክስፐርቶቸች ድጋፍ በመታገዝ የቴክኒክ ኮሚቴ ተቋቁሞ የፈልም ፖሊሲ ማስተገበሪያ (የተቋም ማቃቋሚያ ሰነድ እና የፈልም ፖሊሲ ማስፈጸሚያ ስትራተጂ) ፕሮጀክት እየተከናወነ ነው።
    • የ2005 የዩኔስኮ ኮንቬንሽን ስምምነት መሠረት የ2020 (2012 ዓ.ም.) የሚቀርበውን በየአራት ዓመታቱ የሚዘጋጀውን ሪፖርት ለማጠናቀቅ እንዲቻል ሀገራዊ ኮሚቴውን በማስተባበር በወቅቱ ገቢ ለማድረግ ተችሏል።

    ምንጭ፦ የባህል እና ቱሪዝም ሚኒስቴር

    የኢፌዴሪ ባህል እና ቱሪዝም ሚኒስቴር

Viewing 15 results - 1 through 15 (of 127 total)