Search Results for 'አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ'

Home Forums Search Search Results for 'አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ'

Viewing 15 results - 16 through 30 (of 35 total)
  • Author
    Search Results
  • Anonymous
    Inactive

    በኢትዮጵያ የትምህርትና ስልጠና ሥርዓት አወቃቀር ላይ በሚደረገው ለውጥ ከ1ኛ-6ኛ ክፍል የአንደኛ ደረጃ፤ 7ኛ እና 8ኛ ክፍል መለስተኛ እንዲሁም ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት እንደሚሰጥ የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትሩ አስታውቀዋል።

    አዲስ አባባ (ዶይቼ ቬለ ሬድዮ) – ከመጪው የትምህርት ዓመት (2012 ዓ.ም.) ጀምሮ የአስረኛ ክፍል አጠቃላይ የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና እንደሚቀር የትምህርት ሚኒስትሩ ዶክተር ጥላዬ ጌጤ ተናገሩ።

    በአዲሱ የኢትዮጵያ የትምህርት ፍኖተ-ካርታ መሠረት ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ በሚሆነው አሠራር ለስድስተኛ ክፍል ተማሪዎች ክልላዊ ፈተና ይሰጣል ተብሏል። የትምህርት ሚኒስትሩ ዶክተር ጥላዬ ነሐሴ 15 ቀን 2011 ዓ.ም. በትምህርት ፍኖተ-ካርታ ላይ ረዘም ያለ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

    ሚኒስትሩ አጠቃላይ የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ተብሎ የሚጠራው እና አስረኛ ክፍልን ለሚያጠናቅቁ ተማሪዎች ይሰጥ የነበረው አገር አቀፍ ፈተና ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ እንደማይኖር መናገራቸውን የአዲስ አበባው የዶይቼ ቬለ ሬድዮ ወኪል ዘግቧል።

    ከ1993 ዓ.ም. ጀምሮ ይሰጥ በነበረው አጠቃላይ የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና በአብዛኛው ተማሪዎች ዘጠኝ የትምህርት ዓይነቶች ሲፈተኑ ቆይተዋል። በአገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ አማካኝነት የሚሰጠውን ይኸን ፈተና ያለፉ ተማሪዎች ለተጨማሪ ሁለት ዓመታት ወደ መሰናዶ ትምህርት (preparatory) ይሻገራሉ።

    በኢትዮጵያ የትምህርትና ስልጠና ሥርዓት አወቃቀር ላይ በሚደረገው ለውጥ ከ1ኛ-6ኛ ክፍል የአንደኛ ደረጃ፤ 7ኛ እና 8ኛ ክፍል መለስተኛ እንዲሁም ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ይሰጣል።

    በዚህም መሠረት መጀመሪያ ደረጃ አንደኛ ሳይክል (ከ1ኛ ክፍል እስከ 4ኛ ክፍል)፣ መጀመሪያ ደረጃ ሁለተኛ ሳይክል (ከ5ኛ እስከ 8ኛ ክፍል)፣ ሁለተኛ ደረጃ አንደኛ ሳይክል (9ኛ እና 10ኛ ክፍል) እና ሁለተኛ ደረጃ መሰናዶ ትምህርት (11ኛ እና 12ኛ ክፍል) ተብሎ ሥራ ላይ የነበረው አወቃቀር ይቀየራል።

    በአዲሱ የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት በክልላዊ መንግሥታት የሚሰጥ የስድስተኛ ክፍል ፈተና እንደሚኖር ሚኒስትሩ ተናግረዋል። በኢትዮጵያ የትምህርት ሥርዓት «መጀመሪያ ደረጃ ሁለተኛ ሳይክል» ተብሎ በሚጠራው ምዕራፍ መጨረሻ ለ8ኛ ክፍል ተማሪዎች በክልሎች የሚሰጠው የሚሰጠው ፈተና ሀገር አቀፍ ይሆናል ተብሏል።

    ምንጭ፦ ዶይቼ ቬለ ሬድዮ

    የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – አድማስ ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ የጥራት ደረጃዎች ኤጀንሲ የተዘጋጁት ስታንዳርዶች በተገቢው መልክ በመፈፀም በ2012 ዓ.ም. በተቋም ደረጃ አይ ኤስ ኦ የምስክር ወረቀት (ISO Certificate) ለማግኘት የሚያስችለውን ተግባራት እያከናወነ መሆኑን ገለጸ።

    የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ብሩ አስማረ እንደገለጹት፥ ዩኒቨርሲቲው የትምህርት አሰጣጥ ጥራት ደረጃውን በማሳደግ ለዚሁ ተገቢ የሆነ እውቅና ለማግኘት የሚያስችለው ብቃት ላይ ይገኛል።

    በቴክኒክና ሙያ ኮሌጀች የትምህርት ሥልጠና ጥራት ለማስጠበቅና በየሙያ ደረጃው የሥርዓተ ትምህርት ክለሳ አድርጓል ያሉት ምክትል ፕሬዚዳንቱ የማስልጠኛ መሳሪያዎች (Training Teaching and Learning Materials /TTLM) ዝግጅት በሁሉም የብቃት አሃዶች ማዘጋጀቱንና የትብብር ሥልጠናን አፈፃፃምን የሚያሻሻሉ የተለያዩ ተገባራት እያከናወነ መሆኑን አስረድተዋል።

    አቶ ብሩ አስማረ አያይዘውም የምዘና ሥርዓቱን ለማጠናከርና በዩኒቨርሲቲው የሚተገበረውን የተከታታይ ማጠቃለያና ተቋማዊ ምዘና ዝግጅትና አፈፃፃም ደረጃውን የጠበቀ እንዲሆን መደረጉንም አስረድተዋል።

    በኢትዮጵያ የደረጃ ኤጀንሲ (Ethiopia Standard Agency) የተዘጋጁ የጥራት ምዘናዎችን (stadards) ማለትም የስርዓተ ትምህርት (Curriculum Requirement ES. 6259-1: 2018)፣ የመሣሪያዎች ማሽነሪዎች (Tools, Machines and Equipment Requirement ES 6259-8: 2018)፣ የምዘናና የማሰልጠኛ መሣሪያዎች (Assessment & Instructional Materials ES 6299-9: 2011 ) እና የመሳሰሉትን ተግባራዊ እያደረገ መሆኑን አቶ ብሩ ገልጸዋል።

    ምክትል ፕሬዚዳንቱ አያይዘውም በዩኒቨርሲቲው የሚስጠውን የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና በምርምር ለማገዝ እንዲቻል የተለያዩ ጥናቶች በማካሄድ ያሉ ችግሮችን የመለየት ሥራ በየጊዜው እየተካሄደ መሆኑን ጠቁመዋል።

    በጥቅምት ወር 1990 ዓ.ም. “አድማስ የቢዝነስ ማሰልጠኛ ማዕከል” በሚል ሥራውን የጀመረው ይህ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም፥ በፍጥነት ራሱን በማሳደግ በሚያዝያ ወር 1991 ዓ.ም. የኮሌጅነት ደረጃ አግኝቶ ስሙን “አድማስ ኮሌጅ” ብሎ በመሰየም ሥራውን አስፋፋ። ቀጥሎም በመጋቢት ወር 1999 ዓ.ም. “አድማስ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ” በሚል ስም የትምህርትና የስልጠና ተግባሩን አሳደገ። የከፍተኛ ትምህርት አዋጅ ቁጥር 650/2009 የሚጠይቃቸውን አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅቶች በሙሉ በማሟላት በሐምሌ ወር 2006 ዓ.ም. የሙሉ ዩኒቨርሲቲ ደረጃን አግኝቶ “አድማስ ዩኒቨርሲቲ” ተባለ።

    አድማስ ዩኒቨርሲቲ የዘንድሮን ተመራቂዎችን ጨምሮ ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ከ70 ሺህ በላይ ተማሪዎችን በተለያዩ የትምህርት ዘርፎችና እርከኖች አስመርቋል።

    በአሁኑ ወቅትም በውጭ/ጎረቤት ሀገራት ሶማሌላንድና ፑንትላንድ በሚገኙት ካምፓሶቹ ያሉትን ጨምሮ በጠቅላላው ከ20 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ተቀብሎ እያስተማረ ነው።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    አድማስ ዩኒቨርስቲ የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ብሩ አስማረ


    Anonymous
    Inactive

    አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለ32ኛ ጊዜ 6,857 ተማሪዎችን በደማቅ ሁኔታ አስመርቋል
    —–

    አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች በቅድመ ምረቃና በድኅረ ምረቃ ያሰለጠናቸውን 6,857 ተማሪዎች ሰኔ 29 ቀን 2011 ዓ.ም. አባያ ካምፓስ በሚገኘው አዳራሽ እና ሰኔ 30 ቀን2011 ዓ.ም. በሣውላ ካምፓስ በድምቀት አስመርቋል። ከተመራቂዎች መካከል 4,434 ወንዶች ሲሆኑ 2,423 ሴቶች ናቸው።

    የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ዶ/ር ዳምጠው ዳርዛ በመክፈቻ ንግግራቸው ተመራቂዎች የሥራ ዓለምን ሲቀላቀሉ ከዩኒቨርሲቲው በገበዩት እውቀት፣ ክህሎትና መልካም ሥነ-ምግባር መንግሥትና ህዝብ የአገሪቱን ሰላምና ልማት ለማረጋገጥ እያደረገ ባለው ጥረት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ እንዲሁም ራሳቸውን፣ ወገናቸውንና አገራቸውን ለማሳደግ እንዲተጉ ጥሪ አቅርበዋል።

    የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ እና የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ይናገር ደሴ ለተመራቂዎች ባስተላለፉት መልዕክት ተመራቂ ተማሪዎች በተለያየ መልኩ ወደ ሥራው ዓለም ሲቀላቀሉ በአገራችን የተጀመረውን የለውጥ ሂደት የተሳካ እንዲሆን የበኩላቸውን ጥረት እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።

    በአሁኑ ጊዜ በአገራችን መልካም ተስፋ እየታየ ቢሆንም ተስፋውን የሚያደበዝዙ ችግሮች ይስተዋላሉ ያሉት ዶ/ር ይናገር፥ ችግሮች እንዳይከሰቱና ከተከሰቱም በሰከነ ሁኔታ እንዲፈቱ በማኅበራዊ ሚዲያ ለሚሠራጩ ሀሰተኛ ወሬዎች ቦታ ሳይሰጡ ለአገራችን አንድነትና አብሮነት የዜግነት ግዴታቸውን እንዲወጡም አሳስበዋል።

    የዕለቱ እንግዳና የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ቦርድ አባል ዶ/ር አብርሃም አላኖ በበኩላቸው የአንድ አገር ልማት ያለ ትምህርት መስፋፋት እውን ሊሆን እንደማይችል መንግሥት ተረድቶ ለከፍተኛ ትምህርት ፍትሃዊ መስፋፋትና ተደራሽነት በትኩረት ሲሠራ የቆየ በመሆኑ በዘርፉ አመርቂ ውጤቶች ተመዝግበዋል ብለዋል። መንግሥትና የዘርፉ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት በትምህርት ጥራት ላይ ትኩረት አድርገው እየሠሩ መሆናቸውን የገለፁት ዶ/ር አብርሃም አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲም በአገሪቱ ከሚገኙ የመጀመሪያ ትውልድ ዩኒቨርሲቲዎች መካከል በሁሉም መስኮች ቀዳሚ የመሆን ራዕይ ሰንቆ እየሠራ መሆኑን ገልፀዋል።

    አገራችን ኢትዮጵያ በዕድገት ላይ የምትገኝ አገር መሆኗን ያወሱት የክብር እንግዳው ከለውጡ ጋር ተያይዞ በርካታ መልካም አጋጣሚዎች እንዳሉ ሁሉ ከፍተኛ ተግዳሮቶችና ፈተናዎች የተጋረጡ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህ ረገድ የዕለቱ ተመራቂዎች ምክንያታዊ በመሆንና ከግለኝነት አስተሳሰብ በመውጣት ለማኅበረሳባችን ለውጥ ብሎም አገሪቱ ከገጠማት ፈተና እንድትወጣና የተጀመረው ለውጥ እውን እንዲሆን የበኩላቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል።

    ከአጠቃላይ ተመራቂዎች መካከል 4 ነጥብ በማምጣት የሜዳልያና ዋንጫ ተሸላሚ የሆነው የማርኬቲንግ ማኔጅመንት ተመራቂ እስማኤል ፈድሉ በሰጠው አስተያየት ጠንክሮ መሥራቱና ጊዜውን በአግባቡ መጠቀሙ ለስኬት እንዳበቃው ገልጿል። ማንኛውም ሰው በተሰማራበት መስክ ዓላማ በመሰነቅ በቁርጠኝነት ከሠራ ውጤታማ መሆን ይችላል ያለው ተሸላሚው አሁን ላይ የደረሰበት ደረጃ ጅምር በመሆኑ የትምህርት ደረጃውን በማሻሻል አገሩን በታማኝነትና በቅንንት እንደሚያገለግል ተናግሯል።

    በአጠቃላይ ውጤት 3.98 በማምጣትና 43 A+ በማስመዝገብ በ2ኛነት የተሸለመው የአርክቴክቸርና ከተማ ፕላን ትምህርት ክፍል ተመራቂ ቃለአብ ወንድሙ ታሪኩ በዓላማ መንቀሳቀስና ተግቶ መሥራት ለስኬት ያበቃል ብሏል። ሰሚራ ዲልቦ አወል ከኮኦፕሬቲቭ አካውንቲንግ እና ኦዲቲንግ ትምህርት ክፍል 3.94 ከሴቶች ከፍተኛውን ውጤት በማምጣት እንዲሁም ተመራቂ ዘሀራ ያሲን አማን ከኮምፒውተር ሣይንስ ትምህርት ክፍል 3.92 በማምጣትና 16A+ በማስመዝገብ ልዩ የወርቅ ሀብል ተሸላሚዎች ሆነዋል።

    በዕለቱ ከየትምህርት ክፍላቸው 1ኛ ለወጡ የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች ሽልማት፣ ከኢንስቲትዩት፣ ከኮሌጅና ከት/ቤት 1ኛ ለወጡ ምሩቃን የወርቅ ሜዳልያ፣ ከኢንስቲትዩት፣ ከኮሌጅና ከት/ቤት 1ኛ ለወጡ ሴት ምሩቃን ልዩ ሽልማት፣ በአጠቃላይ ሴት ምሩቃን መካከል ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገበች ምሩቅ የአንገት ሐብል ሽልማት እንዲሁም ከአጠቃለይ ምሩቃን ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገበው ምሩቅ የዋንጫ ሽልማት ተበርክቷል።

    ምንጭ፦ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ

    Semonegna
    Keymaster

    ‹‹የንባብ ባህላችንን እናዳብር፤ ምክንያታዊ ትውልድ እንፍጠር›› በሚል መሪ-ቃል የመጽሐፍት ሽያጭ፣ ዓወደ-ርዕይና ሲምፖዚየም አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ተማሪዎች፣ መምህራን፣ ሠራተኞችና ሌሎች እንግዶች በተገኙበት ተካሂዷል።

    አርባ ምንጭ (AMU) – በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ቤተ-መጽሐፍትና መረጃ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት “የንባብ ባህላችንን እናዳብር፤ ምክንያታዊ ትውልድ እንፍጠር” በሚል መሪ-ቃል የመጽሐፍት ሽያጭ፣ ዓወደ-ርዕይና ሲምፖዚየም ለመጀመሪያ ጊዜ ከሰኔ 3 ቀን እስከ ሰኔ 8 ቀን 2011 ዓ.ም. ተካሂዷል።

    የዝግጅቱ ዓላማ በዩኒቨርሲቲውና በአካባቢው ማኅበረሰብ ዘንድ በንባብ ባህል ዙሪያ ሰፊ ግንዛቤ በመፍጠር እውቀት እንዲስፋፋ እና ልምድ እንዲዳብር ለማድረግ እንዲሁም ማኅበረሰቡ የመጽሐፍትን ጥቅም ተረድቶ ከሌሎች ወጪዎች በመቀነስ የመግዛት ልምድ እንዲቀስም ለማስቻል መሆኑን በዩኒቨርሲቲው የቤተ-መጽሐፍትና መረጃ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዓለምሰገድ ካሣሁን ገልፀዋል።

    የዕለቱ የክብር እንግዳ ገጣሚ፣ ደራሲና መምህር ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ የንባብ ጅማሮ፣ ጥቅምና የመምህራን ሚናን አስመልክቶ ባቀረቡት አንኳር ሀሳብ ንባብ ሊለካ የሚችለው በአንባቢው ላይ በሚያመጣው ዘርፈ ብዙ ለውጥ እንደሆነ ገልጸዋል። ንባብ የተለያየ ነገር ግን የተዋሀደ ይዘት ያለው እንደመሆኑ ማኅበራዊ ተግባቦት እንዲጨምር፣ ተአማኒ እውቀት እንዲዳብር ብሎም ባልኖርንበት ዘመንና ቦታ በምናብ እንድንኖር የሚያደርግ ጥልቅ ምስጢር አለው ብለዋል።

    ጥሩ አንባቢ የአፃፃፍ ስልትና የቃላት አመራረጥን ከመረዳት ባለፈ በሚያነበው ጉዳይ ራሱን የሚመለከትና የሚፈትሽ እንዲሁም የሌሎችንም ስሜት መረዳት የሚችል እንደሆነ ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ ተናግረዋል። ለዚህም መምህራን ከመጽሐፍት ምርጫ አንስቶ መልካም ልምዶችን ለትውልዱ በማካፈል በመረጃ የዳበረና ያወቀ ማኅበረሰብ እንዲፈጠር የበኩላቸውን መወጣት እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል።

    የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ዶ/ር ዳምጠው ዳርዛ በበኩላቸው ለአንድ ማኅህበረሰብ እድገት የተማረ ማኅበረሰብ መፍጠር ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደመሆኑ ላለፉት በርካታ ዓመታት በአገሪቱ ከመሠረተ ትምህርት ጀምሮ እስከ ከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ጥረት ሲደረግ መቆየቱን አውስተዋል።

    ማንበብና መጻፍ ከግለሰብ ባለፈ ለማኅበረሰብ ሁለንተናዊ እድገት ወሳኝ ናቸው ያሉት ፕሬዝደንቱ፥ የንባብ ባህል እንዲዳብር አስፈላጊውን ቁሳቁስ በማሟላት፣ አቅምና ጊዜ በተገቢው በመጠቀም፣ ተፈላጊውን የአዕምሮና የአስተሳሰብ ለውጥ በማምጣት እንዲሁም ምክንያታዊ ትውልድ በመፍጠር ከግለሰብና ከማኅበረሰብ ባለፈ ለአገር ዕድገት አስተዋጽዖ ማበርከት እንደሚቻል ገልፀዋል። በመሆኑም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለንባብ ባህል መዳበር አጽንዖት ሰጥተው ሊሠሩ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።

    የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝደንት ዶ/ር የቻለ ከበደ በበኩላቸው በአገሪቱ ተጨባጭ ሁኔታ ምንም እንኳ ጥንታዊ የሆኑና የተለያየ ዘውግ ያላቸው የስነ-ጽሑፍ ውጤቶች እንዲሁም ወቅታዊ አዕምሯዊ ውጤት የሆኑ የህትመት ውጤቶች ቢኖሩም ከጊዜ ወደ ጊዜ የሚታየው የንባብ ባህል መቀዛቀዝ በመረጃ የበለጸገና ምክንያታዊ የሆነ ዜጋ ከመፍጠር አኳያ እንደ አገር ከፍተኛ ተጽዕኖ የሚያሳድር እንደሆነ ተናግረዋል። በአገሪቱ ለንባብ የሚውለው ጊዜ በዓለም አንባቢ ዜጋ ካላቸው አገራት አንጻር በሣምንት ለንባብ ከሚያውሉት አማካይ ጊዜ በእጅጉ መራቁን የተለያዩ ዓለም አቀፍ ጥናቶች እንደሚያስረዱም ዶ/ር የቻለ ገልፀዋል።

    በማኅበረሰቡ ዘንድ መጽሐፍትን ገዝቶ ከማንበብ ይልቅ የማኅበራዊ ድረ-ገጽ ምርኮኛ መሆን፣ የወረቀትና የህትመት ዋጋ መጨመርና ሌሎችም ለችግሩ መባባስ በምክንያትነት ይጠቀሳሉ። ይሁን እንጂ የንባብ ባህል መዳበር ወሳኝ ጉዳይ በመሆኑ ባህሉ እንዲያንሰራራና መሻሻሎች እንዲመጡ ጠንከር ያለ ጥረትን ይጠይቃል።

    በንባብና ሚዲያ ቴክኖሎጂ ዙሪያ የሚያጠነጥን የውይይት መነሻ ጽሑፍ የዶክትሬት (PhD) ተማሪ በሆኑት አቶ ተመስገን ካሣዬ ቀርቦ ከተሳታፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት ተደርጓል። በዚህም ዘመኑ የቴክኖሎጂና የመረጃ ከመሆኑ ባሻገር የሚዲያ ተግባቦት ባህሎችን ከሌላው ጋር የመቀየጥ አቅም ከፍተኛ እየሆነ መምጣቱ ተገልጿል።

    ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት ንባብ የአንድ ወቅት ሂደት ስላልሆነ በየደረጃው ያለው ሁሉም ማኅበረሰብ ከዋና ሥራው ጎን ለጎን መጽሐፍት ማንበብን ልምድ በማድረግ ከራሱ አልፎ ለሌሎችም መትረፍ የሚያስችል አቅም ማጎልበት እንደሚገባው ገልጸዋል። በተለይም በአገራችን ያሉ ደራሲያን መጽሐፍት ስነ-ጽሑፋዊ ይዘታቸውን ሳይለቁ፣ ታሪክን ሳያዛቡ እንዲሁም በሥነ-ምግባር ረገድ የተሻለ አቀራረብ እንዲይዙ በማድረግ ንቁ ማኀበረሰብ በመፍጠር ለአገራዊ ለውጥ የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ አስተላልፈዋል።

    በመጽሐፍት አውደ ርዕይና ሲምፖዚየሙ የዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ መምህራንና ተማሪዎች እንዲሁም ከአርባ ምንጭ ከተማ እና ከአዲስ አበባ የመጡ የቤተ-መጽሐፍት ባለሙያዎችና የመጽሐፍት ሽያጭ መደብሮች ተሳታፊ ሆነዋል።

    ምንጭ፦ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የንባብ ባህል


    Semonegna
    Keymaster

    የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ  (ኢፌዴሪ) መንግስት ከኔዘርላንድ መንግስት በአዲስ አበባ ከተማ አዲስ የሕፃናት ሆስፒታል ለመገንባት የሚውል የ27.44 ሚሊዮን ዩሮ ድጋፍ ስምምነት ተፈራርሟል። በተጨማሪም የአደጋ (trauma) ሕክምና መስጫ ማዕከል ይገነባል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) የኢትዮጵያ መንግስት ከኔዘርላንድ መንግስት ጋር በመተባበር ከ1.8 ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጭ በአለርቲ ሆስፒታል ግቢ ውስጥ በአይነቱ ልዩ እና የመጀመሪያ የሆነ አዲስ የሕፃናት አጠቃላይ ሆስፒታል ለመገንባት የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረሙ።

    የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስትር ድኤታ ዶ/ር ሊያ ታደሰ በፊርማ ሥነ ስርዓቱ ላይ እንደተናገሩት፥ በሕፃናት ዙሪያ የሚሰጡ የሕክምና አገልግሎቶችን ማሻሻልና ማዘመን አስፈላጊ ከመሆኑ አንጻር ሆስፒታሉ በሕፃናት ዙሪያ ያሉትን ችግሮች ለመቅረፍ የልብ፣ የነርቭ፣ የኩላሊት እንዲሁም ከ30 በላይ የሚደርሱ የሕክምና ስፔሻሊቲ አገልግሎት እንደሚኖሩት ተናግረዋል።

    በአለርት ሆስፒታል ውስጥ የሚገነባው የሕፃናት አጠቃላይ ሆስፒታል በሁለት አመት እንደሚጠናቀቅና 317 አልጋዎች እንደሚኖሩት ወጪውም በኔዘርላንድ መንግስት፣ በአሜርካን ፋውንደሽን እና በኢትዮጵያ መንግስት እንደሚሸፍን በፊርማ ሥነ ስርዓቱ ላይ ተገልጧል።

    ከዚሁ ዜና ጋር በተያያዘ፥ የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነውን የአደጋ (trauma) ሕክምና መስጫ ሆስፒታልን ለመገንባት ከእቴቴ ኮንስትራክሽን ድርጅት ጋር ሚያዝያ 2 ቀን 2011 ዓ.ም. ውል ተፈራርሟል።

    ጤና ሚኒስቴር ከእቴቴ የኮንስትራክሽን ድርጅት ጋር ውል በተፈራረሙበት ወቅት የጤና ሚኒስትሩ ዶ/ር አሚር አማን እንደተናገሩት፥ በተለያዩ ምክንያቶች የሚከሰቱና ለህመም፣ ለአካል ጉዳት እና ለሞት የሚያጋልጡ አደጋዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመሩ በመምጣታቸው በዚህ ዙሪያ የሚሰጡ የሕክምና አገልግሎቶችን ማሻሻልና ማዘመን አስፈላጊ በመሆኑ በድንገተኛ አደጋዎችና ተጓዳኝ ሕክምናዎችን የሚሰጥ ማዕከል በአዲስ አበባ ከተማ አለርት ሆስፒታል ውስጥ ይገነባል ብለዋል።

    ከ751 ሚሊዮን ብር በላይ የተመደበለት እና ባለ 8 ፎቅ የሚገነባለት ይህ ማዕከል በ3 ዓመት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ የታሰበ ሲሆን፤ ከ550 በላይ አልጋዎች የሚኖረውና በቀን ከ2000 እስከ 5000 ተገልጋዮችን ማስተናገድ የሚችል እንደሚሆን ሚኒስትሩ ጨምረው ተናግረዋል።

    የግንባታው በጀት ሙሉ በሙሉ ከመንግስት በመሆኑና ተቋራጩም በተለያዩ የግንባታ ሥራዎች ሰፊ ልምድ ያለው በመሆኑ በግንባታ ሂደቱ ወቅት ያጋጥማል ተብሎ የሚያሳስብ ችግር የለም ተብሏል።

    ምንጭ፦ ጤና ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    የሕፃናት ሆስፒታል


    Semonegna
    Keymaster

    እ.ኤ.አ በ2011 የተመሠረተው ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የሕክምና ዶክተሮችን ሲያስመርቅ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ጊዜ እንደሆነ ተገልጿል። ዩኒቨርሲቲው በአሁኑ ወቅት ስድስት ኮሌጆች፣ አንድ ትምህርት ቤት እና አንድ ተቋም (ኢንስቲትዩት) አለው። 

    ዓዲግራት (ሰሞነኛ)– ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ለመጀመርያ ግዜ ሰባት ሴቶች 25 ወንዶች በድምሩ 32 የሕክምና ዶክተሮችን (medical doctors) እንዲሁም በድኅረ መሠረታዊ መርሃግብር (post basic program) 30 ተማሪዎችን አስተምሮ መጋቢት 1 ቀን 2011 ዓ.ም. አስመርቋል። በዕለቱ የክብር እንግዳ የነበሩ የትግራይ ክልል ም/ር/መስተዳደር ክቡር ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ባስተላለፉት መልዕክት፥ በሃገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች ከፍተኛ የጤና ባለሙያዎች እጥረት እንዳለና ችግሮቻችን በማቃለል አንዳንዱን በመፍታት ልዩነት የሚያመጣ ድርሻ እንደሚኖራችሁ ባለ ሙሉ ተስፋ ነኝ ብለው መልእክታቸው አስተላልፍዋል።

    በዕለቱ የምርቃት ሥነ ስርዓት ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ሚኒስትር ድኤታ ወ/ሮ ስሃረላ ኣብዲላሂ በበኩላቸው የጤና ባለሙያ ማለት የግል ምቾትን እንደ መስዋዕትነት በመክፈል እንብካቤ ለሚያስፈልጋቸው እንክብካቤ መስጠት መሆኑን በማወቅ በየተኛውም የሃገሪቱ ክፍል ሄዳችሁ ያስተማራችሁን ህብረተሰብ ለማገልገል ዝግጁ እንድትሆኑ በማለት ለዕለቱ ተመራቂዎች መልዕክታቸውን አስተላለፈዋል። ዩኒቨርሲቲው የነበሩበትን ፈተናዎች ኣልፈው ለመመረቅ መብቃታችው በጣም የሚያኮራ ታሪክ መሆኑ የዩኒቨርሲቲው ግዝያዊ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ገ/መስቀል ገልፀዋል።

    ኬር ኢትዮጵያ በ7 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር ወጭ ያስገነባውን የምርምርና የስልጠና ማዕከል ለሐረማያ ዩኒቨርሲቲ አስረከበ

    ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የሕክምና ዶክተሮችን ሲያስመርቅ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሆነ ተገልጿል። ዩኒቨርሲቲው የተመሠረተው እ.ኤ.አ በ2011 ሲሆን፥ በአሁኑ ወቅት ስድስት ኮሌጆች፣ አንድ ትምህርት ቤት እና አንድ ተቋም (ኢንስቲትዩት) አለው። ከሁለት ዓመታት በፊት ዩኒቨርሲቲው ባወጣው የአሃዝ ዘገባ በአጠቃላይ ከ16,000 በላይ ተማሪዎች በመደበኛው፣ እንዲሁም ከ6,000 በላይ ተማሪዎች በተከታታይ (continuing education) መርሀ ግብር እያስተማረ ይገኛል።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – STEMpower የተሰኘ መቀመጫውን USA (ሳሌም፥ ማሳቹሴትስ፣ አሜሪካ) ያደረገ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስና እና ሒሳብ ትምህርቶችን በዩኒቨርሲቲዎች እየረዳ የሚገኝ ሲሆን በአገራችን 13 ማዕከላትን ከፍቶ በትብብር እየሠራና እየረዳ ይገኛል።

    ድርጅቱ የድጋፍ አድማሱን በማስፋት በኢትዮጵያ ተጨማሪ 10 ማዕከላትን (ሰባት ማዕከላትን በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች፣ ሶስቱን በተለያዩ ከተሞች እ.አ.አ. በ2019) ለመክፈት ከኢፌዴሪ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር እንዲሁም ከሰባቱ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር የትብብር ስምምነት የካቲት 14 ቀን 2011ዓ.ም. ተፈራርመዋል።

    የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ሂሩት ወልደማርያም (ፕ/ር) STEMpower ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሳይንስና ቴክኖሎጂ ትምህርቶችን ለማበልጸግ እያደረገ ያለውን ትብብር በማመስገን፥ ዩኒቨርሲቲዎችም ዕድሉን በመጠቀም በአግባቡ ማዕከላቱን ማሳለጥ እንደሚጠበቅባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።

    አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በማስተማሪያ ክፍሎቹ ውስጥ ዲጂታል ሰሌዳዎችን መጠቀም ጀመረ።

    የሳንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር) በበኩላቸው ለሰባቱ ዩኒቨርሲቲዎች ፕሬዚዳንቶች (አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲአዲግራት ዩኒቨርሲቲአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲጅማ ዩኒቨርሲቲ እና ወሎ ዩኒቨርሲቲ) ማዕከሉን በመጠቀም በአካባቢዎቻቸው ያሉትን የማኅበረሰብ ችግሮች መፍታት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

    የSTEMpower አስተባባሪ ዳይሬክተርና ፕሬዝዳንት ወ/ሮ ቅድስት ገብረአምላክ፥ “STEMpower ከየት ወዴት?” በሚል ርዕስ ከድርጅቱ አመሠራረት ጀምሮ ዓላማውን፣ አሁን ያለበት ሁኔታ እና የወደፊት ዕቅድ አጭር ማብራሪያ ለተሳታፊዎቹ አቅርበዋል። ለወደፊትም ከሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ጋር በስፋት እንደሚሠሩ ፣ በ2040 የበለጸገች ኢትዮጵያን ማየት እንደሆነ ገልጸዋል።

    አገራችን ኢትዮጵያ የራሷን የሆነ ጥንታዊ ታሪክና ባህል ያላት አገር እንደመሆኗ ድርጅቱ በማኅበራዊ ሳይንስ ላይም ትኩረት እንዲያደርግ ከተሳታፊዎቹ አስተያየት ተሰንዝሯል።

    የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ባደረጉት የመዝጊያ ንግግር ማዕከሎቹ በከፍተኛ ትምህርት እና በሳይንስ ትምህርቶች አከባቢ የሚስተዋሉትን ችግሮች በመቅረፍ የአገሪቱን ብልጽግና ከማረጋገጥ ረገድ መልካም ሁኔታ እንደሚፈጥሩ ገልጸዋል።

    ምንጭ፦ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    STEMpower


    Semonegna
    Keymaster

    የቱሪዝም ማኔጅመንት ትምህርት ክፍል ተማሪዎች ያዘጋጁት የዘንድሮው ውድድር ለ2ኛ ጊዜ የተካሄደ ሲሆን፥ በባለፈው ዓመት የተመረጠችው ወ/ሪት ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በአማራ ክልል በተካሄደው የቁንጅና ውድድር ላይ ተሳትፋ 3ኛ ደረጃ መውጣቷም ተገልጿል።

    ደብረ ብርሃን (ሰሞነኛ)– በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የቱሪዝም ማኔጅመንት ትምህርት ክፍል ተማሪዎች ‹‹ቱሪዝም ለአካባቢ እንክብካቤና ለማኅበረሰብ አቅም መጎልበት›› በሚል መሪ ቃል ሲከበር የቆየው የቱሪዝም ሳምንት ጥር 24/2011 ዓ/ም የቁንጅና ውድድር በማካሄድ ተጠናቀቀ።

    በውድድሩም ወ/ሪት ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ያብፀጋ አይነኩሉ ከሁለተኛ ዓመት የሎጅስቲክና ሰፕላይ ቼን ማኔጅመንት (Logistics and Supply Chain Management) ትምህርት ክፍል ተመርጣለች። በሁለተኛ ደረጃ ተማሪ ኤልሳቤጥ ደስታ የ3ኛ ዓመት የባዮቴክኖሎጂ (Biotechnology) እና በሦስተኛነት ደረጃ ተማሪ ትንሳኤ ፀጋዬ አንደኛ ዓመት የሳይኮሎጂ (Psychology) ትምህርት ክፍል እንደነበሩ ለማወቅ ተችሏል።

    VIDEO: The Yellow Movement AAU: Speaking up for women and girls – empowering women (Ethiopia)

    የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዘዳንት ተወካይ ዶ/ር ጌትነት አሸናፊ በፕሮግራሙ መዝጊያ ላይ ተገኝተው እንደገለጹት የቱሪዝም ማኔጅመንት ትምህርት ክፍል ተማሪዎች ከሳምንት በፊት ጀምሮ በዩኒቨርስቲው ግቢና ውጪ ያለውን አካባቢ በማጽዳት ለሌሎች ምሳሌ የሚሆኑ ተግባራት በማከናወን የቆዩ መሆናቸውን በመግለፅ ላደረጉት በጎ ተግባር ምስጋና አቅርበዋል።

    የቱሪዝም ማኔጅመንት የትምህርት ክፍል ኃላፊ አቶ አብርሃም ኪዳኔ እንደገለፁት የዘንድሮው ውድድር ለ2ኛ ጊዜ የተካሄደ መሆኑን ጠቅሰው፥ በባለፈው ዓመት የተመረጠችው ወ/ሪት ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በአማራ ክልል በተካሄደው የቁንጅና ውድድር ላይ ተሳትፋ 3ኛ ደረጃ በመውጣቷ በርካታ ሽልማቶችን ያገኘች መሆኗን ተናግረዋል።

    በመጨረሻም ለጓሳ ማኅበረሰብ ጥብቅ ስፍራ መታሰቢያነት ‹‹ቱሪዝም ለአካባቢ እንክብካቤና ለማህበረሰብ አቅም መጎልበት›› በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው የቱሪዝም ሳምንት 8 /ስምንት/ ተወዳዳሪዎችን ያሳተፈው የቁንጅና ውድድር ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ደረጃ የወጡትን አሸናፊዎችን በመምረጥና እውቅና በመስጠት በዓሉ ተጠናቋል።

    ምንጭ፦ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ 
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    የቱሪዝም ማኔጅመንት ትምህርት ክፍል


    Semonegna
    Keymaster

    የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጅክቶቹ በገንዘብ ሚኒስቴር የ100 ቀናት ዕቅድ ውስጥ የተካተቱ ሲሆን ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ 798 ኪሎ ዋት የማመንጭት አቅም አላቸው። የፕሮጀክቶቹ ወጪ 795 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር እንደሚገመት በጥናቱ ላይ ተመላክቷል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – በኢትዮጵያ መንግስትና በግል ድርጅቶች (ኢንቨስተሮች) አጋርነት የሚሠሩ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች የኢፌዴሪ የገንዘብ ሚኒስቴር ይፋ አድርጓል።

    ጥር 9 ቀን 2011 ዓ.ም. በገንዘብ ሚኒስቴር በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ እንደተገለፀው ስድስቱ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች በአፋር፣ በሶማሌ፣ በኦሮሚያ እና በትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስታት ስር ይተገበራሉ ተብሏል።

    ስድስቱ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጅክቶች በገንዘብ ሚኒስቴር የ100 ቀናት ዕቅድ ውስጥ የተካተቱ ሲሆን ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ 798 ኪሎ ዋት የማመንጭት አቅም አላቸው። የፕሮጀክቶቹ ወጪ 795 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር እንደሚገመት በጥናቱ ላይ ተመላክቷል።

    የኮምቦልቻ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ የውጪ ንግዱን ለማሳደግ እና የምርት መጠኑን ለመጨመር እየሠራ መሆኑን አስታወቀ

    የገንዘብ ሚኒስቴር ዴኤታ ተሾመ ታፈሰ (ዶ/ር) አገሪቱ መካከለኛ ገቢ ካላቸው አገሮች ተርታ ለመሰለፍ ያስቀመጠችውን ራዕይ ለማሳካት ከዚህም ጋር ተያይዞ በየጊዜው ሳያቋርጥ እያደገ የመጣውን የህዝብ የኃይል አገልግልት ፍላጎት ለማሟላት ከመንግስት የፋይናንስ ምንጮች በተጨማሪ ሌሎች አማራጮችን ማየት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል ሲሉ ገልጸዋል።

    የመንግስትና የግል አጋርነት (መግአ) የመሠረተ-ልማት አቅርቦትን ለማሻሻል እንደ አንድ ስልት የሚወሰድ ነው ያሉት ዶ/ር ተሾመ በአግባቡ ሥራ ላይ ከዋለ የግሉን ዘርፍ የኢንቨስትመንት አቅም እንደ አስፈላጊነቱ ለመጠቀም እድል ይሳጣል ሲሉ ተናግረዋል።

    ምንጭ፦ የገንዘብ ሚኒስቴር/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጅክቶች


    Semonegna
    Keymaster

    የአርሲ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ካስመረቃቸው መካከል 86ቱ የህክምና ዶክተሮች መሆናቸውንና፣ ቀሪዎቹ በጤና መኮንን፣ ክሊኒካል ነርሲንግ፣ ሚድዋይፈሪና በሜዲካል ላቦራቶሪ ሳይንስ መስክ በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ መሰልጠናቸው ተጠቁሟል።

    አሰላ (ሰሞነኛ) – የአርሲ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በህክምና ዶክትሬት፣ በጤና መኮንንና ሌሎች የጤና ትምህርት መስኮች ለ4ኛ ዙር ያሰለጠናቸውን 388 የህክምና እና የጤና ተማሪዎች አስመረቀ።

    የህክምና ሙያ ምሩቃን መከላከል በሚቻል በሽታ (preventable diseases) መሞት እንዲበቃ ጠንክረው በመሥራት ጤንነቱ የተጠበቀ ማኅበረሰብ ለመፍጠር ሊረባረቡ እንደሚገባ የሣይንስና የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትሯ ዶ/ር ሂሩት ወልደማርያም ለተመራቂዎች ባስተላለፉት መልዕክት አሳስበዋል።

    በጤና አገልግሎትና አጠባበቅ ረገድ በሚታየው ውስንነት መዳን በሚቻልባቸው በሽታዎች ሰዎች እንደሚሞቱና ታክሞ መከላከል በሚቻል ሁኔታም የአልጋ ቁራኛ እንደሚሆኑ ያብራሩት ዶ/ር ሂሩት፥ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሥራው ዓለም የሚፈልገውን ብቁና ተወዳዳሪ ዜጋ ከማፍራት አንፃር ትኩረት የሚሹ ቀሪ ሥራዎችን ለመፈጸም መሠራት እንዳለበት አሳስበዋል።

    ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በህክምና እና በነርስነት ይስተማራቸውን 220 ተማሪዎች አስመረቀ

    የአርሲ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዲን ዶ/ር ኑዋማ ቢፋ ኮሌጁ ካስመረቃቸው መካከል 86ቱ የህክምና ዶክተሮች መሆናቸውንና፣ ቀሪዎቹ በጤና መኮንን፣ ክሊኒካል ነርሲንግ፣ ሚድዋይፈሪና በሜዲካል ላቦራቶሪ ሳይንስ መስክ በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ መሰልጠናቸውን ጠቁመዋል። በጤናው መስክ ሀገሪቱ ያለባትን የባለሙያ እጥረት ለማቃለል ዩኒቨርሲቲው ድርሻውን እየተወጣ መሆኑንም ዶ/ር ኑዋማ አመልክተዋል።

    የአርሲ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ዱጉማ አዱኛ ተመራቂዎቹ በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው የቀሰሙትን ዕውቀት ከህይወት ተሞክሯቸው ጋር በማዋሃድ በተሰማሩበት መስክ ኃላፊነታውን መወጣት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

    ከተመራቂዎች መካከል በህክምና ዶክትሬት ዲግሪ ከፍተኛ ውጤት በማምጣት የወርቅ ሜዳልያ ተሸላሚ ዶ/ር አዲሱ ነዲ በሰጠው አስተያየት፥ በሽታን አስቀድሞ መከላከል ላይ መሠረት ያደረገውን የጤና ፖሊሲ ውጤታማ እንዲሆን የሚጠበቅበትን ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን ገልጿል።

    ከሴቶች ተማሪዎች በከፍተኛ ውጤት በማምጣት የተመረቀችው ዶ/ር አያንቱ ሆርዶፋ በበኩሏ በዩኒቨርሲቲው የቀሰመችውን ዕውቀት ወደ ተግባር በመለወጥ ለውጥ ለማምጣት እንደምትጥር ተናግራለች።

    የህክምና ትምህርት የተግባር ትምህርት እንደመሆኑ እርስ በእርስ የነበረ የመማማር ሂደት አሁን ለደረሰችበት ስኬት እንደረዳት ገልጻለች።

    ምንጭ፦ የሣይንስና የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር / ኢዜአ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    የአርሲ ዩኒቨርስቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ


    Semonegna
    Keymaster

    የጊዳቦ ግድብ ሥራ ፕሮጀክት በ258 ሚሊዮን ብር በጀት የተጀመረ ቢሆንም ግንባታው በተያዘለት የጊዜ ገደብ ባለመጠናቀቁ እና የዲዛይን ለውጥ በመደረጉ አጠቃላይ የግንባታ ወጭው 1.66 ቢሊዮን ብር መድረሱን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አስታውቀዋል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢ.ኮ.ሥ.ኮ) በውሃ መሠረተ ልማት ኮንስትራክሽን ዘርፍ እየተገነባ የሚገኘው የጊዳቦ ግድብ ሥራ ፕሮጀክት መቶ በመቶ መጠናቀቁን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ገለጹ።

    የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር አብዱልፈታህ ታጁ በታህሳስ ወር 2011 ዓ.ም. ፕሮጀክቱን ለጎበኙ በኮርፖሬሽኑ የኮርፖሬት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ባለሙያዎች እንደገለጹት የጊዳቦ ዋና ግድብ ሥራ መቶ በመቶ ተጠናቆ በጥር ወር 2011 ዓ.ም እንደሚመረቅ ገልጸዋል።

    የጊዳቦ ግድብ ሥራ ፕሮጀክት በ258 ሚሊዮን ብር በጀት የተጀመረ ቢሆንም ግንባታው በተያዘለት የጊዜ ገደብ ባለመጠናቀቁ እና የዲዛይን ለውጥ በመደረጉ አጠቃላይ የግንባታ ወጭው 1.66 ቢሊዮን ብር መድረሱን አስታውቀዋል።

    በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በብዛት አክሲዮን በመግዛት እየተሳተፉበት ያለውና ግንባታው እይተፋጠነ ያለው ግዙፉ የአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ የኮንፈረንስ ማዕከል

    የግድቡን ዲዛይንና የቁጥጥር ሥራውን ያካሄደው የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ዲዛይንና ቁጥጥር ኮርፖሬሽን ሲሆን፣ ግንባታውን ደግሞ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን አከናውኖታል።

    የኦሮሚያ እና ደቡብ ክልሎችን በመስኖ ተጠቃሚ ያደርጋል ተብሎ የሚጠበቀው የጊዳቦ ግድብ በአጠቃላይ 63.5 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ እና 13,425 ሔክታር መሬት ማልማት ያስችላል የተባለው ይህ የጊዳቦ መስኖ ልማት ግድብ በተያዘለት የጊዜ ገደብ ሳይጠናቀቅ የዘገየው እና የፕሮጀክቱ የገንዘብ መጠኑ የጨመረው ውሉ ከተፈረመ ከሁለት ዓመታት በኋላ ግንባታው መጀመሩ፣ የዲዛይን ለውጥ መደረጉ፣ በአካባቢው የካሳ ክፍያ የሚጠይቁ ሥራዎች መኖራቸው፣ የባለድርሻ አካላት ችግር፣ በግንባታ ዕቃዎች አቅርቦት እጥረት ምክንያት ነው። ግድቡ የተጀመረው በ2002 ዓ.ም. ሲሆን፥ ሲጀመር ይጠናቀቃል ተብሎ የታቀደው በ2004 ዓም ነብር።

    ግድቡ ሲጀመር ተይዞ የነበረው 16 ሜትር ከፍታ ሲሆን አሁን ላይ ወደ 22.5 ሜትር ከፍታ፣ 315 ሜትር ርዝመትና፣ 7.16 ኪ.ሎ ሜትር ርዝመት ያለው በግድቡ ግራ እና ቀኝ የዋና ቦይ ግንባታ ሥራዎችን መሠራቱ እና በአንድ ሺህ አምሳ ሄክታር መሬት ላይ ውሃ እንዳጠራቀመ (ሰው ሠራሽ ሀይቅ እንደሚኖረው) ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል።

    በአሁኑ ወቅት ግንባታው ሙሉ በሙሉ በመጠናቀቁ በሚቀጥለው በያዝነው ወር የፌዴራል፣ የደቡብ እና የኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ ባለሥልጣናት በተገኙበት ይመረቃል ተብሎ መርሐ ግብር ተይዟል።

    ምንጭ፦ ኢ.ኮ.ሥ.ኮ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ 
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    የጊዳቦ ግድብ


    Semonegna
    Keymaster

    አል ማክቱም ፋውንዴሽን በየካ ክፍለ ከተማ ካስገነባው ትምህርት ቤት በተጨማሪ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማም በተመሳሳይ የአፍ መፍቻ ቋንቋቸው አፋን ኦሮሞ የሆኑ ተማሪዎች የሚማሩበት ትምህርት ቤት አስገንብቷል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ተቀማጭነቱን በዱባይ ከተማ ያደረገው አል ማክቱም ፋውንዴሽን የተባለ የተባበሩት አረብ ኤምሬት ግብረ ሰናይ ድርጅት በአርባ ሚሊዮን ብር ወጪ ያስገነባው ትምህርት ቤት ታህሳስ 30 ቀን 2011 ዓ.ም. ተመርቋል። ግብረ ሰናይ ድርጅቱ እስከ አሁን በኢትዮጵያ አራት ትምህርት ቤቶችን ማስገንባቱን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ዘግቧል።

    ትምህርት ቤቱ በየካ ክፍለ ከተማ በተለምዶ አያት አደባባይ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኝ ሲሆን የአፍ መፍቻ ቋንቋቸው አፋን ኦሮሞ የሆኑ ተማሪዎች የሚማሩበት ነው።

    የትምህር ቤቱ የግንባታና የቁሳቁስ ወጪ በግብረ ሰናይ ድርጅቱ የተሸፈነ ሲሆን ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የአስተማሪዎችን ሙሉ የደመወዝ ክፍያም በድርጅቱ የሚሸፈን ይሆናል።

    ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ በትምህርታቸው የላቀ ውጤት ለሚያመጡ ተማሪዎችም ሱዳን በሚገኘው ‘ኢንተርናሽናል ዩኒቨርሲቲ ኦፍ አፍሪካ’ በተሰኘው ዓለም አቀፍ ትምህርት ቤት የነፃ የትምህርት ዕድል ተጠቃሚ እንደሚሆኑም የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ታቦር ገብረመድህን በምርቃት ሥነ ሥርዓቱ ላይ ተናግረዋል።

    በተጨማሪም ለመምህራን የትምህርት ዕድል ለመስጠትና ከሌሎች የአፍሪካ አገራት ጋር የመምህራን የልምድ ልውውጥ ለማድረግ መታቀዱንም ጠቁመዋል። የትምህርት ቤቱን የቅበላ አቅም ለማሳደግ የማስፋፊያ ሥራ ለመሥራት ዝግጅት መጠናቀቁንም ዶ/ር ታቦር ተናገረዋል።

    የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር ከድር ጃርሶ በበኩላቸው ትምህርት ቤቱ የአፍ መፍቻቸው አፋን ኦሮሞ ለሆኑ እና ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ወላጆች ልጆች የትምህርት ዕድል ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው ብለዋል። እንዲሁም ትምህርት ቤቱ በአካባቢው መከፈቱ ለበርካታ ሥራ አጥ ኢትዮጵያውያን የሥራ ዕድል የፈጠረ መሆኑንም ገልጸዋል።

    የአል ማክቱም ፋውንዴሽን የኮሙኒኬሽን ባለሙያ አቶ አብዱልሸኩር መንዛ እንዳሉት ግብረ ሰናይ ድርጅቱ በኢትዮጵያ የትምህርት ዘርፍ የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ በማጠናከር በሌሎች ዘርፎች ለመሥራትም ዕቅድ አለው።

    ግብረ ሰናይ ድርጅቱ በኢትዮጵያ የትምህርት ዘርፍ መጠናከር የአገሪቱ መንግስት ላደረገው ቀና ትብብርም አቶ አብዱልሸኩር አመስግነዋል።

    አል ማክቱም ፋውንዴሽን በየካ ክፍለ ከተማ ካስገነባው ትምህርት ቤት በተጨማሪ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማም በተመሳሳይ የአፍ መፍቻ ቋንቋቸው አፋን ኦሮሞ የሆኑ ተማሪዎች የሚማሩበት ትምህርት ቤት አስገንብቷል።

    በሁለቱም ክፍለ ከተሞች የተገነቡት ትምህርት ቤቶች በአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ስር እንዲተዳደሩ የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ አስረክቧል።

    ምንጭ፦ ኢዜአ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    አል ማክቱም ፋውንዴሽን


    Semonegna
    Keymaster

    ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ አስተማማኝ ሠላም በዘለቄታ እንዲረጋገጥ ከተለያዩ ማኅበረሰብ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሠራ መሆኑን፣ የሀገሪቱ አቅም በሚፈቅደው ደረጃ የተለያዩ ግብዓቶችን ማሟላትን ጨምሮ ሌሎች አስፈላጊ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)–በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ተከስቶ የነበረው የሰላም መደፍረስ ችግር በአሁኑ ሰዓት እየተስተካከለ መሆኑን የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር ሒሩት ወልደማርያም ገለጹ።

    ዶ/ር ሒሩት ባለፈው ሳምንት ለተለያዩ መገናኛ ብዙኃን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፥ በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች መደበኛው የመማር ማስተማር ሥራ መጀመሪያ አከባቢ በሰላማዊ ሁኔታ ተጀምሮ የነበረ ሲሆን በሂደት ግን የአገራችን ለውጥ ያልተዋጠላቸው አካላት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ማዕከል በማድረግ ግጭቶችን በማስፋፋት ሠላም እንዳይኖር ታስቦ እንደ ነበር ተደርሶበታል ብለዋል።

    ተመሳሳይ ዜና፦ ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ በቂ ዝግጅት በማድረግ አዳዲስ ተማሪዎችን መቀበሉን አስታወቀ

    ግጭቶቹ በግል ደረጃ በተማሪዎች ጠብ ተጀምሮ ወደ ብሔር እንዲያድግም ታስቦ እንደነበርና፥ አሁን ግን ከተለያዩ የትምህርት ባለድርሻ አካላት ከሃይማኖት አባቶች፣ ከአገር ሽማግሌዎች፣ ከዩኒቨርሲቲ ቦርድ አባላት፣ ከዩኒቨርሲቲው አመራር፣ ከአካባቢው ማኅበረሰብ፣ ከጸጥታ አካላት ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ፥ ዩኒቨርሲቲዎች ወደ መደበኛ ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲመለሱ እየተደረገ ይገኛል ያሉት ሚኒስትሯ፥ ለዚህም በዩኒቨርሲቲ ቦርድ እንዲሳተፉ ከተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች ጭምር ብቁ ምዑራን መመልመላቸውን፣ ሴቶችም በጉዳዩ እንዲሳተፉ ሀምሳ በመቶ (50%) ያህሉ ሴቶች በቦርድ እንዲመረጡ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።

    በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ረዘም ላለ ጊዜ ትምህርት ተቋርጦ የነበረ ሲሆን፥ አሁን ግን ከተለያዩ አካላት እና ከተማሪዎች ጋር በተደረገ ውይይት ከጥር 1 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ ተማሪዎቹ በመደበኛ የትምህርት ገበታቸው እንደሚገኙ ከስምምነት መደረሱን ሚኒስትሯ አክለው ገልጸዋል።

    የዩኒቨርሲቲዎች አስተማማኝ ሠላም በዘለቄታ እንዲረጋገጥ ከተለያዩ ማኅበረሰብ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሠራ መሆኑን፣ የሀገሪቱ አቅም በሚፈቅደው ደረጃ የተለያዩ ግብዓቶችን ከማሟላት በተጨማሪ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የተለያዩ ምሁራንን በመጋበዝ የተማሪ ሥነ-ልቦና ላይ በመሥራት በተማሪዎች ዘንድ የተወዳዳሪነት ስሜት እንዲፈጠር ሥራዎች እየተሠሩ መሆኑንም ክብርት ሚኒስትሯ ገልጸዋል።

    ምንጭ፦ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር | ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ


    Semonegna
    Keymaster

    አርባ ምንጭ (ሰሞነኛ)– ከ875 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ ተደርጎበት በ2007 ዓ.ም. በ6 ሄክታር መሬት የግንባታ ሥራው የተጀመረውና በ2 ዓመት ከ5 ወር ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ የታቀደው የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ዘመናዊ የማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል በአገራዊ የገንዘብ ግሽበትና የእቃዎች ዋጋ መናር ምክንያት በተያዘለት የጊዜ ገደብ ሊጠናቀቅ አለመቻሉን የዩኒቨርሲቲው የቢዝነስና ልማት ምክትል ፕሬዝደንት ጽ/ቤት ገለጸ።

    የቢዝነስና ልማት ምክትል ፕሬዝደንት ተወካይ ወ/ሮ ታሪኳ ወልደመድኅን እንደገለጹት ነባር የግንባታ ፕሮጀክቶችን ለማስጨረስ ዩኒቨርሲቲው በ2011 ዓ.ም. በጀት ዓመት ከጠየቀው 450 ሚሊየን ብር በጀት በፌዴራል መንግሥት የተፈቀደው 166 ሚሊየን ብር ብቻ ሲሆን ይህም ገንዘብ ቢሆን በወቅቱ ሊለቀቅ አልቻለም። የበጀት ችግሩ እንዳለ ሆኖ ከተቋራጭ ድርጅቱ ጋር መግባባት በመፍጠር በተቻለ መጠን ሥራዎች አየተሠሩ መሆኑን ተወካይዋ ተናግረዋል።

    ከአገር አቀፍ የገንዘብ እጥረቱ በተጨማሪ የዲዛይን ሥራዎች እና በሆስፒታሉ ዙሪያ የድንበር ማካለሉ ሥራ ሙሉ ለሙሉ አለመጠናቀቅ ግንባታው በተያዘለት የጊዜ ገደብ እንዳይጠናቀቅ ካደረጉ ምክንያቶች ዋናዎቹ ናቸው። ድንበር ማካለሉን አስመልክቶ በሆስፒታሉ ዙሪያ ከይዞታቸው ተነሺ ከሆኑ 60 መኖሪያ ቤቶች ለ47ቱ ከከተማው ማዘጋጃ ቤት ጋር በመሆን ተመጣጣኝ ተለዋጭ የመኖሪያ ቦታ ተመርጦ የዲዛይኑ ሥራ ያለቀ ሲሆን በዩኒቨርሲቲውና በከተማው ማዘጋጃ ቤት ትብብር ለነዋሪዎች የመኖሪያ ቤት ግንባታ ለማከናወን በሂደት ላይ ነው። ለቀሪዎቹ ተነሺ ነዋሪዎችም ለመኖሪያ ቤት የሚሆን የቦታ መረጣ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

    ◌ ተመሳሳይ ዜና፦ ጅማ ዩኒቨርሲቲ ያስገነባው ዘመንዊ የህክምና ማዕከል ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ሌሎችች ባለስልጣናት በተገኙበት ተመረቀ

    የሆስፒታሉን ግንባታ በማከናወን ላይ የሚገኘው ይርጋለም ኃ/የተ/የግል ማኅበር መሀንዲስ ይህደጎ ተስፋዬ እንደተናገሩት የግንባታ ሥራዎች በታቀደላቸው ጥራት በመከናወን ላይ ቢገኙም በዩኒቨርሲቲው በኩል የሚለቀቀው ገንዘብ ወቅቱን ጠብቆ አለመድረስ፣ በአማካሪው በኩል የዲዛይን ሥራዎች ሙሉ በሙሉ አለማለቅ እንዲሁም የድንበር ወሰን ማካለል ችግር ግንባታው በተያዘለት የጊዜ ገደብ ውስጥ እንዳይጠናቀቅ ምክንያቶች ሆነዋል። የጋዝና የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሲስተሞቹ በሪፈራል ሆስፒታል ግንባታዎች ከተሰማራንባቸው ዩኒቨርሲቲዎች የተሻለ ዘመናዊነትን የተላበሱ ናቸው ያሉት መሀንዲሱ፥ በአጠቃላይ ሊገነቡ ከታሰቡት 11 ግንባታዎች የሪፈራል ሆስፒታሉ ዋና ህንፃ፣ የአካል ጉዳተኞች መወጣጫ እንዲሁም የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎች ብቻ ግንባታቸው ከ90% በላይ መድረሱን ገልጸዋል።

    አካል ጉዳተኞችን ታሳቢ በማድረግ 7 የመወጣጫ ሊፍትና 400 አልጋዎች ያሉት ዘመናዊው ሆስፒታል በውስጡ መረጃዎች በዘመናዊ መልክ የሚደራጁበት ዳታ ሲስተም (Data System)፣ ህመምተኞች በቀላሉ የህክምና ባለሙያዎችን የሚጠሩበት ነርስ ኮል ሲስተም (Nurse Call System)፣ የሆስፒታሉን ደኅንነት የሚቆጣጠሩ ዲጂታል ካሜራ ሲስተም (Digital Camera System)፣ ታካሚዎችን የሚያዝናኑና በቂ መረጃን የሚሰጡ የቴሌቪዥን ሲስተም (TV System) እና መሰል ዘመናዊ ሲስተሞች የተገጠሙለት ነው።

    የዘመናዊውን የማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል ግንባታ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ዲዛይንና ሱፐርቪዥን ሥራዎች ኮርፖሬሽን የማማከር ሥራ የሚሠራለት ሲሆን ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር ለመማር-ማስተማር ሂደት አጋዥ ከመሆኑም በተጨማሪ ለምርምር ሥራ መዳረሻ እንደሚሆን ይሆናል።

    ምንጭ፦ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ | ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ሆስፒታል

    Semonegna
    Keymaster

    ጂንካ ዩኒቨርሲቲ ለተለያዩ ትምህርት ቤቶች ከሚያደርገው ድጋፍ በተጨማሪም በሌሎች የማኅበረሰብ-አቀፍ አገልግሎቶች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ዩኒቨርሲቲው አቅዶ እየሠራ መሆኑን ተገልጿል።

    ጂንካ ከተማ፣ ደቡብ ኦሞ ዞን (ሰሞነኛ) – ጂንካ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ተገንብተው በ2010 ዓ.ም. ወደ ሥራ ከገቡት ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ አንዱ ሲሆን ዩኒቨርሲቲው ምንም እንኳን ከተመሰረተ አጭር ጊዜ ቢሆንም የተሰጠውን ተልዕኮ ለማሳካት በርካታ ሥራዎችን እየሠራ ይገኛል።

    ዩኒቨርሲቲው በማኅበረሰብ-አቀፍ አገልግሎት (community-based service) በደቡብ ኦሞ ዞን ውስጥ ለሚገኙ 18 ሁለተኛ ደረጃ እና አንድ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት በጥቅሉ ለ19 ትምህርት ቤቶች 510 ኮምፒዩተሮችን ከአንድ ደርጅት እንዲሁም በውጭ ሀገር ከሚኖር አንድ የአካባቢው ተወላጅ ጋር በመተባበር ለእያንዳንዳቸው ሃያ አምስት፣ ሃያ አምስት ኮምቲዩተሮችን ለትምህርት ቤቶቹ የሰጠ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ፕ/ር ገብሬ ይንቲሶ ገልጸዋል።

    ፕሬዚዳንቱ አክለውም እነዚህ ኮምፒዩተሮች ተማሪዎቹ ከቴክኖሎጂ ጋር እንዲተዋወቁ ከማድረጋቸውም በተጨማሪ በሁሉም ኮምፒዩተሮች ላይ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር የሚያዘጋጃቸው የመማሪያ መጽሐፍት እና ሌሎች አጋዥ ሊሆኑ የሚችሉ ሶፍትዌሮች የተጫኑባቸው በመሆኑ ተማሪዎቹ በቀላሉ የሚፈልጉትን ለማግኘት እንደሚያስችላቸው ተናግረዋል። ለዚህም ይረዳ ዘንድ ለICT (information, communication and technology) እና ሂሳብ መምህራን በICT አጠቃቀም ዙሪያ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተሰጥቷቸው ወደ ሥራ እንዲገቡ ተደርጓል ብለዋል ፕሬዚዳንቱ ።

    ድጋፍ የተደረገላቸው ትምህርት ቤት ርዕሳነ መምህራን በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው አዲስ የተከፈተ ቢሆንም ለየትምህርት ቤቶቹ የተደረገው ድጋፍ የመማር ማስተማር ሂደቱን ከማሳለጥ አንፃር ትልቅ አስተዋጽኦ የሚያበረክት ነው ያሉ ሲሆን፥ በቀጣይ ትምህርት ቤቶችን በመደገፍ የትምህርት ጥራት ለማረጋገጥ በሚደረገው ርብርብ ዩኒቨርሲቲው የራሱን አስተዋጽኦ አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል።

    ጂንካ ዩኒቨርሲቲ ለትምህርት ቤቶች ከሚያደርገው ድጋፍ በተጨማሪም በሌሎች የማኅበረሰብ-አቀፍ አገልግሎቶች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ዩኒቨርሲቲው አቅዶ እየሠራ መሆኑን የገለፁት የዩኒቨርሲቲው ቢዝነስ ልማት ምክትል ፕሬዚዳንት ወ/ሮ ነፃነት ይርጉ ሲሆኑ ከብት በማደለብ፣ በከብቶች ህክምና፣ በዶሮ እርባታበንብ እርባታ፣ በአሳ እርባታ በመሳሰሉት ውጤታማ ሥራዎችን ለመሥራት አቅዶ በተግባር እየተንቀሳቀሰ መሆኑን አስረድተዋል።

    ምንጭ፦ የትምህርት ሚኒስቴር
    ——
    See also:

    ትምህርት ቤቶች


Viewing 15 results - 16 through 30 (of 35 total)