Search Results for 'በላይነህ ክንዴ'

Home Forums Search Search Results for 'በላይነህ ክንዴ'

Viewing 6 results - 1 through 6 (of 6 total)
  • Author
    Search Results
  • Semonegna
    Keymaster

    ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ሁለተኛውን የምገባ ማዕከል ለማቋቋም የስምምነት ሰነድ ተፈራረመ

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ከአዲስ አበባ ሴቶች ሕፃናትና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ጋር ለድርጅቱ ሁለተኛውን የምገባ ማዕክል (ተስፋ ብርሀን አሙዲ ቁጥር 2) ለማቋቋም የስምምነት ሰነድ ሰኔ 8 ቀን 2014 ዓ.ም. ተፈራርሟል።

    በከተማዋ የሚገኙ በቀን አንድ ጊዜ መመገብ ለማይችሉ ዜጎች ጤናውን የጠበቀ ምግብ እንዲያገኙ ስድስት የምገባ ማዕከላት መገንባታቸውን ከተማ አስተዳደሩን በመወከል የስምመነት ሰነድ የተፈራረሙት የአዲስ አበባ ሴቶች ሕፃናትና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሀና የሺንጉስ ተናግረዋል።

    መንግሥት ከድርጅቶችና ግለሰቦች ጋር በመተባበር ስራዎች እያከናወነ መሆኑን የተናገሩት ኃላፊዋ ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ከዳሽን ባንክ ኃ.የተ.የግ.ማ. ጋር በመተባበር ለከተማችን ሰባተኛ ለድርጅቱ ደግሞ ሁለተኛ የሆነ የምገባ ማዕከል ለማቋቋም አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ማጠናቀቁን ገልጸዋል፤ ለዚህ የሚውል የ40 ሚልየን ብር ወጪ ለማድረግ የስምምነት ሰነድ መፈራረሙንም አስረድተዋል።

    በሚድሮክ ኢቨስትመንት ግሩፕ የኮርፖሬት ማኅበራዊ ኃላፊነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር የሆኑት አምባሳደር አሊ ሱለይማን በበኩላቸው ሀገራችን እያስተናገደችው ያለው ማኅበራዊ ችግር በሀገሪቷ ብሎም በከተማዋ ድጋፍ የሚሹ ዜጎችን ቁጥር ከፍ አድርጎታል ብለዋል። ለዚህም ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ባለፈው ዓመት “ተስፋ ብርሀን አሙዲ” የተሰኘ የምገባ ማዕከል በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ አቋቁሞ እየሠራ መሆኑን አስታውሰዋል።

    በዚህ ሰዓትም ቁጥር ሁለት ተስፋ ብርሀን አሙዲ የምገባ ማዕከልን በልደታ ክፍለ ከተማ በመገንባት ማኅበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ስራ መጀመሩን ገልፀዋል።

    በስምነት ሰነዱም ቢሮው የመገንቢያ ቦታ የማመቻቸት፣ ከቦታው ጋር ተያይዘው ለሚነሱ የሦስተኛ ወገን የመብት ጥያቄ ኃላፊነት ወስዶ ለማመቻቸት እና የተመጋቢ ምልመላና መረጣ የመሳሰሉ የከተማ አስተዳደሩ ኃላፊነቶችን እንደሚወጣ ተገልጿል።

    ሚድሮክ የኢንቨስትመንት ግሩፕ ከዳሽን ባንክ ኃ.የተ.የግ.ማ. ጋር በመተባበር በሚገነቡበት ቦታ ላይ የሚገኙና በዝቅተኛ ኑሮ ለሚኖሩ ስምንት አባወራዎች ስምንት የመኖሪያ ቤቶች ለመገንባት እንዲሁም ባሉበት የልማት ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚያስችላቸውን 16 የሱቅ ቤቶች በመገንባት ለማስረከብ እንደሚሠራምዳይሬክተሩ ተናግረዋል።

    ከዚህም በተጨማሪ በምገባ ማዕከሉ ቅጥር ግቢ ያለውን ክፍት ቦታ በከተማ ግብርና ለማልማትና የልማቱን ውጤትም ለተመጋቢዎች በምግነት እንዲጠቀሙ ለማድረግ እንደሚሠራ በሚድሮክ በኩል ስምምነቱን የፈረሙት አምባሳደር አሊ አረጋግጠዋል።

    በተያያዘ ዜና፥ ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ (ኢትዮ አግሪ ሴፍት ኃላ/የተ/የግል ማኅበር) እና በላይነህ ክንዴ ግሩፕ (ፊቤላ ኢንዱስትሪስ ኃላ/የተ/የግል ማኅበር) በጥምረት በአማራ ክልል ምዕራብ ጎጃም ዞን ውስጥ በምትገኘው ማንኩሳ ከተማ ያስገነቡት ዘመናዊ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመርቆ ሥራውን ጀምሯል

    ማንኩሳ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፥ ግንባታው ብቻ 43 ሚሊዮን ብር ወጪ ተደርጎበታል፤ የወጪው 75 በመቶ በሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ተሸፍኗል፤ ትምህርት ቤቱን ገንብቶ ለመጨረስ የወሰድው ጊዜ ስምንት ወራትን ብቻ ሲሆን፥ ትምህርት ቤቱ 36 የመማሪያ ክፍሎች፣ ዘመናዊና የተሟሉ የአስተዳደር ህንጻዎች፣ ቤተ-መጽሐፍት፣ የተሟላ ቤተ-ሙከራ፣ የመረጃና ግንኙነት ቴክኖሎጂ (ICT)፣ ንጹህ የሴትና የወንድ መፀዳጃ ቤት ህንጻዎች እና ሌሎችም የትምህርት ግብዓቶች ተሟልተውለታል።

    ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ

    Anonymous
    Inactive

    የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አመራር አባላት ፊቤላ ኢንዱስትሪያል በማስገንባት ላይ የሚገኘውን ግዙፍ የምግብ ዘይት ፋብሪካን ጎበኙ

    የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አመራር አባላት ፊቤላ ኢንዱስትሪያል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር በማስገንባት ላይ የሚገኘውን ግዙፍ የምግብ ዘይት ፋብሪካን ጎበኙ። ፋብሪካው በተያዘው በጀት ዓመት ተመርቆ ምርት እንደሚጀምር በጉብኝቱ ወቅት ተገልጿል።

    የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፋይናንስ በማድረግ እየተሳተፈበት የሚገኘውና በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በቡሬ ከተማ በኢትዮጵያዊው ባለሃብት አቶ በላይነህ ክንዴ የተገነባው የዘይት ፋብሪካ በዓመት 500 ሚሊዮን ሊትር የምግብ ዘይት የሚያመርት ሲሆን፣ የሀገር ውስጥ የምግብ ዘይት ፍጆታን ከ50 እስከ 60 በመቶ መሸፈን የሚያስችልና ለዘይት ግዥ የሚወጣውን የውጭ ምንዛሬ በማዳን የጎላ ፋይዳ እንደሚኖረውም ተገልጿል።

    የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሚሰማሩና ለበርካቶች የሥራ ዕድል ለሚፈጥሩ የኢኮኖሚ ዘርፎች ብድር የሚያቀርብ ሲሆን፥ በቡሬ ከተማ ከፍተኛ መዋለ ንዋይ ወጥቶበት በመገንባት ላይ ለሚገኘው የምግብ ዘይት ፋብሪካም ባንኩ ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ብድር ማቅረቡን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የብድር አስተዳደር ምክትል ፕሬዚዳንትና የጉብኝት ቡድኑ አስተባባሪ አቶ ሙሉነህ አቦዬ ይገልፃሉ።

    በቡሬ ከተማ በ30 ሄክታር መሬት ላይ ግንባታው ተገባዶ የማሽን ተከላ ሥራው እየተጠናቀቀ የሚገኘው ይህ የምግብ ዘይት ፋብሪካ ከአንድ ወር በኋላ ወደ ምርት እንደሚገባ የተገለፀ ሲሆን፥ ከ2500 በላይ ለሚሆኑ ዜጎችም የሥራ ዕድል ይፈጥራል ተብሏል።

    በአቶ በላይነህ ክንዴ በመገንባት ላይ ያለው ፋብሪካው፥ የሀገር ውስጥ የምግብ ዘይት ፍጆታን በከፍተኛ ደረጃ እንደሚሸፍን በጉብኝቱ ወቅት ተገልጿል። በሀገር ውስጥ ያለውን የምግብ ዘይት አቅርቦት ችግርን ለመፍታት ወደ ዘርፉ መግባታቸውን የገለጹት አቶ በላይነህ ክንዴ፥ ፋብሪካው ወደ ምርት ሲገባ የውጭ ምንዛሬ በማዳን በኩል ፋይዳው የጎላ እንደሚሆንም ጠቁመዋል።

    በመገንባት ላይ ያለው ትልቅ የምግብ ዘይት ፋብሪካ አካባቢው ከሱዳን ጠረፍ እስከጃዊ አኩሪ አተር፣ ኑግ፣ ሰሊጥ፣ ሱፍ፣ ስንዴና በቆሎ በከፍተኛ ደረጃ ትርፍ አምራች በመሆኑ ምርቶቹን በግብአትነት በመጠቀም የምግብ ዘይት በከፍተኛ ደረጃ በማምረት የአገሪቱን ከ50 እስከ 60 በመቶ ፍላጎት እንደሚሸፍንም ነው አቶ በላይነህ የጠቆሙት።

    የኢትዮጵያ ንግድ ባንክም በቡሬ ከተማ በመገንባት ላይ ለሚገኙት ሌሎች አምራች ኢንዱስትሪዎች ፋይናንስ በማድረግ ላይ ሲሆን፣ በሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች ለሚገኙና በአምራች ኢንዱስትሪው ለተሰማሩ የግል ኢንቨስተሮች ፋይናንስ በማድረግ ላይ እንደሚገኝና ይህን ጥረቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አቶ ሙሉነህ አቦዬ አስታውቀዋል።

    በቡሬ ከተማ ግንባታው ተጠናቆ ወደ ምርት ለመግባት በዝግጅት ላይ ያለው ፊቤላ ኢንዳስትሪያል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር የዘይት ፋብሪካ በ2006 ዓ.ም የተጀመረ ሲሆን የጀሪካን፣ የማሸጊያ፣ የሳሙና፣ የማርጋሪንና የካርቶንን ጨምሮ ሰባት የተለያዩ ፋብሪካዎችን በውስጡ ይዟል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ፊቤላ ኢንዱስትሪያል

    Semonegna
    Keymaster

    በዓመት 500 ሚሊዮን ሊትር የምግብ ዘይት የሚያመርተው ፋብሪካ ዘንድሮ ሥራ ይጀምራል

    ቡሬ (አዲስ ዘመን) – የአገር ውስጥ የምግብ ዘይት ፍጆታን ከ50 እስከ 60 በመቶ መሸፈን የሚያስችልና በቡሬ ከተማ እየተገነባ የሚገኘው የምግብ ዘይት ፋብሪካ ከሁለት እስከ አራት ወራት ውስጥ ተጠናቆ ወደ ምርት ይገባል ተባለ። የውጭ ምንዛሬ በማዳን የጎላ ፋይዳ እንደሚኖረውም አዲስ ዘመን ጋዜጣ ዘግቧል።

    በፌዴራልና በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ከፍተኛ አመራሮች የካቲት ወር አጋማሽ፣ 2012 ዓ.ም. የተጎበኘው በኢትዮጵያዊ ባለሃብት አቶ በላይነህ ክንዴ በመገንባት ላይ ያለው ፋብሪካው፤ የአገር ውስጥ የምግብ ዘይት ፍጆታን ከ50 እስከ 60 በመቶ ይሸፍናል ተብሏል።

    በአገር ውስጥ ያለውን የምግብ ዘይት አቅርቦት ችግርን ለመፍታት ወደ ዘርፉ መግባታቸውን የገለጹት አቶ በላይነህ ክንዴ፥ ከአንድ ፋብሪካ በስተቀር ቀሪዎቹ እንደተገጣጠሙም ተናግረዋል። በዓመት 500 ሚሊዮን ሊትር ዘይት የማምረት አቅም እንዳለውና አገር ውስጥ ያለውን የምግብ ዘይት አቅርቦት እንደሚፈታም ተናግረዋል።

    ድርጅቱ ላለፉት 13 ዓመታት ሰሊጥ ወደ ውጭ በመላክ ግንባር ቀደም እንደነበር በማስታወስ፥ በተደጋጋሚ በመንግሥትና በሕዝብ ይቀርብ የነበረው ጥያቄ እውን የሚያደርገው አቀነባብሮ የሚያቀርበው ፋብሪካ ዘንድሮ ወደ ምርት እንደሚገባ ነው ባለሀብቱ የተናገሩት። ማንኛውንም አይነት የቅባት እህሎችን እንደሚያጣራና በአሁኑ ወቅት ለአምስት መቶ ሰዎች የሥራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን ወደ ምርት ሲገባ ቁጥሩ እስከ ሦስት ሺህ ከፍ እንደሚልም አብራርተዋል። ፋብሪካው በግብአትነት 20 ሚሊዮን ኩንታል እህል እንደሚያስፈልገው በመጠቆም፥ ከጉትን እስከ ጎንደር ጫፍ ያሉ አርሶ አደሮችም ምርታማነታቸውን እንዲያሳድጉ በጋራ እንሠራለን ብለዋል።

    የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተካ ገብረየሱስ፥ አሁን ባለው ሁኔታ የሕዝቡን ፍላጎት ለማሟላት አቅም ያለው የምግብ ዘይት ፋብሪካ አለ ማለት ይከብዳል፤ አብዛኛው የምግብ ዘይት ፍላጎት ከውጭ በሚገቡ ምርቶች እየተሸፈነ እንደሚገኝም ተናግረዋል። በባለሀብቱ አቶ በላይነህ ክንዴ የሚገነባው 50 በመቶ ፍላጎትን ከሸፈነ ቀሪውንም ሌሎች ወደ ምርት የሚገቡ ፋብሪካዎች ይሸፍኑታል ብለዋል። ፋብሪካዎች ማሽን ስላስገቡ ይጠናቀቃል ማለት አይደለም ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፥ የመብራት ችግር እንዳያስተጓጉል ጎን ለጎን እየተሠራ መሆኑንና ፋብሪካው ወደ ምርት ሲገባ የውጭ ምንዛሬ በማዳን በኩል ፋይዳው የጎላ እንደሚሆንም ጠቁመዋል።

    በአማራ ክልል ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ የፕሮሞሽንና ሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ይሄነው አለም፥ ባህር ዳር ዙሪያና ቡሬ ከተማም እንደቅደም ተከተላቸው ሰፊ የኢንቨስትመንት ማዕከል መሆናቸውን ተናግረዋል። ባለሀብቱ ትልቅ የዘይት ፋብሪካ እንዲተክሉ ያነሳሳቸው አካባቢው ትርፍ አምራች መሆኑ ነውም ብለዋል።

    እንደ እርሳቸው ማብራሪያ፥ ከሱዳን ጠረፍ እስከጃዊ አኩሪ አተር፣ ኑግ፣ ሰሊጥ፣ ሱፍ፣ ስንዴና በቆሎ በከፍተኛ ደረጃ ይመረታል፤ ፋብሪካው ምርቶቹን በግብአትነት በመጠቀም ዘይት በከፍተኛ ደረጃ በማምረት በዕቅዱ መሠረት የአገሪቱን ከ50 እስከ 60 በመቶ ፍላጎት እንደሚሸፍንም ተናግረዋል። ምሥራቅ ጎጃም፣ ምዕራብ ጎጃምና አዊ ደቡባዊ ጎንደር እስከ ሱዳን ጠረፍ ከፍተኛ ምርት በመኖሩ የፌዴራልና የክልሉ መንግሥት የግብርና ምርት አቀነባባሪዎች ትኩረታቸውን ወደ አካባቢዎቹ እንዲያርጉም ፍላጎት እንዳላቸው ተናግረዋል።

    በላይነህ ክንዴ ግሩፕ በተለያዩ ዘርፎች የተሰማራ ድርጅት ሲሆን፤ በገላን ከተማ የጀመረው የመኪና መገጣጠሚያ፣ ሆቴልና እርሻ ሥራ ተጠቃሽ ናቸው። በቡሬ ከተማ በግንባታ ላይ ያለው የዘይት ፋብሪካ በ2006 ዓ.ም የተጀመረና በ30 ሄክታር ላይ ያረፈ ነው። የጀሪካን፣ የማሸጊያ፣ የሳሙና፣ የማርጋሪንና የካርቶንን ጨምሮ ሰባት የተለያዩ ፋብሪካዎችን ይዟል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    በላይነህ ክንዴ የምግብ ዘይት ፋብሪካ

    Semonegna
    Keymaster

    የከተማዋን የቱሪዝም ዕድገት ከፍ ለማድረግ የዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ እና ዳግማዊ ምኒልክ ሃውልቶችን የከተማ አስተዳደሩ ኅብረተሰቡን በማሳተፍ ያስገነባል። ስለሆነም የሁለቱ ታላላቅ መሪዎች ሃውልት በከተማዋ እንዲቆም እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ከ6 መቶ ዓመታት በላይ ባስቆጠረችው የድሮዋ ደብረ ኤባ የዛሬዋ ደብረ ብርሃን ከተማ ለዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ እና ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሃውልት ሊቆምላቸው እንቅስቃሴ መጀመሩን ከተማ አስተዳደሩ አስታውቋል።

    የከተማዋ ምክትል ከንቲባ እና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ብርሃን ገብረሕይወት ጥር 9 ቀን 2011 ዓ.ም. አዲስ አበባ ላይ በሰጡት መግለጫ ደብረ ብርሃን ከተማን የቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ የከተማ አስተዳደሩ እየሠራ ነው፤ ከተማዋን የኮንፈረንስ ቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግም ከተማ አስተዳደሩ ባዛሮችን በተለያዩ ጊዚያት እንደሚያካሂድ ተገልጿል።

    የከተማዋን የቱሪዝም ዕድገት ከፍ ለማድረግ የዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ እና ዳግማዊ ምኒልክ ሃውልቶችን የከተማ አስተዳደሩ ኅብረተሰቡን በማሳተፍ ያስገነባል። ስለሆነም የሁለቱ ታላላቅ መሪዎች ሃውልት በከተማዋ እንዲቆም እንቅስቃሴ እየተደረገ ነውም ተብሏል።

    ደብረ ብርሃን ኢንዱስትሪ ፓርክ በከተማዋ ለሚኖሩ ዜጎች የተለያዩ የሥራ ዕድሎችን ፈጥሯል

    ከተማ አስተዳደሩ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ እየሠራ እንደሆነም አስታውቋል። ደብረ ብርሃን ከተማ በዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ መመሥረቷ ይታወቃል።

    አጼ ዘርአ ያዕቆብ

    አጼ ዘርአ ያዕቆብ በዘውድ ስማቸው ቆስጠንጥንዮስ ከአባታቸው ቀዳማዊ ዳዊት እና ከእናታቸው ንግስትክብረ እግዚ እ.ኤ.አ. በ1399 ከአዋሽ ወንዝ አጠቀብ ትገኝ በነበረው ትልቅ ተብላ በምትጠራው መንደር የድሮው ፈታጃር ክፍለ ሀገር ተወለዱ። የነገሡበትም ዘመን እ.ኤ.አ. ከ 1434 እስከ 1468 (እስከሞቱበት ጊዜ) ነበር። ያረፉትም በደጋ ደሴት፣ ጣና ሃይቅ ነው።

    ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ

    ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ከአባታችው ከሸዋው ንጉሥ ኃይለ መለኮት ሣህለ ሥላሴና ከእናታቸው ወይዘሮ እጅጋየሁ ለማ አድያም እ.ኤ.አ. ነሐሴ 17 ቀን 1844 ደብረ ብርሃን አካባቢ አንጎለላ ከሚባል ሥፍራ ተወልደው፤ በአንጎለላ መቅደላ ኪዳነ ምኅረት ቤተ ክርስቲያን ክርስትና ተነሱ። የነገሡበትም ዘመን እ.ኤ.አ. ከ 1889 እስከ 1913 (እስከሞቱበት ጊዜ) ነበር። ያረፉትም ተዓካ ነገሥት ለማርያም ወደብረ መንክራት ስዕል ቤት ኪዳነ ምኅረት ገዳም (አዲስ አበባ) ነው።

    ምንጭ፦ የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    ዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ እና ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሃውልት


    Semonegna
    Keymaster

    “ለኢንቨስትመንት በሚል ሰበብ አርሶ አደሩን በማደህየት ኢንቨስትመንቱን ማሳደግ አይቻልም፤ መሬታቸው የሚወሰድባቸው አርሶ አደሮች ተመጣጣኝ ካሳ ማግኘት አለባቸው።” ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው

    ዘጋቢ፡-ደጀኔ በቀለ (አብመድ)

    ባሕር ዳር – የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ቢሮ በ2011 ዓ.ም በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ፣ በሕግ ማዕቀፎች እና አሠራሮች ላይ ሲሰጥ የነበረውን ክልላዊ የምክክር መድረክ ዛሬ አጠናቅቋል።

    የአማራ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ለኢንቨስትመንት በሚል ሰበብ ብዙ አርሶ አደሮች መብታቸው ተጥሶ እንደነበር በመጥቀስ አርሶ አደሩን በማደህየት ኢንቨስትመንቱን ማሳደግ አይቻልም፤ መሬት የሚወሰድባቸው አርሶ አደሮች ተመጣጣኝ ካሳ ማግኘት አለባቸው ሲሉ አስገንዝበዋል። ቀደም ሲል ካሳ የማያገኙበት ሕግ የነበረ ቢሆንም ሕጉን የማስተካከል እርምጃ መወሰዱንም አስታውቀዋል።

    አርሶ አደሮች እና የነባር ይዞታ ባለቤቶች መሬታቸውን ሕጋዊ በሆነ መንገድ እንዲጠቀሙ መደረጉ ጥያቄ በሚያነሱበት ጊዜ በመረጃ ላይ የተመሠረተ ምላሽ ለመስጠት ከማገዙም በላይ ህብረተሰቡ ተረጋግቶ እንዲሠራ ያደርገዋል። በመሆኑም አርሶ አደሩን ከአላስፈላጊ እንግልት የምናድንበት በመሆኑ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ርዕሰ መስተዳድሩ አሳስበዋል።

    አርሶ አደሮች በጉልበተኛ ጥቅማቸውን የሚያጡበት ፍትሃዊ ያልሆነ አሠራር ካለ የገጠር መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም ቢሮ ህዝባዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ጠንክሮ መሥራት እና የፍትህ ስርዓቱን ማስከበር ይጠበቅበታልም ነው ያሉት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው።

    ሕገ-ወጥ የመሬት ወረራን በተመለከተ ትኩረት ተሰጥቶት እንዲሠራ ርዕሰ መስተዳድሩ በጥብቅ አሳስበዋል። በተለይ የወል መሬቶች በሕገ-ወጥ መንገድ ወደ ግለሰቦች ይዞታ ስር እየገቡ በመሆኑ በፍጥነት መግታት ካልተቻለ ስር እየሰደደ ሄዶ ግለሰቦች ላይ ጫና ማሳደሩ እንደማይቀር አስገንዝበዋል።

    በመድረኩ የተሳተፉ አካላት በባለቤትነት ይዞ በመንቀሳቀስ ከሚመለከተው ባለድርሻ አካላት ጋር ትኩረት ሰጥተው ሊሠሩ እንደሚገባም አፅንዖት ሰጥተው ተናግረዋል።

    ለተከታታይ አምስት ቀናት የቆየውን የምክክር መድረክ የተካፈሉ አስተያየት ሰጪዎች በበኩላቸው በሚችሉት አቅም ሁሉ ህብረተሰቡን ለማገልገል ፍቃደኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።

    ተጨማሪ ዜና፦ ኢትዮጵያዊው ባለሃብት አቶ በላይነህ ክንዴ እያስገነቡ ያሉት የምግብ ዘይት ፋብሪካ በቅርቡ ሥራ ይጀምራል

    አቶ ወዳጅ ምስክር ከሰሜን ወሎ ዞን፣ ወይዘሮ በላይነሽ አሻግሬ ደግሞ ከደቡብ ጎንደር ፋርጣ ወረዳ በምክክር መድረኩ የተገኙ ተሳታፊዎች ናቸው። ከውይይቱ በቂ ግብዓት እንዳገኙ ነግረውናል። ተሳታፊዎቹ እንደተናገሩት ወቅቱን መሰረት ያደረገ የገጠር መሬት አጠቃቀም ስልጠና መውሰዳቸው ለቀጣይ የተጣለባቸውን የሕዝብ ኃላፊነት በብቃት ለመወጣት ዝግጁ እንደሚያደርጋቸው ለአብመድ ጋዜጠኞች አረጋግጠዋል።

    በመዝጊያ ሥነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት ርዕሰ መስተዳድር ገዱ አንዳርጋቸው የገጠር መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም ቢሮ ከወረዳ እስከ ክልል ድረስ ተቋማዊ በሆነ መንገድ ሥራውን በአግባቡ ለመወጣት ጥረት እያደረገ ያለ ተቋም መሆኑን አውስተው፥ መሬት ሀብት እና የማንነት መገለጫ መሆኑን በመረዳት የኃላፊነት ስሜት በተሞላበት መንገድ ሲንቀሳቀስ ለቆየው ለተቋሙ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ ሥራው አድካሚ መሆኑን በመጥቀስ ወደ ዘመናዊ የመረጃ ቋት ለማስገባት ተቋሙ እያደረገ ያለው ጥረት የሚበረታታ ነው ብለዋል።

    ከገጠር መሬት ጋር በተያያዘ ለሚከሰቱ ማንኛውም ጥያቄዎች ምላሽ መስጠት የሚችለው በመድረኩ ላይ የተሳተፈው ባለሙያ ነው፤ በተለይ በምዕራብ ቆላማው የክልሉ አካባቢዎች ለበርካታ ዘመናት ጥሩ አሠራር ያልነበረባቸውን ቦታዎች በዚሁ ተቋም ውስጥ በተሰማሩ ሙያተኞች እና አመራሮች አማካኝነት ውጤታማ በሆነ መንገድ ማስተካከል ተችሏል ብለዋል።

    በከተሞች ዙሪያ የሚኖሩና ትኩረት የማያገኙ አርሶ አደሮች ጥቅማቸው እና መብታቸው እንዲከበር በማድረግ በኩል ትልቅ ሥራ ተሰርቷል፤ ተገፍተው ለነበሩ አርሶ አደሮች በተገቢው መንገድ ካሳ እንዲያገኙ ተደርጓል ብለዋል።

    ምንጭ፦ የአማራ መገናኛ ብዙሀን ድርጅት (አብመድ)

    ገዱ አንዳርጋቸው

    Semonegna
    Keymaster

    ቡሬ ከተማ ውስጥ በአቶ በላይነህ ክንዴ የተቋቋመው የፊቤላ ኢንዳስትሪያል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ስር እየተገነባው ያለው የምግብ ዘይት ፋብሪካ ሥራ ሲጀምር በሀገራችን የሚስተዋለዉን የምግብ ዘይት እጥረት በ60 በመቶ ይቀንሳል።

    አዲስ አበባ – በሀገራችን በህብረተሰቡ የመሰረታዊ እቃዎች የዕለት ፍጆታ ላይ የአቅርቦት እጥረት ይስተዋላል። የምግብ ዘይት አቅርቦት እጥረት በመኖሩ መንግስት ለህብረተሰቡ በየወሩ በኮታ ልክ ያከፋፍላል። ይሁንና ችግሩ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ ይገኛል ሲሉ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ቅሬታ ያነሳሉ። በአማራ ክልል በወር ከ23 ሚሊየን ሊትር በላይ የምግብ ዘይት አቅርቦት ያስፈልገዋል። ክልሉ እያሰራጨ ያለው ግን 7 ነጥብ 7 ሚሊየን ሊትር የምግብ ዘይት እንደሆነ ከአማራ ክልል ንግድ ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

    በቡሬ ከተማ በላይነህ ክንዴ በተሰኙ ባለሀብት ፊቤላ ኢንዱስትሪያል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር በሚል ስያሜ የምግብ ዘይትና ሌሎች ምርቶች ማምረቻ ፋብሪካ እየተገነባ ይገኛል። ከ500 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦለት ግንባታው የተጀመረው ፋብሪካ የምግብ ዘይት፣ ፕላስቲክ፣ ሳሙና እና የተቀነባበረ ሰሊጥ ያመርታል።

    የፊቤላ ኢንደስትሪያል ኃ/የተ/የግል ማህበር አስተዳደር እና ፋይናንስ ኃላፊ አቶ ጎጃም ዓለሙ እንደተናገሩት በ2006 ዓ.ም የመሠረት ድንጋይ ተጥሎ ወደ ግንባታ ገብቷል። የህንጻ እና መሠረተ ልማት አውታሮች ግንባታ ተጠናቋል። ነገር ግን የዘይት ፋብሪካው የማሽን ተከላ ዘግይቷል። ለዚህም በዋነኝነት እንደምክንያት የሚጠቀሰው ሀገሪቱ ያጋጠማት የውጭ ምንዛሪ እንደሆነ ከዚህ በፊት Mutesi የተሰኘ በአፍሪካ የንግድና ቢዝነስ እንቅስቃሴ ላይ ያተኮረ ሚዲያ ዘግቦ ነብር። አሁን ላይ ግን ማሽኑን ለመትከል ዝግጅቱ ተጠናቋል አቶ ጎጃም እንደገለጹት። በአጭር ጊዜ ውስጥም ወደ ምርት ይገባል ነዉ ያሉት። የፊቤላ ኢንደስትሪ የምግብ ዘይት ማምረት ሥራ ሲጀምር ከ1 ሚሊዮን ሊትር በላይ በቀን የማምረት አቅም ይኖረዋል። በዚህም የአማራ ክልል የዘይት አቅርቦት እጥረትን ከመፍታት አልፎ ከክልሉ ውጭ ላሉ አካባቢዎች ማድረስ ይችላል።

    “የዘይት ፋብሪካው ሥራ ሲጀምር በሀገራችን ያለውን የፋብሪካ ቁጥር ያሳድጋል። በሀገር ደረጃ የሚስተዋለዉን የምግብ ዘይት እጥረት ችግር እስከ 60 በመቶ ይቀንሳል። በየዓመቱ ከ12 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የቅባት እህሎችን በግብዓትነት ስለሚጠቀም ለአርሶ አደሩ የገበያ ዕድል በመፍጠር ተጠቃሚ ያደርጋል” በማለት አቶ ጎጃም ተናግረዋል። ወደ ውጭ ምርቶችን በመላክ የውጭ ምንዛሪ ያስገኛልም ብለዋል።

    የመብራት እና የውሀ አቅርቦት ችግር የምርት ሂደቱ ላይ ከፍተኛ ጫና የሚያሳድር እና ጊዜ የማይሰጥ እንቅፋት፥ ምናልባትም ፋብሪካው ሊያጋጥሙት ከሚችሉት ተግዳሮቶች ዋነኛው መሆኑን ጠቁመዉ የሚመለከታቸው አካላት አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጡ መልዕክት አስተላልፈዋል።

    Ethiopian millionaire Belayneh Kinde and others awarded for investing in pulses, oilseeds & spices

    የቡሬ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ እና የንግድ፣ ኢንደስትሪ እና ገበያ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ይገርማል ሙሉሰዉ በበኩላቸዉ ፊቤላ ኢንደስትሪያል ኃ/የተ/የግል ማኅበር በሀገር ደረጃ የሚስተዋለዉን የምግብ ዘይት አቅርቦት ችግር ይቀንሳል ብለዋል። ለወጣቶች የሥራ ዕድል ከማስገኘቱ በላይ ለአርሶ አደሩ የገበያ ትስስር በስፋት እንደሚፈጥርም ተናግረዋል።

    የህንጻ እና የመሠረተ ልማት ግንባታዉ ከ95 በመቶ በላይ መጠናቀቁን ጠቅሰዉ የመብራት እና ውሀ አቅርቦት ችግር ካልገጠመው በተያዘው በጀት ዓመት ፋብሪካው ሥራ ይጀምራል። ይሁን እንጂ የመብራት እና የውሀ ችግሩ ስር የሰደደ እና ከከተማ አስተዳደሩ አቅም በላይ በመሆኑ የፌዴራል መንግስት ትኩረት እንደሚያሻዉ አቶ ይገርማል ነግረውናል።

    ፋብሪካው እስከ 1500 ለሚሆኑ ሰዎች በቋሚነት እና በጊዚያዊነት የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር የአማራ ብዙኃን መገናኛ ድርጅትን ዋቢ በማድረግ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ዘግቧል።

    አቶ በላይነህ ክንዴ ማን ናቸው?

    • የተወለዱት በአማራ ክልል፣ ምዕራብ ጎጃም ዞን፣ ሰቀላ ወረዳ (ቡሬ አጠገብ) ነው፤
    • የአስራ ሁለተኛ ክፍል ትምህርታቸውን እንዳጠናቀቁ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ውጤት ስላልመጣላቸው ሁርሳ ወታደራዊ ማሠልጠኛ ገብተው ወታደራዊ ስልጠና ተከታትለዋል፤
    • ነገር ግን በውትድርና ሕይወት ብዙም አልገፉም፤ የደርግ መንግስት ወድቆ የኢህአዴግ መንግስት ስልጣን ሲይዝ የውትድርና ሥራን ትተው እጅግ አናሳ በሆነ ገቢ የቀን ሥራ ላይ ተሰማሩ፤
    • በቀን ሥራ ገፍትው ጥቂት ገንዘብ እንዳጠራቀሙ የማር እና የቅቤ ንግድ ጀመሩ፤
    • በማር እና ቅቤ ንግድ ለአስር ዓመታት ሠርተው ንግዳቸውን በማሳደግ “በላይነህ ክንዴ አስመጪና ላኪ” የሚል ድርጅት መሠረቱ፤
    • ይህንን የአስመጪና ላኪነት ሥራ ከጊዜ ወደጊዜ በካፒታል፣ በሥራ ዘርፍ እና ሠራተኞችን በመቅጠር፣… በአጠቃላይ በሁሉም አቅጣጫዎች በማሳደግ በአሁኑ ጊዜ ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ጥቂት ሚሊየነሮች ተርታ ሊሰለፉ ችለዋል (ይህንንም በዓለም ታዋቂው የቢዝነስ መጽሔት ፎርቤስ/Forbes በ2009 ዓ.ም ዘገባው አንስቷቸው ነበር)፤
    • በአሁኑ ወቅት የአቶ በላይነህ ክንዴ አጠቃላይ ሀብት ከሶስት ቢሊየን ብር (ከ111 ሚሊየን ዶላር) በላይ ሲሆን የተሰማሩበት የንግድና ምርት ዘርፍም አስመጪና ላኪነት፣ ትራንስፖት፣ የግንባታ ምርቶች፣ እርሻ እና ፋይናንስ ሲሆኑ ሀገሪቱ ውስጥ ባሉ ግዙፍ አክሲዮን ማኅበራት፥ ለምሳሌ ያህል ጎልደን ባስ ኢትዮጵያ፣ ኢትዮጵያ ሆቴል፣ አዳማ ራስ ሆቴል፣ ፀሐይ ኢንዱስትሪያል ፣ ኳሊቲ ብረታ ብረት ማምረቻ አክሲዮን ማኅበራት ውስጥ ሁነኛ ድርሻ አላቸው።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እና Mutesi

    በላይነህ ክንዴ

Viewing 6 results - 1 through 6 (of 6 total)