Search Results for 'ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር'

Home Forums Search Search Results for 'ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር'

Viewing 15 results - 1 through 15 (of 22 total)
  • Author
    Search Results
  • Anonymous
    Inactive

     ጤናችን በእጃችን! ― 1.2 ሚሊዮን ሰዎችን ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ የሚከላከል ፕሮጀክት ይፋ ሆነ

    አዲስ አበባ – በግል የንግድ ዘርፍ፣ በመንግሥት እና በመንግሥታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች መካከል የተመሠረተው ጥምረት ሐምሌ 16 ቀን 2012 ዓ.ም. የኮቪድ-19 ወረርሽኝ የሚያስከትለውን ከፍተኛ አደጋ ለመከላከል የሚያስችል ለሚቀጥሉት ቀጣይ ወራት የሚሠራ እና እስከ 6 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ወጪ ሊኖረው የሚችል <ጤናችን በእጃችን!> የተሰኘው ፕሮጀክት ይፋ ተደረገ። ፕሮጀክቱ የውሃ፣ የሳሙና እና ሌሎች ተመሳሳይ ተግዳሮቶች እጥረት የሚያጋጥማችውን እና በጣም ጥቅጥቅ ያሉ የመኖሪያ አካባቢዎች ውስጥ የሚገኙ የከተማዋ ነዋሪዎችን ለማገዝ ብሎም ራሳቸውን ከወረርሽኙ እንዲጠብቁ የሚያስችል ይሆናል።

    የፕሮጀክቱ አባል የሆኑት አምራች ኩባንያዎች በፕሮጀክቱ የመጀመሪያዎቹ 6 ወራት ውስጥ ትርፍን መሰርት ያላደረገ ሥራ ለመሥራት እና ሠራተኞቻቸውን በሥራ መደብ ላይ ለማቆየት ተስማምተዋል። ይህንን ለማካካስ ጥምረቱ ለተሳታፊ ኩባንያዎች ወሳኝ ከሆኑ ጥሬ ዕቃዎች እና ከማምረት ጋር ለተያያዙ የክንዋኔ ወጪዎችን የሚሸፍን ይሆናል።

    ጤናችን በእጃችን! ፕሮጀክት በይፋ መጀመርን ተከትሎ ይህ አዲስ ጥምረት የፊት ጭምብሎችን እና ሳሙናዎችን የማምረት እና ማሠራጨት፣ የውሃ ገንዳዎችን መትከል፣ ብሎም የባህሪ ለውጥ ለማምጣት የሚያስችሉ የግንዛቤ ለውጥ ፈጣሪ ትምህርቶችን ለ1.2 ሚሊዮን ለሚሆኑ ከፍተኛ ተጋላጭ ተበለው ለተለዩ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች የኮቪድ-19 ወረርሽኝን የመከላከል ሥራን በሚያጠናክር መልኩ የሚያደርስ ይሆናል።

    ዳልበርግ ግሩፕ (Dalberg Group) እና ሮሃ ግሩፕ (Roha Group) የተባሉ የግል ድርጅቶች ተነሳሽነት በመውሰድ በሀገሪቱ በአሁኑ ጊዜ ያለውን የወረርሽኝ የመከላከል ብሔራዊ ምላሽ ላይ ዘላቂ ተፅዕኖ ለመፍጠር በሚያስችል መልኩ በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነውን የግል እና የመንግሥት ተቋማት በጋራ በማደራጀት ወደ ሥራ ገብተዋል። የፕሮጀክቱ የሙከራ ጊዜ የሚያስፈልገውን 1 ሚሊዮን ዶላር በሮሃ ግሩፕ በኩል የተገኘ ሲሆን፥ ቀሪው 5 ሚሊዮን ዶላር ከለጋሽ ድርጅቶች፣ የግሉ ዘርፍ እና መንግሥታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች የሚሰበሰብ ይሆናል። ጥምረቱ የንፅህና መጠበቂያ የሆኑ ልዩ ልዩ ቁሳቁሶችን ማምረትና በጣም ተጋላጭ ለሆኑ የማኅበረሰብ ክፍሎች በማከፋፈል በዓይነቱ ለየት ያለ የንግድ ሥራ ሞዴሎችንም ማስተዋወቅ ችሏል።

    መንግሥት በበኩሉ በገንዘብ ሚኒስቴር በኩል ለፕሮጀክቱ የሚመረቱ ዕቃዎች ላይ የተጨማሪ እሴት ታክስን ያነሳ ሲሆን፥ ዓላማውም የግል ተቋማት በኮቪድ-19 ወረርሽኝላይ ለሚደረገው የመከላከል ሥራ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበርክቱ ለማስቻል ነው።

    ፕሮጀክቱ እስካሁን ድረስ 15 የሚሆኑ ሀገር በቀል በማምረቻ ዘርፍ የተሰማሩ ኩባንያዎችን በአንድ ላይ በማሰባሰብ አነጋግሯል። ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና ሴቭ ዘ ችልድረን (Save the Children) በጎ አድራጊ ድርጅት ጋር በጋራ ለመሥራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል።

    የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር የከንቲባ ጽ/ቤት ውስጥ ብሎክን መሠረት ያደረገ የማኅበረሰብ አደረጃጀት ኤጀንሲ በከተማው ውስጥ የሚገኙ 24,934 አካባቢዎችን በመለየት የሚገኙበትን ጊዜያዊ ሁኔታ መረጃ ሰብስቦ አዘጋጅቷል። በተጨማሪም በ10 ክፍለ ከተማዎች የሚገኙ 121 ወረዳዎች ውስጥ 1,357 የተደራጁ ማዕከላትን በመጠቀም የፊት ጭንብሎችን እና ሳሙናዎችን ለከፍተኛ ተጋላጭ ተበለው ለተለዩ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች የሚያከፋፍል ይሆናል።

    በተጨማሪም ሴቭ ዘ ችልድረን (Save the Children) ለጥምረቱ የቴክኒክ ድጋፍ፣ መመሪያ እና የሕብረተሰቡ ተሳትፎን በተመለከተ ድጋፍ ይሰጣል። የሚሠራጨው በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የፀደቁ የእጅ መታጠብ፣ የፊት ጭንብል መልበስ እና አካላዊ ርቀት መጠበቅን የሚመለከቱ መልዕክቶችን ያካትታል። የሠራተኞቹን እና የሕብረተሰብ አካላትን ጤና እና ደህንነት ለመጠበቅ ከ260 በላይ የክፍለ ከተማና የወረዳ ቡድን አመራሮችም ስልጠና ተሰጥቷቸዋል።

    በተያያዘም ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ ፕሮጀክቱ የሙከራ ጊዜውን ጨርሶ ሙሉ በሙሉ ከመጀመሩ በፊት የፈንድ አስተዳደርና የሥራ ሂደት ለመቆጣጠር የፕሮጀክቱን ውጤታማነት ለመገምገም ከጥምረቱ ጋር አብሮ የሚሠራ ይሆናል።

    የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ማኅበረሰባችን ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ጉዳት ለመከላከል የበኩላችንን ማድረግ በመቻላችን ከፍተኛ ደስታ ይሰማናል። ጥምረቱን የተቀላቀሉና ኃላፊነታቸውን በመወጣት አዳዲስ መፍትሄዎችን በማምጣት ይህን አስቸጋሪ ጊዜ ለማለፍ አብረውን እየሠሩ ያሉትን አጋሮቻችንን እናመሰግናለን” ብለው የጥምረቱ መሥራቾች ተናግረዋል።

    አክለውም ይህ ጥምረት ወረርሽኙን ለመዋጋት የሚያስፈልገውን ቁሳቁሶች ብሎም የባህሪ ለውጥ ትምህርት ድጋፍ የሚሰጥ ሲሆን፥ ሌሎችም በንግዱ ዘርፍ የተሰማሩ ድርጅቶች እና ተቋማት ይህን ጥምረት በመቀላቀል የበኩላቸውን እንዲያደርጉ ጥሪ እናቀርባለን።

    ፍሰሃ አለማየሁ የፍሪ ዞን ኢንተርናሽናል (Free Zone International) ዋና ሥራ አስኪያጅ በበኩላቸው “የጥምረቱ አባል በመሆናችን የማምረት ሥራችን ሳይስተጓጎል በ ሀ ገራችን ውስጥ ኮቪድ-19 ወረርሽኝ የመከላከል እንቅስቃሴ እንድንደግፍ አስችሎናል” ብለው ተናግረዋል።

    ጤናችን በእጃችን!

    ጤናችን በእጃችን! በዳልበርግ ግሩፕ እና በሮሃ ግሩፕ የተመሰረት የግል እና የመንግሥት ተቋማትን አንድ ላይ የያዘ ጥምረት ነው። በሀገራችን የኮሮና ወረርሽኝ መከላከል ሥራ ላይ ለውጥ ለማምጣት ሁለቱ ኩባንያዎች የግሉ ሴክተር አቅምን እና ብቃቶችን ለማደራጀት ተነሳሽነት ወስደው ወደ ሥራ ገብተዋል።፡

    ጥምረቱ ተጋላጭ የሆኑትን የሕብረተሰብ ክፍሎችን በመለየት ባሉበት ቦታ መፍትሄ ለማቅረብ የሚቻልበትን መንገድ ሲሠራ ቆይቷል፡፡ በከፍተኛ አደጋ ላይ ከሚገኙ ንዑስ ምድቦች በተጨማሪ የህብረተሰባችንን ኢኮኖሚያዊ ጤና ለማረጋገጥ አካል የሆኑት የንግድ ድርጅቶችም የዚህ ጥምረት ትኩረት ናቸው። ስለሆነም ጤናችን በእጃችን! የተሰኘው ፕሮጀክት ከፍተኛ አደጋ ተጋላጭ ማኅበረሰቦችን የሚረዱ አስፈላጊ የንፅህና እና የመከላከያ ምርቶችን በማምረት እና በማሠራጨት ረገድ ልዩ የንግድ ሥራ ሞዴል በማስተዋወቅ የንግድ ተቋማት ይህ አስጨናቂ ጊዜ የፈጠረውን የገበያ እጦት ለመቋቋም የሚያስችላቸው መንገዶችን በማዘጋጀት የንግድ ድርጅቶች ወጪያቸውን ለመሸፈን እና ሠራተኞቻቸውን ለማቆየት የሚያስችል ይሆናል። https://www.tenachinbejachin.org

    [caption id="attachment_15265" align="aligncenter" width="600"]ጤናችን በእጃችን! (Tenachin Bejachin!) Initiative ጤናችን በእጃችን! (Tenachin Bejachin!) Initiative[/caption]

    Semonegna
    Keymaster

    የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የውሃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአሜሪካ የግምጃ ቤት ዲፓርትመንት ሴክሬታሪ በየካቲት 21 ቀን 2012 ዓ.ም. (እ.ኤ.አ. በ28 February 2020) የታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በተመለከተ ኢትዮጵያ ያልተሳተፈችበትን ስብሰባ ተከትሎ የወጣውን ጋዜጣዊ መግለጫ በከፍተኛ ቅሬታ ተመልክተውታል።

    ስብሰባው የተካሄደው ኢትዮጵያ አስቀድማ ለግብጽ፣ ለሱዳን እና ለአሜሪካ ስብሰባው ለሌላ ጊዜ እንዲተላለፍ አሳውቃ እያለ ነው።

    የግድቡ ባለቤት የሆነችው ኢትዮጵያ በመርሆዎች መግለጫ ስምምነቱ መሰረት የግድቡን ሙሌት ከግንባታው ትይዩ በፍትሐዊ እና ምክንያታዊ አጠቃቀም እና ጉልህ ጉዳት ያለማድረስ መርሆዎች መሠረት የምታከናውን ይሆናል።

    ኢትዮጵያ የግድቡን የመጀመሪያ ሙሌት እና የውሃ አለቃቅ መመሪያ እና ደንብ ለማዘጋጀት የሚደረገው ድርድር ተጠናቋል በሚል የተሰጠውን መግለጫ አትቀበልም።

    በዋሽንግተን ዲሲ የግብጽ ዐረባዊት ሪፐብሊክ ፈርሞበታል የተባለው “ረቂቅ” የሦስቱ ሀገራት የድርድርም ሆነ የሕግ እና ቴክኒክ ቡድኖች ውይይት ውጤት አይደለም። የቴክኒክ ጉዳዮች ድርድሩም ሆነ የሕግ ማዕቀፍ ዝግጅቱ ላይ የሚደረገው ድርድር አልተጠናቀቀም።

    ኢትዮጵያ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ሙሌት እና የውሃ አለቃቅ መመሪያ እና ደንብ የሚዘጋጀው በሶስቱ ሀገራት ብቻ እንደሆነ አቋሟን ቀድማ አሳውቃለች።

    ኢትዮጵያ ግብጽ እና ሱዳን በሚያውቁት እና በተስማሙበት እንዲሁም በመርሆዎች መግለጫ ስምምነት መርህ አንቀጽ ስምንት አድናቆታቸውን በሰጡት ሂደት መሠረት ሁሉንም የግድብ ደህንነት የሚመለከቱ ጉዳዮች በዓለምአቀፍ የባለሙያዎች ቡድን ምክረ ሃሳብ መሰረት የተሰጡትን ምክረ-ሃሳቦች መፈጸሟን ትቀጥላለች።

    የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ሙሌት እና የውሃ አለቃቅ መመሪያ እና ደንብን ለማዘጋጀት ቀሪ መሰረታዊ ልዩነቶችን ለመፍታት ኢትዮጵያ ከግብጽ ዐረባዊት ሪፐብሊክ እና ከሱዳን ሪፐብሊክ ጋር የጀመረችውን ሂደት ለመቀጠል ቁርጠኛ ናት።

    ከዚሁ ጉዳይ ጋር በተያያዘ፥ የኢትዮጵያ መንግስት ሕዳሴ ግድብን በተመለከተ ብሔራዊ ጥቅምን የሚነካ ድርድር እንደማያደርግ የሚስትሮች ም/ቤት አስታወቀ።

    ታላቁ የሕዳሴ ግድብን የሚመለከት ማንኛውም ነገር የኢትዮጵያን ፍላጎትና ጥቅም በሚጠብቅ መልኩ ብቻ እንደሚከናወን የሚስትሮች ምክር ቤት ገልጿል።

    ምክር ቤቱ በዛሬው ዕለት ባካሄደው ስብሰባ ሕዳሴ ግድብን በተመለከተ ብሔራዊ ጥቅምን የሚነካ ድርድር የኢትዮጵያ መንግስት እንደማያደርግ አስታውቋል።

    በዛሬው ዕለት ባካሄደው 80ኛ መደበኛ ስብሰባው ምክር ቤቱ የኮሮና ቫይረስ መከላከል ስራዎችን የሚከታተል ስድስት አባላት ያሉት ብሔራዊ የሚኒስትሮች ኮሚቴ ማቋቋምን ጨምሮ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል።

    የብሔራዊ የሚኒስትሮች ኮሚቴው ስድስቱ አባላትም የሰላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል፣ የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ፣ የገቢዎች ሚኒስትር ወይዘሮ አዳነች አቤቤ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገዱ አንዳርጋቸው፣ የትራንስፖርት ሚኒስትር ወይዘሮ ዳግማዊ ሞገስ እና የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሊያ ታደሰ ናቸው።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    Ethiopian government's statement regarding the negotiations on GERD የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ

    Anonymous
    Inactive

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ከብሔራዊ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መፃሕፍት ኤጀንሲ፣ ከትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ባህልና ቱሪዝም ቢሮ እና ከመቐለ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመቀናጀት “ግዕዝ እና ሥነ-ፈውስ” በሚል ቃል የተዘጋጀው 5ኛው ሀገር አቀፍ የግዕዝ ጉባዔ ለሁለት ተከታታይ ቀናት በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ አዲሐቂ ካምፓስ ሲካሄድ ቆይቶ ቀጣይ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ሰኔ 2 ቀን 2011ዓ.ም. ተጠናቋል።

    በጉባዔው መክፈቻው ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት ክብርት ወ/ሮ ብዙነሽ መሠረት የባህል ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ያስተላለፉት መልዕክት “አገራችን ከ80 በላይ ቋንቋዎች የሚነገሩባት ብዝሃ-ባህል ያለን ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ሀገር መሆናችን እንደአፍሪካ አህጉር መልካም አጋጣሚዎች ቢኖረንም ያሉንን ባህላዊ እሴቶችና ሀገር በቀል ዕውቀቶችን አስተዋውቀን በሚገባ አልተጠቀምንባቸውም። የራሳችን የሆነ ፊደልና የግዕዝ ቋንቋ ያለን ሲሆን፣ እነዚህ ልዩ ጥበቃና እንክብካቤ የሚያስፈልጋቸው በጥናትና ምርምር እየተደገፈ በመሰነድ ለትውልድ ማስተላለፍ የሁላችን ኃላፊነት ሆኖ ይገኛል ካሉ በኋላ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ላለፉት አራት ዓመታት ተመሳሳይ የጥናትና ምርምር መድረኮች የተካሄዱበት አግባብና ውጤታማነት ሲገመግም ጉባዔዎች በተባባሪ የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ በጋራ የሚካሄዱ መሆናቸው እንደ ጥሩ ጅምር የሚወሰድ ነው ብለዋል።

    አክለው ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ከዚህ ቀደም በተካሄዱ ጉባዔያቱ በቋንቋው ጥናት ዙሪያ ያሉ ጠቃሚ ልምዶች፣ በቋንቋው ጥናት አስፈላጊነት በቂ ግንዛቤ ያገኘንባቸው ነው ብሎ መውሰድ ይቻላል። የዘንድሮው የመቀሌ ጉባዔ ለየት የሚያደርገው ከግዕዝ ወጣ ብሎ በሥነ-ፈውስ ላይ ትኩረት ማድረጉ ጭምር መሆኑ ነው። የግእዝ ቋንቋ በሥነ-ፈውስ ደረጃ ምን ይላል የሚለው ጥያቄ መልስ የሚሰጥባቸው፣ አቅጣጫና መፍትሄ የሚቀርብባቸው ጥናታዊ ጽሑፎች በጉባዔው የሁለት ቀን ውሎ ይቀርባሉ ተብሎ ታሳቢ ተደርጓል።ሥነ-ፈውስ ኅሊናዊ፣ ሥነ-ፈውስ ሥጋዊ፣ ሥነ-ፈውስ መድኃኒታዊ፣ ሥነ-ፈውስ መንፈሳዊ፣ እያልን ብዙ ነጥቦችን ማንሣት እንችላለን። ሰው በጎ አስተሳሰብ እንዲኖረው፣ ለአገር፣ ለወገን፣ እንዲኖር ጤናማና ያልተዛባ አእምሮ እንዲኖረው ያስፈልጋል። ሁሉን ጎጂ አድርጎ የሚመለከት አእምሮዊ ህልውናዊ እንደሚያስፈልገው አምናለሁ። በዚህ ጉባዔ የስነ-ፈውስ ደረጃ ምንድነው የሚለውን ጥያቄ መልስ የሚሰጡ አማራጮችን በስፋት መዳሰስና በጉባዔው ማጠቃለያም የተሳታፊዎች ንቁ ተሳትፎና ውይይት ለቋንቋው ልማት ለምናካሂደው ተግባራዊ እንቅስቃሴዎች ሊያግዙ የሚችሉ ምክረ-ሀሳቦች እንደሚመጡ ያለኝ ተስፋ ላቅ ያለ ነው በማለት መልዕክታቸውን በማስተላለፍ ጉባዔው በይፋ አስጀምረዋል።

    5ኛው ሀገር አቀፍ የግዕዝ ጉባዔ በተያዘለት መርሃ-ግብሮች መሠረት በግእዝ ላይ የተደረጉ የተለያዩ የጥናትና ምርምር ስራዎች ቀርበው ገለፃና ውይይት ተደርጎባቸዋል። እነዚህም ግዕዝና ሥነ-ፈውስ በመጋቤ ምስጢር ፍሬስብሃት ዱባሌ (ከኢ.ኦ.ተ. ቤተ ክርስቲያን)፣ ግዕዝና ለፈውስ የሚደረስ ጸሎት በዶ/ር አባ ዳንኤል አሰፋ (ከፍራንቺስኮ ካቶሊክ ዩኒቨርሲቲ)፣ ግዕዝና የባህል መድሃኒት በመጋቤ ምስጢር ስማቸው ንጋቱ (ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ)፣ ዘይትረከቡ በውስጠ ልሳነ ግዕዝ ሕቡኣነ ስመ እግዚአብሔር ዘይህቡ ፈውሰ ድኅነት በአቶ ሃፍተ ንጉስ (ከአዲግራት ዩኒቨርሲቲ)፣ ግዕዝ (The General Features of the Geez Magical Texts) በአቶ ጉኡሽ ሰለሞን (ከአዲግራት ዩኒቨርሲቲ)፣ ጸበልና ማየ ጸሎት በግዕዝ ባህል ወፊዚክስ በዶ/ር ሀጎስ አብርሃ (ከመቐለ ዩኒቨርሲቲ) ይገኙበታል።

    ምንጭ፦ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የግዕዝ ጉባዔ


    Semonegna
    Keymaster

    መንግሥት ሆይ፥ የጤና ባለሙያውን ጥያቄ ከልብህ አድምጥና መፍትሄ ስጥ
    (ዶ/ር አክሊሉ ደበላ)

    አሁን ነገሮች ወዴት እያመሩ እንደሆነ ሁሉም እያየው ነው። አነሰም በዛ መንግሥትም በዚህ ምክንያት መጨነቁ አልቀረ። በዚህ ችግር የሚነካካ አካል ብዙ እንደሆነም አምናሁ። የጤና ባለሙያው፣ መንግሥትና ሕዝብ ሳይወዱ በግድ ባለጉዳዮች ናቸው። የባለሙያው ጥያቄ ግልጽ ሆኖ ቀርቧል። በዚህ ጥያቄ ላይ የተለያየ አስተያየት ያላቸው ሰዎች አሉ። የሚሰጡትም አስተያየቶች ነገሩን የከፋ እንዳያደርጉ መጠንቀቅ ከሁሉም ይጠበቃል።

    የሐኪሙ ጥያቄ ዛሬ የበቀለ የሚመስላቸው ተሳስተዋል። ጥያቄውም ሆነ ተግባር ያልታየበት የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር መልስ ሲንከባለሉ ቆይተው ዛሬ ወደ አደባባይ የወጡ ናቸው። “እስከዛሬ የት ነበራችሁ?” ማለት ቢቻልም በጥልቅ ሲታሰብ ልክ አይሆንም። የመቶ ዓመት ጥያቄ እንኳን ቢሆን የሆነ ጊዜ በሥርዓቱ መመለስ አለበት። ችግሮቹን የፈጠረ የዶ/ር አቢይ መንግሥት ነው ያለ የለም፣ መመለስ ያለበት ግን አሁን እሱ ነው። ሕዝቡ በደፈናው በሐኪሙ ላይ መጥፎ አስተያየት ከመስጠቱ በፊት ነገሩን አዙሮ አዟዙሮ ቢያስብ መልካም ነው። ዛሬ ገንፍሎ የወጣው ጩኸት የፖለቲካ ሁኔታ ምቹ ስለሆነ ብቻ አይደለም (መሆኑ አንድ ነገር ቢሆንም)፤ ይልቅስ እየተባባሰ የመጣው የችግሩ ተፈጥሮ ራሱ የመገንፈል ልክ ላይ ደርሶ ነው እንጂ። እዚህ ላይ የደረሰውን ጉዳይ ሁሉም በጥንቃቄ ካልያዘ ጉዳቱ ከተፈጥሯዊነት ይልቅ ሰው-ሠራሽ አንዳናደርገው።

    ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የተጠየቀውን ነገር ለመመለስ ምን ያህል እምነት የሚጣልበት አካል እንደሆነ አላውቅም። ነገሮችን እየመለሰ ያለበት አኳኋን ግን መልካም አይደለም። እስከሚገባኝ ድረስ በውይይቱም ላይ ለመመለስ ቃል የገባባቸው ጉዳዮች ራሱ ሲፈጽም የነበረ ሕግን የጣሰ አሠራር ነው። የሀገሪቷን ሕግ ጥሶ ወጪ መጋራትን (cost-sharing) ቢያስተካክል ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ሲሠራ የነበረውን የወንጀል ሂሳቡን አወራረደ ይባላል እንጂ የሐኪሙን ጥያቄ መለሰ ተብሎ ለዜና የሚቀርብ ጉዳይ አልነበረም። ወሃ የማይቋጥር ጥቃቅን ነገሮች አስር ጊዜ እንደሰበር ዜና የሚለጥፍበት መንፈስ ግን አስቂኝ ነው። ስጠረጥር ግን ባለሙያውን ንዴት ውስጥ በመክተት ይበልጥ እንዲገፉበት የፈለገም ይመስለላል። ከሳምንታት በፊት ሰምተን ያለቀውን ጉዳይ ዛሬ በሰበር ዜና ባገኘው ሚዲያ ሁሉ ማስተጋባት የቅንነት ልቡን የሚታመን አያደርገውም። ጊዜያዊ ስሜቱን ማብረድም ሆነ ዘላቂ መፍትሄውን በሰከነ መንገድ መመለስ ይጠበቅበታል እንጂ የብልጣብልጥነት ጨዋታ በመገናኛ ብዙሃን (ሚዲያ) በኩል መጫወት አይጠቅምም።

    ሌላው ከዶ/ር አቢይ ጋር ተያይዞ፡- እንደሚታወቀው ባለፈ ከሕክምና ማኅበረሰብ ጋር ያደረገው ውይይት ብዙዎችን አስከፍቷል። በዚህም የተነሳ የብዙ ሐኪሞች የሥራ ሞራል ወርዷል፣ የብዙዎች ስሜት ቀዝቅዟል። በዚህ ብቻም የተነሳ ብዙ ህመምተኞች ይጎዳሉ፤ ተጎድተዋል። ይህ እንግዲህ ከጥያቄዎቻቸው ጋር ቀጥተኛ ተዛምዶ የሌለው ተጨማሪ ችግር ነው። የአንድ አገር መሪ በተናገረው ነገር የሚበላሸው ብዙ ነገር እንደሆነ ግልጽ ነው። የዚህንም ፍሬ አይተነዋል። ለዚህ ትክክለኛው መድኃኒት እርምት ነው። ስለ ባለሙያው ክብርም ባይሆን ስለሚበደሉቱ ህመምተኞች ሲባል፣ የተነገረውም በአደባባይ ስለሆነ፣ የዶ/ር አቢይ መንግሥት በአደባባይ ይቅርታ ቢጠይቅ አገር ትጠቀማለች።

    ሌላው ከሕክምና ስነምግባርና ሀገሪቱ ካለችበት ሁኔታ አንጻር የተለያየ አስተያየት የሚሰጡ ሰዎች አሉ። እርግጥ ነው ሀገሪቷ ገና አልተረጋጋችም፤ እርግጥ ነው የሐኪሞቹን ጥያቄ ለራሳቸው የፖለቲካ አጀንዳ ሊያውሉ የሚፈልጉ አካላት ሊኖሩ ይችላሉ። ይህን ለማስቀረት ኃላፊነት ያለበት ደግሞ ጠያቂው ሐኪም ብቻ ሳይሆን ተጠያቂው መንግሥትና ተመልካቹ ማኅበረሰብም ጭምር ነው። መመለስ ባለበት መንገድ ካልተመለሰ ባልተፈለገ መንገድም ሊወድቅ ይችላል፤ ስጋቱ የሁሉም ነው። ይህን ተፈጥሯዊ ዕጣውን በመዘንጋት ከየአቅጣጫ ጠያቂውን ብቻ መውቀስ ተገቢ አይደለም፤ ጥያቄውንም ማራከስ ይሆናል። እርግጥ ነው ሕክምና በተቻለው መጠን ሁሉ ህመምተኛን ማስቀደምን ይጠይቃል። ይህን ጠያቂዎቹም ያውቃሉ። ይሁንና የሕክምና ሥራ የሚሠራው ሰው ሆኖ መኖር ከተቻለ ብቻ መሆኑን መዘንጋት የለብንም። በብዙ ቦታዎች ያለው እውነታ ደግሞ የደኅንነት ስጋት ጉዳይ ስለሆነ ከሁሉም ይቀድማል– ከሕክምናም። ይህን ችግር ግን ብዙ ሰው የተረዳው አይመስለኝም። ብዙዎቹ ጥያቄዎች ደግሞ ቀጥታ ለህሙማኑ ጥቅም የሚውሉ ናቸው። በአሠራር ብልሹነት መሥራት አልቻልንም ማለት እንደ አገር ቢታሰብ ትልቅ ችግር ነው እንጂ የሕክምና ባለሙያ ጥያቄ ብቻ ተደርጎ ባልተወሰደ ነበር።

    ከማኅበራዊ ድረ-ገጾች ጩኸት እስከ ሥራ ማቆም ተደርሷል። ነገሮች በዚሁ የሚሄዱ ከሆነ ደግሞ ሥራ ማቆሙ እየተስፋፋ ሄዶ የብዙዎቹ ሕይወት እስከ መቅጠፍ ሊደርስ ይችላል። ማኅበራዊ ቀውስ ሊያስከትል የሚችል ጉዳይም ሊሆን ይችላል እና ሁሉም ቆሞ ቢያስብበት ሸጋ ነው። “መንግሥትስ በዚህ አስቸጋሪ ጊዜ ላይ ሆኖ የሕክምና ባለሙያን ጥያቄ መመለስ ይችላል ወይ?” ከተባለ “አዎ ይችላል።” ምናልባትም ጊዜ የሚፈልጉ አንዳንድ ከባድ ጥያቄ የሆኑበትም ካሉ አመላለሱን ያማረ በማድረግ መተማመንን መፍጠር ይችላል። አሁን እየሄደ ባለበት መንገድ ግን አይደለም። ለዚህም ነው “መንግሥት ሆይ፥ የጤና ባለሙያውን ጥያቄ ከልብህ አድምጥና መፍትሄ ስጥ!” የምንለው።

    አክሊሉ ደበላ (የሕክምና ዶ/ር)
    ——
    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    መንግሥት የጤና ባለሙያዎች ጥያቄ


    Semonegna
    Keymaster

    በምክክር በድረኩም የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ አዲሱ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሐብታሙ አበበ ዩኒቨርሲቲውን በታታሪነት፣ በታማኝነት እና በቅንነት በማገልገል ዩኒቨርሲቲውን የልሂቃን ተቋም እና የመጀመሪያ ተመራጭ ዩኒቨርሲቲ ለማድረግ ተግተው እንደሚሠሩ ገልጸዋል።

    ሆሳዕና ከተማ (ሰሞነኛ)– ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ለአራት ወራት ያህል ለዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንትነት መረጣ ሲያካሂድ ቆይቶ፥ ለመጨረሻ ዙርም ዶ/ር ሐብታሙ አበበ፣ ዶ/ር ኑሪ ላፌቦ እና ዶ/ር አብርሃም አለማየሁ አልፈው ነበር። ከእነዚህ ሦስት ዕጩ ተወዳዳሪዎች መካከልም ዶ/ር ሐብታሙ አበበ በአጠቃላይ ውጤት 69.57% በማስመዝገብ ለዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንትነት ብቁ መሆናቸውን አስመስክረው፣ የኢፌዴሪ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚያዝያ 24 ቀን 2011 ዓ.ም. ለዩንቨርሲቲውና ለሚመለከታቸው ቢሮዎች በፃፈው ደብዳቤ ዶ/ር ሐብታሙ አበበን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ሆነው ተሹመዋል።

    የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ሆነው የተሾሙት ዶ/ር ሐብታሙ አበበ ለፕሬዝዳንትነት ሲወዳደሩ ያቀረቡትን የዩኒቨርሲቲውን የእድገት ስልታዊ ዕቅድ (University’s Development Strategic Plan) በይበልጥ ለማስገንዘብ እና በዩኒቨርሲቲው ውስጥ የላቀ ታታሪነት፣ ትብብር እና ስኬታማ የመማር ማስተማር፣ የምርምር እና የማኅበረሰብ አገልግሎት ስኬቶችን ለማስመዝገብ የሚያስችላቸውን የመጀመሪያ ዙር ምክክር ከማኅበራዊ ሳይንስ፣ ንግድ እና ምጣኔ ሀብት (Business and Economics)፣ ከግብርናና ከተፈጥሮ ሀብት ኮሌጆች እና ከሕግ ትምህርት ቤት ጋር ግንቦት 5 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምረዋል።

    በምክክር በድረኩም ፕሬዝዳንቱ ዩኒቨርሲቲውን በታታሪነት፣ በታማኝነት እና በቅንነት በማገልገል ዩኒቨርሲቲውን የልሂቃን ተቋም እና የመጀመሪያ ተመራጭ ዩኒቨርሲቲ ለማድረግ ተግተው እንደሚሠሩ በመግለጻቸው ከተሰብሳቢ መምህራን አድናቆት ከመቸራቸውም በላይ በጋራ ራዕያቸውን ለማሳካት ተግተው አብረዋቸው እንደሚሠሩ መምህራኑ ቃል ገብተውላቸዋል።

    ፕሬዝዳንቱ እያደረጉት ያለውን የምክክር መድረክ ቀጥለው ግንቦት 6 ቀን 2011 ዓ.ም. በዩንቨርሲቲው ዱራሜ ካምፓስ፣ ግንቦት 7 ቀን በዋናው ካምፓስ ምህንድስና (Engineering)፣ ጤና እና የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ (Natural and Computational Sciences) ኮሌጆች፣ በመጨረሻም ግንቦት 8 ቀን በዩንቨርሲቲው የንግስት እሌኒ መሐመድ መታሰቢያ ሆስፒታል እና ከዩኒቨርስቲው የአስተዳደር ሠራተኞች ጋር እእንደሚቀጥል ታውቋል።

    ዶ/ር ሐብታሙ አበበ በሐምሌ ወር 2011 ዓ.ም. አንድራ ፕራዴሽ (Andhra Pradesh) ግዛት (ደቡም ምስራቃዊ ህንድ) ውስጥ ከሚገኘው አንድራ ዩኒቨርሲቲ (Andhra University) የዶክትሬት ዲግሪያቸውን አግኝተዋል።

    ምንጭ፦ ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ሐብታሙ አበበ


    Semonegna
    Keymaster

    እ.ኤ.አ በ2011 የተመሠረተው ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የሕክምና ዶክተሮችን ሲያስመርቅ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ጊዜ እንደሆነ ተገልጿል። ዩኒቨርሲቲው በአሁኑ ወቅት ስድስት ኮሌጆች፣ አንድ ትምህርት ቤት እና አንድ ተቋም (ኢንስቲትዩት) አለው። 

    ዓዲግራት (ሰሞነኛ)– ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ለመጀመርያ ግዜ ሰባት ሴቶች 25 ወንዶች በድምሩ 32 የሕክምና ዶክተሮችን (medical doctors) እንዲሁም በድኅረ መሠረታዊ መርሃግብር (post basic program) 30 ተማሪዎችን አስተምሮ መጋቢት 1 ቀን 2011 ዓ.ም. አስመርቋል። በዕለቱ የክብር እንግዳ የነበሩ የትግራይ ክልል ም/ር/መስተዳደር ክቡር ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ባስተላለፉት መልዕክት፥ በሃገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች ከፍተኛ የጤና ባለሙያዎች እጥረት እንዳለና ችግሮቻችን በማቃለል አንዳንዱን በመፍታት ልዩነት የሚያመጣ ድርሻ እንደሚኖራችሁ ባለ ሙሉ ተስፋ ነኝ ብለው መልእክታቸው አስተላልፍዋል።

    በዕለቱ የምርቃት ሥነ ስርዓት ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ሚኒስትር ድኤታ ወ/ሮ ስሃረላ ኣብዲላሂ በበኩላቸው የጤና ባለሙያ ማለት የግል ምቾትን እንደ መስዋዕትነት በመክፈል እንብካቤ ለሚያስፈልጋቸው እንክብካቤ መስጠት መሆኑን በማወቅ በየተኛውም የሃገሪቱ ክፍል ሄዳችሁ ያስተማራችሁን ህብረተሰብ ለማገልገል ዝግጁ እንድትሆኑ በማለት ለዕለቱ ተመራቂዎች መልዕክታቸውን አስተላለፈዋል። ዩኒቨርሲቲው የነበሩበትን ፈተናዎች ኣልፈው ለመመረቅ መብቃታችው በጣም የሚያኮራ ታሪክ መሆኑ የዩኒቨርሲቲው ግዝያዊ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ገ/መስቀል ገልፀዋል።

    ኬር ኢትዮጵያ በ7 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር ወጭ ያስገነባውን የምርምርና የስልጠና ማዕከል ለሐረማያ ዩኒቨርሲቲ አስረከበ

    ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የሕክምና ዶክተሮችን ሲያስመርቅ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሆነ ተገልጿል። ዩኒቨርሲቲው የተመሠረተው እ.ኤ.አ በ2011 ሲሆን፥ በአሁኑ ወቅት ስድስት ኮሌጆች፣ አንድ ትምህርት ቤት እና አንድ ተቋም (ኢንስቲትዩት) አለው። ከሁለት ዓመታት በፊት ዩኒቨርሲቲው ባወጣው የአሃዝ ዘገባ በአጠቃላይ ከ16,000 በላይ ተማሪዎች በመደበኛው፣ እንዲሁም ከ6,000 በላይ ተማሪዎች በተከታታይ (continuing education) መርሀ ግብር እያስተማረ ይገኛል።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ


    Semonegna
    Keymaster

    አምቦ (ኢዜአ) – አምቦ ዩኒቨርሲቲ ”ዳክዬ” የተባለ አረምን በምርምር አውጥቶ ለእንስሳት መኖነት ጥቅም ላይ ማዋሉን አስታወቀ። ተቋሙ በተጨማሪም አትክልትን የሚያጠቃ ተባይን ለመከላከል ለአርሶ አደሩ ድጋፍ እየሰጠ ነው።

    ዩኒቨርስቲው በግብርና፣ በጤና፣ በአካባቢ ጥበቃና በሌሎችም ዘርፎች ከ100 በላይ ችግር ፈቺ የምርምር ፕሮጀክቶች አሉት። ከእነዚህ ውስጥ በተለይ ”ዳክዬ” የተባለ አረምን ከአሜሪካ ዓለም አቀፍ የልማት ተራድኦ ድርጅት ጋር በመተባበር ላለፉት ሦስት ዓመታት ባደረገው ምርምር ውጤታማ መሆናቸውን በዩኒቨርሲቲው የምርምርና ማኅበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዘዳንት ዶ/ር ብዙነሽ ሚዴቅሳ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ገልጸዋል።

    በምርምር የተገኘው አረም ለመኖነት የሚውለው በመጠለያ ውስጥ ውሃ በተጨመረባቸው ገንዳዎች በማባዛት በማከናወን ከሌላ የእንስሳት ጋር 20 በመቶው ያህሉ በማደባለቅ ነው።

    በኦሮሚያ ክልል አቦካዶ አምራች ገበሬዎች የተሻሻሉ ዘሮችን በመጠቀም ምርታቸውን ማሳደግ ችለዋል

    ገንቢ የሆኑ ንጥረ ነገሮቹን በመያዙ በአሁኑ ወቅት ለወተት ላሞች፣ እንቁላልና ለስጋ ዶሮዎች መኖ በማዋል ውጤታማ መሆናቸውን ዶ/ር ብዙነሽ አስረድተዋል። እስካሁንም መኖውን የሚጠቀሙ ዶሮዎች እንቁላላቸው ከውጭ ዝርያዎች የተለየ፣ የአስኳሉ ቀለም ቢጫና መጠኑም ከፍ ያለ እንዲሁም የወተት ላሞችን ለሰባት ወራት ያህል ምርት ለመስጠትበ ያስችላቸዋል ብለዋል።

    በቀላሉ የሚዘጋጅ በመሆኑ ለእንስሳት መኖ የሚወጣውን ወጪ የሚቀንስ ከመሆኑም በላይ ምርታማነትንም እንደሚጨመር አመልክተው፣ ስለአጠቃቀሙ በማህበር ለተደራጁ ሴቶች ስልጠና ሰጥተው እየተሰራበት መሆኑን ምክትል ፕሬዚዳንቷ ተናግረዋል።

    አትክልትና ሌላውን አዝርዕት የሚያጠቃ ተባይን ለመከላከል ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ከውጭ የሚገቡ ኬሚካሎችን ውጤታማነታቸውን በመስክ ሙከራ ተረጋግጦ ሥራ ላይ እንዲውሉ መደረጉንና ለአርሶ አደሩም ድጋፍ እየሰጡ መሆናቸውንም አመልክተዋል።

    ዶ/ር ታደሰ ሽብሩ የዩኒቨርሲቲው ተመራማሪና መምህር ናቸው። በተባይ ምክንያት በተለይ በሽንኩርት፣ ጥቅል ጎመንና ቲማቲም ላይ የሚደርሰው ተጽዕኖ ለመከላከል ለአርሶ አደሩ የመድኃኒት አቅርቦትና የምክር አገልግሎት በነጻ በመስጠት እያገዙ መሆናቸውን ተናግረዋል። በዚህም ውጤታማ በመሆን አገልግሎቱን ለማስፋፋት ጥረት እያደረጉ ናቸው።

    የዩኒቨርስቲው ባለሙያዎች ባደረጉላቸው ድጋፍ ተባይ በአትክልታቸው ላይ ያደርስባቸው የነበረው አሁን መቃለሉን የተናገሩት ደግሞ በምዕራብ ሸዋ ዞን ቶኬ ኩታዬ ወረዳ የደጋ ፍሌ ቀበሌ አርሶ አደር እሸቱ ለሚ ናቸው።

    በአምቦ ከተማ የቀበሌ ሁለት ነዋሪ ወ/ሮ ትዕግስት አበበ በበኩላቸው ከ11 ሴቶች ጋር ተደራጅተው ዩኒቨርሲቲው ባመቻቸላቸው የመኖና የስልጠና ድጋፍ በዶሮ እርባታ ላይ በመሰማራት ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል። በተለይ የዶሮዎቹ እንቁላል ከሽያጭ አልፎ ለልጆቻቸው ምግብነት በማዋል ተጠቃሚ እንደሆኑ ገልጸዋል።

    አምቦ ዩኒቨርስቲ በቀጣይነትም የምርምር ውጤቶችን ለሁሉም የአካባቢው ወረዳዎች ለማዳረስ ሥራውን እንደሚያጠናክር አመልክቷል።

    ምንጭ፦ ኢዜአ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    አምቦ ዩኒቨርስቲ ዳክዬ


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትና የውጪ ምንዛሬ እጥረት ለሀገር በቀል የመድኃኒት እና የሕክምና መገልገያ አምራቾች እውነተኛ ፈተና መሆን አለመሆናቸው በገለልተኛ አካል ሊጠና ይገባል ሲሉ የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅርቦት ኤጀንሲ ባለድርሻ አካላት ተናገሩ።

    ጥር 24 ቀን 2011 ዓ.ም ከሀገር ውስጥ አምራቾች በተደረገው ውይይት የ6 ወር የመድኃኒት አቅርቦት አፈፃፀም 25% መሆኑን ተከትሎ ለአቅርቦቱ ዝቅተኛ አፈፃፀም በተደጋጋሚ በምክንያትነት የሚሰጡት የውጭ ምንዛሪ እጥረትና የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ በገለልተኛ አካል ተጠንቶ ድጋፍ የሚያስፈልገውን በመደገፍ የሚያጭበረብረውን በማጣራት እርምጃ ሊወሰድበት ይገባል ሲሉ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ገልፀዋል።

    ኤጀንሲው ለሀገር ውስጥ አምራቾች በቅድሚያ ክፍያ እንዲሁም 25 በመቶ ጨረታ ላይ እንዲወዳደሩ እንደሚደግፉ የተጠቀሱት አስተያየት ሰጪዎቹ አሁንም አምራቾች መድኃኒቶችን በበቂ መጠን ጥራት ማቅረብ አለመቻላቸው አጠራጣሪ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

    ◌ News: Humanwell Healthcare Group inaugurates Humanwell Pharmaceutical Ethiopia PLC in Chacha town

    እንደአስተያት ሰጪዎች ገለጻ ሀገር በቀል አምራቾች ኤጀንሲው የሚሰጣቸው የቅድሚያ ክፍያ ሒሳብ በአግባቡ ቃላቸውን ለመተግበር እያዋሉት መሆኑ ወይም ሌላ ዓላማ መዋሉ ሊጠና ይገባል ብለዋል። አክለውም የሚሰጠውን ገንዘብ ለሌላ የግል ንግድ እየተጠቀሙበት መሆኑን ጥርጣሬ እንዳላቸው ገልጸዋል።

    በተያያዘ ዜና የቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊዎች በአዳማ ከተማ የግማሽ ዓመት አቅድ አፈጻጸም ላይ እንዳሉት ሀገር በቀል የመድኃኒት አምራቾች ኤጀንሲው በሚያቀርበው ገንዝብ ለግል አቅራቢዎች ትርፍ ለማሳደድ እንደሚያውሉት መረጃ አለ ሲሉ ተናግረዋል። ከዚህ በተጨማሪም የሚደረገው ድጋፍ በአግባቡ የመያጠቀሙበት ከሆነ በሂደት እየለዩ እርምጃ ለወሰድ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።

    ከዚሁ ውይይት በተጨማሪ የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅርቦት ኤጀንሲ የጀመረውን ለውጥ ለማስቀጠል አቅርቦቱን የበለጠ ለማሻሻል ብቻውን መስራቱ ውጤታማ ሊያደርገው እንደማይችል የኤጀንሲው የግዥ ትንበያና ገበያ ጥናት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አብይ ክፍሎም አብራርተው የሀገር ውስጥ አምራቾቹ ሊያስቡበት እንደሚገባም አቶ አብይ አክለው ገልፀዋል።

    ◌ News: SanSheng Pharmaceutical PLC inaugurated in the Eastern Industry Zone in Dukem, Ethiopia

    የአገር ውስጥ አምራቾች አፈፃፀማቸውን መፈተሽ እንዳለባቸውና አፈፃፀማቸው ዝቅ ባለ ቁጥር በመድኃኒት እጦት የሚያልፈውን የሰው ሕይወት ሊያስቡ እንደሚገባ የመድኃኒትና የህክምና መሣርያዎች ግዢ ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ጎይቶም ጊጋር ገልፀዋል።

    የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ አቶ ሣሙኤል ኃይሉ በበኩላቸው በአሁኑ ሠዓት የመድኃኒት እጥረት እንደ ቀልድ የሚታይ ጉዳይ አይደለም ብለዋል።

    አቅርቦቱ ዝቅ እንዲል ካደረጉ ምክንያቶች መካከል የውጭ ምንዛሬና የመብራት መቆራረጥ በዋናነት በውይይቱ የተጠቀሱ ሲሆን ኤጀንሲው ይህን ለማስተካከል አፈፃፀማቸውን ለመለካት የሚያስችል ነጥቦችን የያዘ ረቂቅ ሰነድ (KPI) ቀርቦ የጋራ ማድረግ ተችሏል።

    በመጨረሻም ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር፣ ከብሔራዊ ባንክ፣ የኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት እና ሌሎች የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት መገኘታቸው በቀጣይ ችግሩን በመቅረፍ የሕብረተሠቡን የመድኃኒት ፍላጎት ለማሟላት ያስችላል ብለዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅርቦት ኤጀንሲ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ 

    የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅርቦት ኤጀንሲ


    Semonegna
    Keymaster

    ጎንደር (ሰሞነኛ)– በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እየተተገበረ ለሚገኘው የጤና መረጃ አብዮት ትልቅ የሰው ኃይል የሚፈጥር የቀጠና/ወረዳ ጤና መረጃ ሥርዓት (District Health Information System 2 – DHIS2) አካዳሚ እና የኤለክትሮኒክስ ጤና ፈጠራ ቤተሙከራ (e-health innovation lab) በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ግቢ ጥር 30 ቀን 2011 ዓ.ም ተመረቀ።

    በምረቃ ፕሮግራሙ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ደሳለኝ መንገሻ፣ የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር አበባው ገበየሁ፣ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ከፍተኛ ኃላፊዎች፣ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዚዳንቶች እንዲሁም በህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የሄልዝ ኢንፎርማቲክስ (Health Informatics) ትምህርት ክፍል የሁለተኛ እና ሦስተኛ ዲግሪ ተማሪዎች፣ የአቅም ግንባታ እና የሜንተርሽፕ ድጋፍ ፕሮጀክትን (Capacity Building and Mentorship Project – CBMP) ከሚተገብሩ ዩኒቨርሲቲዎች የመጡ ተሳታፊ መምህራን እና የጤና ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

    VIDEO: Ethio-American Doctors Group (EADG): Building a regional healthcare system & medical tourism

    የምረቃ መርሀግብሩን በንግግር የከፈቱት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ደሳለኝ መንገሻ የተመረቀው አካዳሚ በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እና በተመረጡ ዩኒቨርሲቲዎች እየተተገበረ የሚገኘውን የአቅም ግንባታ እና የሜንተርሽፕ ድጋፍ ፕሮጀክት (CBMP) ለመደገፍ ታስቦ የተከፈተ መሆኑን ገልፀው፤ በተለይ በአማራ እና በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለሚገኙ የጤና ተቋማት የሰው ኃይል በማሰልጠን ትልቅ ድጋፍ እንደሚያደርግ ተናግረዋል። ሀገሪቱ የያዘችውን የጤና መረጃ ሥርዓት በማዘመን የልህቀት ማዕከል ለመሆን ዩኒቨርሲቲው እየሠራ ይገኛል ብለዋል። ለተሳታፊዎች ለፕሮጀክቱ ቡድን አባላት እዲሁም ለጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እና ለክልሉ ጤና ጥበቃ ቢሮ ምስጋና አቅርበዋል ዶ/ር ደሳለኝ በንግግራቸው መብቂያ።

    በሀገራችን የሚታየው የጤና መረጃ አያያዝ ሥርዓት ከማሰባሰብ እስከ መረጃ መተንተን የሚታዩ በርካታ ክፍተቶች ያሉበት በመሆኑ እንደ DHIS2 ዓይነት ሥርዓቶችን መጠቀም ግድ መሆኑን የተናገሩት ዶ/ር አበባው፥ ዩኒቨርሲቲው በትክክለኛው ሰዓት አካዳሚውን በመክፈቱ ምስጋና ይገባዋል ብለዋል። ዶ/ር አበባው አያይዘውም ዩኒቨርሲቲው የአቅም ማጎልበቻ ስልጠናዎችን መስጠት አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበው የተጀመረው ሥራ እንደሀገርም እንደ ዩኒቨርሲቲም የሚያኮራ ነው ብለዋል።

    በአሁኑ ሰዓት 90 በመቶ የሚሆኑ የጤና ተቋማት በDHIS2 ሥርዓት ሪፖርቶችን ማቅረብ መጀመራቸው ከጤና ጥበቃ ሚንስተር የመጡ ኃላፊዎች ተናግረዋል። መሆኑም ተመርቆ የተከፈተው አካዳሚ የጤና ኬላዎችን በመከታተል እና በመገምገም ድጋፍ ማድረግ እንዲሁም ወረዳዎችን በመረጃ አያያዝ ሥርዓት ሞዱል የማድረግ ኃላፊነት እንዳለበት ኃላፊዎች ተናግረዋል።

    የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር ተቀራርቦ እየሠራ የሚገኘው ሥራ ለሌሎች ተቋማትም አርአያ መሆኑን የገለፁት ተሳታፊዎች፥ የ DHIS2 አካዳሚ በዩኒቨርሲቲው መከፈቱ የዩኒቨርሲቲውን አመራሮች እና አጠቃላይ የዩኒቨርሲቲውን ማኅበረሰብ የሚያኮር ሥራ መሆኑ ገልፀዋል።

    በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር በተያዘው የጤና መረጃ አብዮት ዙሪያ ማብራሪያ የቀረበ ሲሆን፥ ዶ/ር ቢንያም ጫቅሉ በአቅም ግንባታ እና የሜንተርሽፕ ድጋፍ ፕሮጀክት (CBMP) እስካሁን የተሠሩ ተግባራትን እና የወደፊት አቅጣጫዎችን አቅርበዋል። በቀረበው ሀሳብ ላይ ውይይት ተደርጎ መርሀ ግብሩ ተጠናቋል።

    District Health Information System 2 (DHIS2) ምን እንደሆነ በዝርዝር ለማንበብ እዚህ ይጫኑ (እንግሊዝኛ)

    ምንጭ፦ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    DHIS2


    Anonymous
    Inactive

    የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር በአዲስ አበባ የተለያዩ የጤና ተቋማትን ጎበኙ
    —–

    ኢትዮጵያ በጤናው ዘርፍ እያደረገች ያለችው እንቅስቃሴ ከጊዜ ወደ ጊዜ ከፍተኛ መሻሻሎችን እያሳየ መምጣቱ ተገለፀ፡፡

    የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሀኖም በዛሬው እለት አዲስ አበባ የሚገኘውን የጃን ሜዳ ጤና ጣቢያ እና የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታልን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡ ዋና ዳይሬክተሩ በጃን ሜዳ ጤና ጣቢያ በቤተሰብ ጤና ቡድን በጤና ጣቢያው ባለሙያዎች ቤት ለቤት እየተሰጡ ያሉ የጤና አገልግሎቶችንም በተገልጋዮቹ ቤተሰቦች ቤት በመገኘት ጎብኝተዋል፡፡

    የጃንሜዳ ጤና ጣቢያ ዝቅተኛ ኢኮኖሚ ላላቸው ግለሰቦች ቤታቸው ድረስ በመሄድ በአይነቱ አዲስ የሆነ የህክምና ግልጋሎት የሚሰጥ ሲሆን ታካሚዎቹ ተጨማሪ ህክምና ካስፈለጋቸው ወደ ጤና ጣቢያው ሪፈር እንደሚያደርጋቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡

    በቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ጉብኝታቸው መደሰታቸውን የገለፁት ዶ/ር ቴዎድሮስ ሆስፒታሉ የልብ ቀዶ ህክምና መጀመሩና በመመረዝ ህክምና ዙሪያ እያደረገ ያለው እንቅስቃሴ የሆስፒታሉን እመርታ እንደሚያሳይ ተናግረዋል፡፡

    “ጤና ለሁሉም” በሚለው የዓለም ጤና ድርጅት መርህ መሰረት የዓለም ጤና ድርጅት ከኢትዮጵያ ጋር በጋራ ለመስራት ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ዋናው ዳይሬክተሩ የተናገሩ ሲሆን የሀገሪቷ ከፍተኛ የጤና አመራሮች ለጤናው ዘርፍ ስርዓት መጠናከር የሰጡትን ትኩረት አድንቀዋል፡፡

    ምንጭ፦ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– በ2006 ዓ.ም. በሰባት የየመገናኛ ብዙሃን (ሚዲያ) እና ኪነ ጥበብ ባለሙያዎች የተቋቋመው ጉዞ ዓድዋ፥ አንድ ሺሕ አስር ኪሎሜትሮችን የሚሸፍን፣ ከኢትዮጵያ ዋና ከተማ አዲስ አበባ ተነስቶ መዳረሻውን የዓድዋ ድል አምባ ተራሮች ጫፍ ላይ የሚያደርግ ረዥም የእግር ጉዞ ነው። ላለፉት ስድስት ዓመታት ከጥር ወር ጀምሮ የዓድዋ ድል በዓል እስከ ሚከበርበት የካቲት 23 ቀን ድረስ ከስድስት ሳምንታት ላላነሰ በየዓመቱ ሳይቋረጥ የቆየው ጉዞ ዓድዋ፥ ዘንድሮ የኢትዮጵያዊነቱ ስሜት እጅግ ጎልቶ በጉዞው ላይ የሚሳተፉት ቁጥርም ጨምሯል። በዘንድሮው ጊዞ ዓድዋ 44 ተጋዦች ከአዲስ አበባ እና 4 ተጓዦች ከሐረር በአጠቃላይ 48 ተጓዦች ጥር 7 ቀን 2011 ዓ.ም. ቀን ከአዲስ አበባ ተነስተዋል።

    የመላው አፍሪቃውያን ድል እስከመባል የደረሰው ታላቁ የዓድዋ ድል፥ የግዝፈቱን ያህል ክብር እና መታወሻ ሥነሥርዐት ሳይኖረው እየተከታተለ ከመጣው ትውልድ ጋር የበዓሉ አከባበር ዐውድ እየወረደ ጭራሽ እየተዘነጋ እና እየደበዘዘ መሔድ ያሳሰባቸው የጉዞ ዓድዋ መሥራቾች ትውልዱ ትኩረት ሰጥቶ የድሉን መንፈስ እንዲጋራ ለማድረግ ይህንን የጉዞ ሐሳብ አመንጭተዋል።

    ◌ የጉዞ ዓድዋ ተጓዦችና የኢትዮጵያዊያን አስተያየት

    በዚህም የተነሣ ጉዞ ዓድዋ ባለፉት ስድስት ዓመታት ብቻ ከታለመው ዓላማ አንጻር ከፍተኛ የሆነ አመርቂ ውጤት በማስመዝገብ የዓድዋ ድል በዓል ቀድሞ ከነበረበት አከባበር የላቀ ተሳትፎ ያለው የድል በዓል እንዲሆን አስተዋጽዖ ለማድረግ ተችሏል።

    ጉዞውን ከማካሔድ በተጓዳኝ በየመንገዱ ተንቀሳቃሽ የመጻሕፍት ንባብ መሰናዶ በማካሔድ በየዓመቱ የሚጓዙ አባላትን በዓድዋ ጦርነት እና ድል ዙሪያ በቂ የሆነ ግንዛቤ እና ዕውቀት የማጋራት ዝግጅቶችን ሲያካሂድ ቆይቷል። ከአንድ ወር በላይ በተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን ሰፊ ሽፋን የሚሰጠው የጉዞው የዕለት ተእለት ውሎ፣ በዓሉ ከመድረሱ አስቀድሞ በበርካታው ሕዝባችን ላይ የካቲት 23 ዕለትን በጉጉት የመጠበቅ ስሜት እንዲፈጠር አድርጓል።

    ◌ የዓድዋ ድል በዓል በጎሰኞች ዓይን የዲያቆን ዳንኤል ክብረት መጣጥፍ

    ከዚህ ቀደም የድል በዓሉ በብቸኝነት ከሚከበርባቸው የአዲስ አበባ እና የዓድዋ ከተሞች በተጨማሪ ከ28 በላይየሚሆኑ የክልል ከተሞች እና በርካታ ሕዝብ የሚኖርባቸው የገጠር ወረዳዎች ተጓዥ ቡድኑ በየደረሰበት በሚኖሩ ደማቅ አቀባበሎች ላይ በሚሰጡ የግንዛቤ መስጫ መልዕክቶች ስለ ዓድዋ ድል ታሪክ ግንዛቤ በመሰጠቱ የበዓሉአከባበር ከፍተኛ ለውጥ በማምጣት ላይ ይገኛል። የጉዞ ዓድዋ ትሩፋቶች፦

    • በዓድዋ ከተማ ውስጥ በአምስት ዓመት አንድ ጊዜ ብቻ የነበረው የዓድዋ ድል በዓል አከባበር ሥነ ሥርዐትበየዓመቱ እንዲካሔድ አስችሏል።
    • የበዓሉ አከባበር በፌደራል መንግሥት ደረጃ እንዲከበር ልዩ ትኩረት እንዲሰጠው ከፍተኛ አስተዋጽዖ አድርጓል።
    • ከ120 ዓመታት በፊት መቀሌ ከተማ በሚገኘው የእንዳየሱስን ምሽግ ለማስለቀቅ ከጣሊያን ጦር ጋር ሲዋጉ ሕይወታቸው ያለፉ ጀግና ኢትዮጵያውያን አጽም የትም ተበታትኖ በመቅረቱ፥ ጉዞ ዓድዋ በአሁኑ ሰዓት የቦታው አስተዳዳሪ የሆነውን የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ በማንቃት፤ የካቲት 26 ቀን 2008 ዓ. ም አጽማቸውን አሰባስቦ በክብር እንዲያርፍ ተደርጓል። ከዚህም ባሻገር በዓመቱ የካቲት 26 ቀን 2009 ዓ.ም በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ወጪ “የጀግኖች ኢትዮጵያዊያን መታሰቢያ ሙዚየም” የተሰኘ ጣራ አልባ ቤተ መዘክር በእንዳየሱስ ታሪካዊ ምሽግ ላይ ተገንብቶ ለመመረቅ በቅቷል።
    • የዓድዋ ጦርነት መንስዔ የሆነው የዉጫሌ ውል የተፈረመበት “ይስማ ንጉሥ” የተባለው ታሪካዊ ቦታ ተከልሎ ጥበቃ እንዲደረግለት በማድረግ ጉዞ ዓድዋ ቁልፍ ሚና ተጫውቷል። ከዚህም በተጨማሪ ውሉ በተፈረመበት ዕለት ሚያዝያ 25 ቀን በየዓመቱ፤ ምሁራዊ ተዋስዖ የሚደረግባቸው መድረኮች በመፍጠር፣ ላለፉት ስድስት ዓመታት ባበረከተው የላቀ አስተጽዖ የአምባሰል ወረዳ የዓድዋ ድልን ለመዘከርና ቦታውን የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ ያለመቋሚ ቤተ መዘክር በቦታው ላይ እንዲገነባ የሚያስችል የ19 ሚልዮን ብር የበጀት ድጋፍ ከአማራ ክልል መንግሥት እንዲያገኝ ጉዞ ዓድዋ ቁልፍ ሚና ተጫውቷል።
    • ለበርካታ ዓመታት አገልግሎቱ ተዘግቶ የቆየው በዳግማዊ ዐፄ ምኒልክ የትውልድ መንደር “አንጎለላ” የሚገኘው የዳግማዊ ዐፄ ምኒልክ መታሰቢያ ክሊኒክ እንዲከፈት ከፍተኛ ቅስቀሳ በማድረግ፤ በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ድጋፍ ክሊኒኩ ታዳጊ የጤና ጣቢያ ሆኖ በድጋሚ አገልግሎት እንዲሰጥ ጉዞ ዓድዋ አስተዋጽዖ ካደረጉ መካከል ግንባር ቀደሙን ሚና ተጫውቷል።
    • የዓድዋ ጀግና የሆኑት ራስ አሉላ አባ ነጋ የቀብር ቦታ በሆነው የአባ ገሪማ ገዳም ውስጥ ለሁለቱም ጾታዎች ጉብኝት ምቹ በሆነ ቦታ ላይ ሐውልት እንዲቆምላቸው ጉዞ ዓድዋ ባመቻቸው ዕድል በአንድ ባለ ሀብት ሐውልታቸው ተሠርቶ ለምረቃ በቅቷል።
    • በየዓመቱ በሚካሔዱ ጉዞዎች ከዓድዋ ድል ጋር ግንኙነት ያላቸው ቦታዋችን እና ልዩ ታሪካዊ መረጃዎችን በምስል እና በጽሑፍ በመሰብሰብ ለጥናትና ምርምር አስተዋጽዖ ማበርከት የሚችሉ የታሪክ ግብዓቶችን በማደራጀት በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች በተለይም የማኅበራዊ ድረ ገጽን በመጠቀም ቅርሶችን የማስተዋወቅና የመጠበቅ ሥራዎችንበ መሥራት ላይ ይገኛል።

    የጉዞ ዓድዋ ማኅበር የዓድዋ ድል በዓል በኢትዮጵያውያን እንዲሁም በጥቁር አፍሪካውያን ዘንድ የሚገባውን ክብር እንዲያገኝ ላደረገው ጥረት፣ ከላይ ለተጠቀሱት እና በየዓመቱ በሚያደርጋቸው እጅግ አመርቂ ክንዋኔዎች ምክንያት በ2009 ዓም በቅርስና ባሕል ዘርፍ የዓመቱ በጎ ሰው ተሸላሚ ሆኗል።

    ላይ የሚሳተፉ ተጓዦች በጉዞአቸው ላይ የሚያደርጓቸውን የተለያዩ ክንዋኔዎችና የሚዘግቧቸውን ታሪክ ተኮር ዘገባዎች ለመከታተል የማኅበሩን የፌስቦክ ገጽ ይጎብኙ።

    ◌ ዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ እና ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ በደብረ ብርሃን ከተማ ሃውልት ሊቆምላቸው ነው

    ምንጭ፦ በጎ ሰው ሽልማት / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ጉዞ ዓድዋ


    Anonymous
    Inactive

    እሁድ ጥር 5 ቀን 2011 ዓ.ም. ሁለተኛው ዙር ከትራፊክ ፍሰት ነፃ መንገዶች ቀን (car free day) በአዲስ አበባ፣ ባህር ዳር፣ ሀዋሳ፣ ጅማ፣ መቀሌ፣ ጅጅጋ እና ድሬደዋ በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል።

    የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር

    Semonegna
    Keymaster

    በአስር ሺህ ካሬ ሜትር ላይ በ58 ሚሊዮን ብር ወጪ በአዳማ ከተማ የተገነባዉ ጊዜ ያለፈባቸው እና ጥቅም ላይ የማይውሉ መድኃኒቶችን ማስወገጃ ማዕከል 10 ሺህ ኪሎ ግራም በሰዓት የማቃጠል አቅም ያለው ሲሆን፥ በሌሎች 7 ከተሞችም 500 ኪሎ ግራም በሰዓት ማቃጠል የሚችሉ ማዕከላትም በመገንባት ላይ ይገኛሉ።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የኢትዮጵያ የመድኃኒት ፈንድና አቅርቦት ኤጀንሲ በ100 ቀናት ዕቅድ የመጠቀሚያ ጊዜ ያለፈባቸው እና በተለያዩ ምክንያቶች ጥቅም ላይ የማይውሉ መድኃኒቶችን እና የህክምና ግብአቶችን ማስወገጃ ማዕከል ገንብቶ አስመረቀ።

    በአስር ሺህ ካሬ ሜትር ላይ በ58 ሚሊዮን ብር ወጪ በአዳማ ከተማ የተገነባዉ ጊዜ ያለፈባቸው እና ጥቅም ላይ የማይውሉ መድኃኒቶችን ማስወገጃ ማዕከል (incinerator) ምረቃ ሥነ ስርዓትላይ የተገኙት የኢፌዴሪ የጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ ዶ/ር አሚር አማን እንደተናገሩት፥ ማዕከሉ 10 ሺህ ኪሎ ግራም በሰዓት የማቃጠል አቅም ያለው ሲሆን፥ በሌሎች 7 ከተሞችም 500 ኪሎ ግራም በሰዓት ማቃጠል የሚችሉ ማዕከላትም በመገንባት ላይ ይገኛሉ ብለዋል። በቅርቡም ግንባታቸው ተጠናቆ አገልግሎት እንደሚጀምሩ ዶ/ር አሚር አክለው ተናግረዋል።

    ጊዜ ያለፈባቸው መድኃኒቶች እና ግብዓቶች ማስወገጃ ማዕከሉ ለሀገራችን የመጀመሪያ ሲሆን ከዚሀ ቀደም በየተቋሟቱ በተለያዩ ምክንያቶች ጥቅም ላይ የማይውሉ ወይም የተበላሹ መድኃኒቶችን በማስወገድ ረገድ ይገጥሙ የነበሩ ችግሮችን ከመሠረቱ እንደሚፈታ የገለጹት ሚኒስትሩ፥ የምለሳ ሎጂስቲክ (recycle logistic) ስርዓትን በመተግበር የማያገለግሉ የህክምና ግብአቶች እና በባኅሪያቸው ጎጂ የሆኑ ኬሚካሎችን በዘመናዊ መንገድ አካባቢን በማይበክል ሁኔታ በማስወገድ ከዚህ ቀደም አካባቢ የሚበከልበትን ሁኔታ እንደሚያስቀር ተናግረዋል።

    የኢትዮ-አሜሪካውያን ዶክተሮች ቡድን እያስገነባ ያለው ዓለም አቀፍ አገልግሎት ይሰጣል ተብሎ የሚጠበቀው ሆስፒታል

    ለዚህ ሥራ መሳካት ተባባሪ የሆኑ ያካባቢው ማኅበረሰብ አባላትና የአዳማ ከተማ ከንቲባ ጽ/ቤትን ያመሰገኑት ሚኒስትሩ፥ ማዕከሉ ለአካባቢ ነዋሪዎች ቅድሚያ ተጠቃሚ የሚያደረግ ስልጠናና የሥራ ዕድል በኤጀንሲው እንዲመቻችላቸውም ተናግረዋል።

    የኢትዮጵያ የመድኃኒት ፈንድና አቅርቦት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬከተር ዶ/ር ሎኮ አብርሀም በበኩላቸው የአዳማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በሌላው ዓለም የሚተገበሩ ዘመናዊ አሠራሮችን በመቀመር የመድኃኒት እና የህክምና መገልገያ አቅርቦት እና ስርጭት የልህቀት ማዕከል ሆኖ ለሌሎች ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች መማማሪያ እንዲሆን ምቹ ሁኔታዎች መፈጠራቸውን ተናግረው ለአካባቢው፥ ማኅበረሰብም የሥራ ዕድል እየፈጠረ እንደሆነ እና በቀጣይም አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

    ምንጭ፦ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    መድኃኒቶችን ማስወገጃ


    Semonegna
    Keymaster

    ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ የ2011ዓ.ም. አዲስ ገቢ ተማሪዎችን በታህሳስ ወር መጨረሻ ላይ ለመቀበል ቅድመ ዝግጅት መጨረሱን ገለጸ። ዩኒቨርሲቲ አዲስ እንደመሆኑ መጠን ራሱን ለማስፋፋት ያስችለው ዘንድ መምህራንን እና ሠራተኞችን በስፋት እየቀጠረ ነው።

    አሰበ ተፈሪ (ሰሞነኛ) – ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ የ2011ዓ.ም. አዲስ ገቢ ተማሪዎችን በታህሳስ ወር መጨረሻ ላይ ለመቀበል ቅድመ ዝግጅት መጨረሱን ገለጸ።

    የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሙክታር ሙሀመድ እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው በ2010ዓ.ም. ተማሪዎችን ለመጀመሪያ ጊዜ ተቀብሎ ማስተማር የጀመረ ሲሆን፥ በማስፋፊያ ግንባታ መዘግየት ምክንያት በ2011ዓ.ም. የተመደቡትን ተማሪዎች እስካሁን ድረስ ጥሪ ያላደረገ አብራርተው በዚህ ወር መጨረሻ ግን ለተማሪዎቹ ጥሪ እንደሚያደርግ ገለጸዋል።

    የዩኒቨርሲቲው የአስተዳደር ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ግርማ መኮንን በበኩላቸው የተማሪዎች የመኖሪያ ቤቶች (ዶርምተሪ) ግንባታ እየተጠናቀቀ በመሆኑ ዩኒቨርሲቲው በቀጣይ 15 ቀናት ውስጥ በማስታወቂያ ለተማሪዎቹ ጥሪ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

    የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የጤና እና የህክምና ሳይንስ ኮሌጅ የህክምና ዶክተሮችን ጨምሮ 220 የጤና ባለሞያዎችን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዶ/ር አሚር አማን በተገኙበት ዛሬ አስመርቋል።

    ከዚሁ ጋር በተያያዘ ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ አዲስ እንደመሆኑ መጠን ራሱን ለማስፋፋት፣ የትምህርት ክፍሎችን (ዲፓርትመንቶች) እና የተማሪዎችን ቁጥር ለመጨመር ያስችለው ዘንድ መምህራንን እና ሠራተኞችን በስፋት እየቀጠረ ነው።

    ዩኒቨርሲቲው ባለፈው ዓመት በአካባቢው ያለውን የብዝሀ ሕይወት ለመንከባከብና ለመጠበቅ በሚል ዓላማ ከኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት ጋር ተባብሮ ለመሥራት የሚያስችለውን ስምምነት መፈራረሙን መዘገባችን ይታወሳል።

    ምንጭ፦ የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር | ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ


    Semonegna
    Keymaster

    የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል የካንሰርና የልብ ህክምና ማዕከል ግንባታ 56 በመቶ ደርሷል

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሜዲካል ኮሌጅ ከ986 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የሚያስገነባው የካንሰርና የልብ ህክምና ማዕከልን በተያዘለት ግዜ ለማጠናቀቅ እየተሠራ መሆኑን ተገለጸ።

    የሆስፒታሉ የምህንድስና ኢንጂነሪንግ ክፍል አስተባባሪ ኢንጅነር ሞቲ አሰፋ ለ ኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) እንደገለጹት እየተገነቡ ያሉት የካንሰርና የልብ ህክምና ማዕከላት መጀመሪያ አካባቢ ቶሎ ወደ ሥራ ያለመግባትና በብረት ዋጋ ንረት ምክንያት መዘግየት የታየበት ቢሆንም ግንባታው 56 በመቶ ደርሷል።

    የማዕከላቱ መሠረት በ12 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈ ሲሆን ባለ12 እና 10 ወለል ህንፃዎች ይኖሩታል ብለዋል። ህንፃዎቹ ከ600 በላይ የመኝታ ክፍሎች እንደሚኖራቸው ነው ኢንጂነር ሞቲ ያብራሩት።

    ከዚሁ ጎን ለጎን ከተጀመረ ስምንት ዓመታትን ያስቆጠረውና ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የእናቶችና ህጻናት ማዕከል ባለ 8 ወለል ህንፃም በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

    በህንጻ ተቋራጩ እና ክትትል በሚያደርገው ተቆጣጣሪ ድክመት ምክንያት ተጓትቶ የነበረው ፕሮጀክቱ ባለሙያዎችን በመቀየር በአሁኑ ወቅት ሥራው በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝና በዚህ ሳምንት ከፊሉን ሥራ ለማስጀመር እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው ብለዋል።

    ◌ Ethiopia: Are Ethiopian hospitals constructed in environment-suitable and climate-friendly way?

    የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ ሜዲካል አገልግሎት ዋና ፕሮቮስት ዶ/ር ወንድማገኝ ገዛኸኝ በበኩላቸው ማዕከላቱ አገልግሎት መስጠት ሲጀምሩ በሀገሪቱ በካንሰርና በልብ ህመም ለሚሰቃዩ ዜጎች የሚሰጡት ጥቅም ከፍተኛ ነው ብለዋል። በተለይ ህክምናዎቹ የሚጠይቁት ወጪ ከፍተኛ በመሆኑ አብዛኛውን ህብረተሰብ ተጠቃሚ ያደርጋል ነው ያሉት።

    ከሰባት ዓመት በፊት ሆስፒታሉ በቀን ከ500 ያልበለጡ ህሙማንን ብቻ ያስተናግድ እንደነበር የተናገሩት ዶክተር ወንድማገኝ፥ በአሁኑ ወቅት በየቀኑ ለሁለት ሺህ ሰዎች ህክምና አገልግሎት እያገኙ ነው ብለዋል።

    በአሁኑ በወቅት በወር ለ1 ሺህ 500 እናቶች የወሊድ አገልግሎት እየተሰጠ ሲሆን በግንባታ ላይ የሚገኘው የእናቶችና ህፃናት ህንፃ ሲጠናቀቅ በቀን ለ400 እናቶች የወሊድ አገልግሎት መስጠት እንደሚችል ጠቁመዋል።

    ህንፃው 15 የማዋለጃ ክፍሎች እንደሚኖሩት የጠቀሱት ዶ/ር ወንድማገኝ በቅርቡ አገልግሎቱን ለማስጀመር ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ጋር በቅንጅት እየተሠራ መሆኑን አንስተዋል።

    የሆስፒታሉ ሀኪም ዶ/ር ዮናስ ገብረጊዮርጊስ በበኩላቸው የሚገነቡት የካንሰርና የልብ ህክምና ማዕከላት በሀገሪቱ በመንግስት በብቸኝነት አገልግሎት እየሰጠ ካለው የጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ተጨማሪ በመሆን ህብረተሰቡ የጤና አገልግሎቱን በአቅራቢያው እንዲያገኝ ያስችላል ብለዋል።

    የማዕከላቱ መገንባት በሀገሪቱ ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ የመጣውን የካንሰር ህመም ለመከላከል የሚሰጠው ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑን የተናገሩት ዶክተር ዮናስ ግንባታው በተያዘለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረግ ይገባል ብለዋል።

    ፕሮጀክቱ በሁለት ዓመት ውስጥ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቅቆ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምርም ተነግሯል።

    ምንጭ፦ ኢዜአ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የካንሰርና የልብ ህክምና ማዕከል

Viewing 15 results - 1 through 15 (of 22 total)